fa
Feedback
ጦር ሜዳ

ጦር ሜዳ

رفتن به کانال در Telegram

ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን -ከዚህ ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ -ከሥልጣናትና ከኀይላት -እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው። ኤፌ 6:12 *ጦር ሜዳ ውስጥ መሆኑን ያላወቀ ሰው ለውግያ የተዘጋጀ አይደለም፡፡ ሁሌ የተማረከ እና የተሸነፈ ነው፡፡ ሰለዚህ "የእግዚአብሔርን ሙሉ የጦር ዕቃ ልበሱ ኤፈ 6:13.... ... አስተያየት ካላችሁ @endyab

نمایش بیشتر
1 143
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+17 روز
+630 روز
آرشیو پست ها
photo content

አንተ ግን ***** መስፍን ማሞ with ዳዊት ጌታቸው እና መስከረም ጌቱ **************** ሁኔታውን ስናይ እየሆነ ያለውን ከቁጥጥር ውጪ የሆነ ሚመስለውን ለምን ይኼ ሁሉ እግዚአብሔር ካለህ ስትል ነፍስ ስትቃትት ኸረ ያምላክ ያለህ አንተ ግን በዙፋንህ ተረጋግተህ ተቀምጠሃል ሁሉንም አውቀህ እግዚአብሔር ከጅማሬ እስከፍጻሜው ባለቤት ነህ የታሪክ ጸሐፊው ባንተ ማረፍ ነው መልካሙ ምርጫ ሌላ እኮ የለም ከቶ ያለው ብልጫ ኑሮ ሲወሳሰብ ሰዉ ግራ ገብቶት ነገ አልታይ ብሎት ውሉ ሲጠፋበት እግዚአብሔር እያለ ለምን ይኼ ሆነ እያለ የሰው ልጅ እንቅልፍ ካይኑ ሸሸ አንተ ግን በዙፋንህ ተረጋግተህ ተቀምጠሃል ሁሉንም አውቀህ እግዚአብሔር ከጅማሬ እስከፍጻሜው ባለቤት ነህ የታሪክ ጸሐፊው ባንተ ማረፍ ነው መልካሙ ምርጫ ሌላ እኮ የለም ከቶ ያለው ብልጫ ሁሉ እኮ በእጅህ ነው አሳብህ ጥልቅ ነው ላመኑብህ መታመኛ እግዚአብሔር ነህ መዳኛ

No one wakes up one day and decides to become a hypocrite. It happens incrementally when the secret place dies. When a man st
No one wakes up one day and decides to become a hypocrite. It happens incrementally when the secret place dies. When a man stops praying, he stops encountering the holiness of God. When he stops encountering God's holiness, he loses his fear of God. But because he still knows how to look spiritual, how to use the language, and how to put on a show for people, he starts relying on performance instead of the power of the Holy Spirit. His public mask stays intact while his private character completely decays. The good news is that hypocrisy dies by getting back to the secret place and laying your sins bare before the Lord in repentance. Then living a lifestyle of prayer and fellowship with God.

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1:21 ​"ከፍተኛው የብስለት ደረጃ ከክርስቶስ ውጪ ሌላ ምንም ፍላጎት፣ ምንም ሀሳብ፣ ምንም ምኞት ሳይኖርክ ሲቀር ነው፤ ለክርስቶስ ሲባል መሞት ታላቅ ደስታ እንደሆነ ሲሰማክ ለክርስቶስ ሲባል በድህነት፣ በስቃይ፣ በንቀትና በመከራ ውስጥ መኖር ጣፋጭ ሆኖ ሲታይክ፣ ጌታህ እስከከበረ ድረስ በአንተ ላይ ምን እንደሚደርስ ግድ ሳይሰጥህ ሲቀር እንዲሁም እንደደረቀ ቅጠል በነፋስ ብትወሰድም የጌታ እጅ እንደ ፈቃዱ እየመራክ መሆኑን እስካወክ ድረስ ወዴት እየሄድክ እንደሆነ ግድ በማይሰጥህ ሁኔታ ውስጥ ስትሆን ነው።"         ቻርለስ ሰፐርጀን

Repost from N/a
ቅዱስ አውግስጢኖስ "ኀጢአት ማለት ቅደም ተከተሉ የተዛባ ፍቅር ነው" ብሎ እንደተረጐመው፣ ቅድስና ማለትም ቅደም ተከተሉን የጠበቀ ፍቅር ነው። ርሱ አስቀድሞ ወድዶኛልና እኔም ደግሞ እወደዋለሁ የምንልበት የፍቅር ቋንቋችን ቅድስና ይባላል። ቅድስና የሌለው ፍቅር ዱዳ ነው። ፍቅር የሌለው ቅድስናም ግብዝነት ነው። ✍️ ምናሴ ይርጉ ቆላስይስ 2:20-23 20-21 #ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ #ከክርስቶስ ጋር #ከሞታችሁ፥ 22 እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት፦ #“አትያዝ”፥ #“አትቅመስ”፥ #“አትንካ”፡ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና። 23 ይህ እንደ ገዛ #ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቆን ጥበብ ያለው ይመስላል፥ ነገር ግን ሥጋ ያለ ልክ እንዳይጠግብ ለመከልከል ምንም #አይጠቅምም።

ዮሐንስ 10:27-29 27 በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ #ይከተሉኝማል፤ 28 እኔም #የዘላለም #ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ #ለዘላለምም #አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም #አይነጥቃቸውም። 29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ #ከአባቴም እጅ #ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም። ሮሜ 6:1-2 1 እንግዲህ ምን እንላለን? #ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን? 2 አይደለም። #ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? አዳም በኔ ውስጥ ሞቷል፤ ህያው ሆኖ አይኖርም። ኢየሱስ ግን በኔ ውስጥ ይኖራል፤ ህያው ሆኖ ለዘላለም ይኖራል... አዳም በኔ እንደሞተ ብቻ ሳይሆን; እኔ በአዳም ውስጥም ሞቼአለሁ፤ አዳም በኔ, እኔም በአዳም ውስጥ ህብረት የለንም… በኔ ኢየሱስ እንደሚኖር ብቻ ሳይሆን; በኢየሱስ ውስጥም እኖራለሁ፤ እኔ በኢየሱስ, ኢየሱስ በኔ ፍጹም በሆነ አንድነት እንደምንኖር፤ እንዲሁ በኔና በመጀመሪያው ሰው መካከል ፍጹም በሆነ መለየት ተለያይተናል… ከአዳም ባለመሆኔ ከሞት፣ ከኩነኔ፣  ከመጥፋት፣ ከአሮጌ ሰውነት ሁሉ ጋር ተቆራርጬአለሁ… በኢየሱስ በመሆኔ ከህይወት፣ ከጽድቅ፣ ከአለመጥፋት፣ ከአዲሱ ሰውነት  ጋር በዘላለም ቃልኪዳን  ታስሬአለሁ.... አዳማዊ ማንነቴን  በሃጢአት በመወለድ ያገኘሁትን በመስቀል ለመቸንከር አሮጌ ማንነቴን ከአዳም ጋር ሰቀልሁ፤ ስጋዊ፣ አለማዊና ዲያብሎሳዊ የጽድቅ መሳሪያዎቼን ከእርሱ ክበብ ስወጣ ሁሉንም ቀበርኋቸው…. መሲህያዊ ማንነቴን ከሰማያዊ ልደት አገኘሁ፤ ከቅቡእ አምላክ ጸጋ  በመካፈሌ የእርሱን መልክ በሙላት እስክይዝ ድረስ  በመንፈሱ ሃይል እየተጋደልሁ ርዝራዥ አዳማዊነቴን ዘወትር እሰቅላለሁ…. በመጀመሪያው አዳም  ከሆነብኝ ይልቅ በኋለኛው አዳም የሆነልኝ እጅግ ይበዛል… ከራቅሁት ርቀት ይልቅ በኋለኛው ሰው የቀረብሁት ቅሩብነት እጅግ ድንቅ ነው…  ከተቆጠረልኝ በደል ይልቅ የተቆጠረልኝ ጽድቅ….  ከገባሁበት  ጉስቁልና ይልቅ የ ወጣሁበት ከፍታ.... በተፈጥሮ ከነበርሁበት  ጭለማ ይልቅ በልእለ ተፈጥሮ የበራልኝ የብርሃን ድምቀት.... ከታወጀብኝ  ከሞት ኩነኔ ይልቅ የታወጀልኝ የጽድቅ ብዛቱ በቀላሉ እንዲህ ተብሎ የማይነገር ግሩም መለኮታዊ ችሮታ የተገለጠበት  ነው…. ✍️TTL (https://t.me/LOGOSJO1)

ዮሐንስ 10:27-29 27 በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ #ይከተሉኝማል፤ 28 እኔም #የዘላለም #ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ #ለዘላለምም #አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም #አይነጥቃቸውም። 29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ #ከአባቴም እጅ #ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም። ሮሜ 6:1-2 1 እንግዲህ ምን እንላለን? #ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን? 2 አይደለም። #ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? አዳም በኔ ውስጥ ሞቷል፤ ህያው ሆኖ አይኖርም። ኢየሱስ ግን በኔ ውስጥ ይኖራል፤ ህያው ሆኖ ለዘላለም ይኖራል... አዳም በኔ እንደሞተ ብቻ ሳይሆን; እኔ በአዳም ውስጥም ሞቼአለሁ፤ አዳም በኔ, እኔም በአዳም ውስጥ ህብረት የለንም… በኔ ኢየሱስ እንደሚኖር ብቻ ሳይሆን; በኢየሱስ ውስጥም እኖራለሁ፤ እኔ በኢየሱስ, ኢየሱስ በኔ ፍጹም በሆነ አንድነት እንደምንኖር፤ እንዲሁ በኔና በመጀመሪያው ሰው መካከል ፍጹም በሆነ መለየት ተለያይተናል… ከአዳም ባለመሆኔ ከሞት፣ ከኩነኔ፣  ከመጥፋት፣ ከአሮጌ ሰውነት ሁሉ ጋር ተቆራርጬአለሁ… በኢየሱስ በመሆኔ ከህይወት፣ ከጽድቅ፣ ከአለመጥፋት፣ ከአዲሱ ሰውነት  ጋር በዘላለም ቃልኪዳን  ታስሬአለሁ.... አዳማዊ ማንነቴን  በሃጢአት በመወለድ ያገኘሁትን በመስቀል ለመቸንከር አሮጌ ማንነቴን ከአዳም ጋር ሰቀልሁ፤ ስጋዊ፣ አለማዊና ዲያብሎሳዊ የጽድቅ መሳሪያዎቼን ከእርሱ ክበብ ስወጣ ሁሉንም ቀበርኋቸው…. መሲህያዊ ማንነቴን ከሰማያዊ ልደት አገኘሁ፤ ከቅቡእ አምላክ ጸጋ  በመካፈሌ የእርሱን መልክ በሙላት እስክይዝ ድረስ  በመንፈሱ ሃይል እየተጋደልሁ ርዝራዥ አዳማዊነቴን ዘወትር እሰቅላለሁ…. በመጀመሪያው አዳም  ከሆነብኝ ይልቅ በኋለኛው አዳም የሆነልኝ እጅግ ይበዛል… ከራቅሁት ርቀት ይልቅ በኋለኛው ሰው የቀረብሁት ቅሩብነት እጅግ ድንቅ ነው…  ከተቆጠረልኝ በደል ይልቅ የተቆጠረልኝ ጽድቅ….  ከገባሁበት  ጉስቁልና ይልቅ የ ወጣሁበት ከፍታ.... በተፈጥሮ ከነበርሁበት  ጭለማ ይልቅ በልእለ ተፈጥሮ የበራልኝ የብርሃን ድምቀት.... ከታወጀብኝ  ከሞት ኩነኔ ይልቅ የታወጀልኝ የጽድቅ ብዛቱ በቀላሉ እንዲህ ተብሎ የማይነገር ግሩም መለኮታዊ ችሮታ የተገለጠበት  ነው…. ✍️TTL (https://t.me/LOGOSJO1)

Repost from N/a
1 ጴጥሮስ 1:18-19,23 18-19 ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ። 23 ዳግመኛ #የተወለዳችሁት #ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ #በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል #ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ። 🚧 መቀደስ #ከልጅነት አይቀድምም ፤ ልጅነቱን ያለወቀ ሰው ልቀድስ ቢል እንኳ አይቀደስም ፤ #“ከፈረሱ ጋሪ” እንደሚል የሀገሬ ሰው ፤ #ጋሪው #ከፈረስ ከቀደመ መሰነካከል ነው እንጂ ትርፉ ፣ አንድ እርምጃ አያስኬድም ፤ ከራሳችን የሚንፈጥረው ቅድስናም የለንም ፤ በውሳጣችን ካለው ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ከተቀበልነው የቅድስና 🍓ዘር የተነሳ ነው እለት እለት የሚንቀደሰው ! 😁 ሲጃራ 🚬  pocket ላይ “ ማጨስ ሳንባን ይጎዳል” ተብሎ  ሰው ሲጃራን ያጨሳል ! ግን ይህ ሰው ወደ ክርስቶስ ስመጣ ፣ ሳንባን ይጎዳል ተብሎ ሳይሆን ሲጃራን የሚያቆመው ፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ከተቀበለው ከቅድስና ዘር ነው ! እናም የሚበልጠውን ክርስቶስ ስለያዘ ነው ! 🗯️🗯️ ለዚህም ነው ጳውሎስ የቆላስይስ ሰዎችን እንደዚህ የሚላቸው ፦ ቆላስይስ 2:20-23 20-21 ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር #ከሞታችሁ፥ 22 እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት፦ #“አትያዝ”፥ #“አትቅመስ”፥ #“አትንካ”፡ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና። 23 ይህ እንደ ገዛ ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቆን #ጥበብ ያለው ይመስላል፥ ነገር ግን ሥጋ ያለ ልክ እንዳይጠግብ ለመከልከል #ምንም አይጠቅምም። 🐬አሳ ማንነቱ መዋኘት ነው ፤ አትወኝ ብትለውም ይዋኛል 🚧 ብቻ  ከውሃ ውስጥ አይውጣ እንጂ! 🚧እኛም የክርስቶስ ዘር በውስጣችን ይኑር እንጂ ፤ እለት እለት #መቀደስ ማንነታችን ነው !  🚧ብቻ ከፀጋው እንዳንወጣ ! ሮሜ 6:6 6 ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና። #መቀደስ ከውስጥ እንጂ በውጫዊ ግፊት አይደለም ፤ #ፍቅር ያዋረደውን #ክርስቶስን እያያን #እንቀደሳለን ፤ በፀጋው ሆነን #እንቀደሳለን #በራስ ጥረት ሰው አይቀደስም !

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ "ተው" እየተባለ የማይሰማ ሰው"ይሄ መንገድ አያስኬድም ተመለስ" እየተባለ የምይመለስ ሰው 👉 ለጥፋት የተዘጋጀ ነው ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ዔሊ ልጆቹን "ትክክል አይደላችሁም፣ ተው" ስላቸው፣ ልጆቹ "የአባታቸውን ተግሣጽ አልሰሙም" ነበር። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ከዛ እንዲህ ይላል:- "እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ስለ ፈለገ፣ ልጆቹ የአባታቸውን ተግሣጽ አልሰሙም።" 📖 1ሳሙ 2:25 ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ▪️ ልጆቹ የእግዚአብሔር መሥዋዕት ያቃልሉ ነበር ▪️ በዝሙት እና መዳራት ይመላለሱ ነበር ▪️ የመጥፎ ተግባራቸው ወሬ በእግዚአብሔር መካከል ተሰራጭቶ ነበር 📖 1ሳሙ 2:22-25 ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚠️ ማስጠንቀቂያ "የተግሣጽ ድምፅ የማይሰማ ሰው መጨረሻው ጥፋት ነው" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

ሠርገኛ ነህ ወይስ ለቀስተኛ? *** ወደ ገላትያ ሰዎች 2:21 --- ²¹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ። ወዳጄ፦ ✍️ ለአይሁድ ተሰጥቶ የነበረውን የሙሴ ሕግ ካልፈጸምኩ ብሎ መፍጨርጨር ለአሜሪካ መንግሥት ግብር ካልከፈልኩ ብሎ እንደመጨነቅ ነው!! ✍️ ለአሜሪካ መንግሥት ግብር ክፈል እንዳልተባልክ ሁሉ የሙሴንም ሕግ ጠብቅ አልተባልክም!! ✍️ የሙሴ ሕግ የተሰጠው ለአይሁዳውያን ብቻ እንጂ ለአለም ሁሉ አይደለም!! ✍️ የሙሴ ሕግ በራሱ የተመሰረተው የሌዊ ክሕነት ላይ ነው!! ✍️ በሙሴ ሕግ ሊቀካሕናቱ አሮን እንጂ ኢየሱስ አይደለም!! ✍️ ኢየሱስን ካሕን አድርጎ ያልሾመን የሙሴ ሕግ ጠብቂ የተባለች ቤተክርስቲያን የለችም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ደመወዝ እንጂ ስጦታ የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ የራስ ጥረት እንጂ የጸጋ እርዳታ የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ መስራት እንጂ ማመን አይቻልም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ባርነት እንጂ ልጅነት የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ መርከስ እንጂ መጽደቅ አይታወቅም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ሞት እንጂ ሕይወት የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ፍርሀት እንጂ ድፍረት የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ መቅሰፍት እንጂ ምህረት አይታወቅም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ኩነኔ እንጂ ሰላም የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ሀዘን እንጂ ደስታ የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ለቅሶኛ እንጂ ሠርገኛ የለም!! 📌 ጸጋ የተሰጠው ለአለም ሁሉ እንጂ ለአይሁዳውያን ብቻ አይደለም!! 📌 በጸጋ ሊቀካሕናቱ ኢየሱስ እንጂ አሮን አይደለም!! 📌 በጸጋ ጽድቅ እንጂ ኩነኔ የለም!! 📌 በጸጋ ሰላም እንጂ መታወክ የለም!! 📌 በጸጋ በረከት እንጂ እርግማን የለም!! 📌 በጸጋ ሕይወት እንጂ ሞት የለም!! 📌 በጸጋ ስጦታ እንጂ ደመወዝ የለም!! 📌 በጸጋ እረፍት እንጂ መባከን የለም!! 📌 በጸጋ መቻል እንጂ መዛል የለም!! 📌 በጸጋ መርካት እንጂ መጠማት የለም!! 📌 በጸጋ ልጅነት እንጂ ባርነት የለም!! 📌 በጸጋ ደስታ እንጂ ሀዘን የለም!! 📌 በጸጋ መቀደስ እንጂ መርከስ የለም!! 📌 በጸጋ ድፍረት እንጂ ፍርሀት የለም!! 📌 በጸጋ ድል እንጂ ሽንፈት የለም!! 📌 በጸጋ ሠርገኛ እንጂ ለቅሶኛ የለም!! 👉 እኔ በጸጋው አርፌአለሁና ሠርገኛ ነኝ!! አንተስ.....ሠርገኛ ነህ ወይስ ለቅስተኛ? በእኔ ኑሩ በፍቅሬም ኑሩ በኢየሱስ መኖር ማለት በፍቅር መኖር ነው ኢየሱስ የኖረው በአብ ፍቅር መንፈስ ቅዱስ በኢየሱስ ፍቅር እንድንኖር ኃይለችን ነው በኢየሱስ መኖር ማለት ትዕዛዙን መጠበቅ ነው ትዕዛዙ ደግሞ ፍቅር ነው የኢየሱስ ፍሬ ፍቅር ነው የእኛም ፍሬያችን ፍቅር ነው አንዳንድ ጊዜ መኖር ቤተክርስቲያን መሄድ፣ መንፈሳዊ ሕብረት ማድረግ፣ መጸለይ፣ ቃል መጥናት ብቻ የምንወዳቸው ሰዎች ብቻ ሁሉም ነገር ያስጠላናል በቃ ይህን ስሜት መካድ አንችልም ራሳችንን አንወሽ ስሜቱን እንቀበለው  ይህ ስሜት የሚሰማን እኛ ብቻ አይለንም "በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ "እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤" እወነታውን ተቀብለን ስንደክምም ብርቱዎች ነን በእግዚአብሔር እንጽናና።። ይህች አለም እንኳን ለእኛ ለኢየሱስም አልተመቻቸም !!! ብርቱ ደካማ ደካማ ብርቱዎች ነን አይዟችሁ ጸጋው የሚዋልሉትን ይደግፋል ያልተገባ ሞገስ ይብዛላችሁ ✍️TTG

ሠርገኛ ነህ ወይስ ለቀስተኛ? *** ወደ ገላትያ ሰዎች 2:21 --- ²¹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ። ወዳጄ፦ ✍️ ለአይሁድ ተሰጥቶ የነበረውን የሙሴ ሕግ ካልፈጸምኩ ብሎ መፍጨርጨር ለአሜሪካ መንግሥት ግብር ካልከፈልኩ ብሎ እንደመጨነቅ ነው!! ✍️ ለአሜሪካ መንግሥት ግብር ክፈል እንዳልተባልክ ሁሉ የሙሴንም ሕግ ጠብቅ አልተባልክም!! ✍️ የሙሴ ሕግ የተሰጠው ለአይሁዳውያን ብቻ እንጂ ለአለም ሁሉ አይደለም!! ✍️ የሙሴ ሕግ በራሱ የተመሰረተው የሌዊ ክሕነት ላይ ነው!! ✍️ በሙሴ ሕግ ሊቀካሕናቱ አሮን እንጂ ኢየሱስ አይደለም!! ✍️ ኢየሱስን ካሕን አድርጎ ያልሾመን የሙሴ ሕግ ጠብቂ የተባለች ቤተክርስቲያን የለችም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ደመወዝ እንጂ ስጦታ የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ የራስ ጥረት እንጂ የጸጋ እርዳታ የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ መስራት እንጂ ማመን አይቻልም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ባርነት እንጂ ልጅነት የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ መርከስ እንጂ መጽደቅ አይታወቅም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ሞት እንጂ ሕይወት የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ፍርሀት እንጂ ድፍረት የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ መቅሰፍት እንጂ ምህረት አይታወቅም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ኩነኔ እንጂ ሰላም የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ሀዘን እንጂ ደስታ የለም!! ✍️ በሙሴ ሕግ ለቅሶኛ እንጂ ሠርገኛ የለም!! 📌 ጸጋ የተሰጠው ለአለም ሁሉ እንጂ ለአይሁዳውያን ብቻ አይደለም!! 📌 በጸጋ ሊቀካሕናቱ ኢየሱስ እንጂ አሮን አይደለም!! 📌 በጸጋ ጽድቅ እንጂ ኩነኔ የለም!! 📌 በጸጋ ሰላም እንጂ መታወክ የለም!! 📌 በጸጋ በረከት እንጂ እርግማን የለም!! 📌 በጸጋ ሕይወት እንጂ ሞት የለም!! 📌 በጸጋ ስጦታ እንጂ ደመወዝ የለም!! 📌 በጸጋ እረፍት እንጂ መባከን የለም!! 📌 በጸጋ መቻል እንጂ መዛል የለም!! 📌 በጸጋ መርካት እንጂ መጠማት የለም!! 📌 በጸጋ ልጅነት እንጂ ባርነት የለም!! 📌 በጸጋ ደስታ እንጂ ሀዘን የለም!! 📌 በጸጋ መቀደስ እንጂ መርከስ የለም!! 📌 በጸጋ ድፍረት እንጂ ፍርሀት የለም!! 📌 በጸጋ ድል እንጂ ሽንፈት የለም!! 📌 በጸጋ ሠርገኛ እንጂ ለቅሶኛ የለም!! 👉 እኔ በጸጋው አርፌአለሁና ሠርገኛ ነኝ!! አንተስ.....ሠርገኛ ነህ ወይስ ለቅስተኛ? በእኔ ኑሩ በፍቅሬም ኑሩ በኢየሱስ መኖር ማለት በፍቅር መኖር ነው ኢየሱስ የኖረው በአብ ፍቅር መንፈስ ቅዱስ በኢየሱስ ፍቅር እንድንኖር ኃይለችን ነው በኢየሱስ መኖር ማለት ትዕዛዙን መጠበቅ ነው ትዕዛዙ ደግሞ ፍቅር ነው የኢየሱስ ፍሬ ፍቅር ነው የእኛም ፍሬያችን ፍቅር ነው አንዳንድ ጊዜ መኖር ቤተክርስቲያን መሄድ፣ መንፈሳዊ ሕብረት ማድረግ፣ መጸለይ፣ ቃል መጥናት ብቻ የምንወዳቸው ሰዎች ብቻ ሁሉም ነገር ያስጠላናል በቃ ይህን ስሜት መካድ አንችልም ራሳችንን አንወሽ ስሜቱን እንቀበለው  ይህ ስሜት የሚሰማን እኛ ብቻ አይለንም "በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ "እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤" እወነታውን ተቀብለን ስንደክምም ብርቱዎች ነን በእግዚአብሔር እንጽናና።። ይህች አለም እንኳን ለእኛ ለኢየሱስም አልተመቻቸም !!! ብርቱ ደካማ ደካማ ብርቱዎች ነን አይዟችሁ ጸጋው የሚዋልሉትን ይደግፋል ያልተገባ ሞገስ ይብዛላችሁ ✍️TTG

Repost from N/a
በህይወት ምልልስ ውስጥ ብዙ ኃላፊነቶች፣ ፈተናዎች ሊገጥምህ ይችላል። እግዚአብሔር ግን በራስህ ብቻ እንድንተማመን አይፈልግም። ክርስቶስ ለሚገጥም ማንኛውም ነገር ሁሉ ኃይልን ይሰጥሀል። ሁሉን መቻል
በህይወት ምልልስ ውስጥ ብዙ ኃላፊነቶች፣ ፈተናዎች  ሊገጥምህ ይችላል። እግዚአብሔር ግን በራስህ ብቻ እንድንተማመን አይፈልግም። ክርስቶስ ለሚገጥም ማንኛውም ነገር  ሁሉ ኃይልን  ይሰጥሀል። ሁሉን መቻል ማለት የፈለከውን ሁሉ በራስህ ኃይል ታደርጋለህ ማለት አይደለም። ይልቁንም በክርስቶስ ኃይል ፈተናን ማለፍ፣ ታማኝ ሆኖ መኖር ማለት ነው። ዛሬ የሳምንቱን ስትጀም  በፍርሃት ወይም በጭንቀት ሳይሆን ክርስቶስ ከአንተ ጋር እንዳለ በመታመን ጀምር። ምንም ዓይነት ሸክም ወይም ፈተና ቢመጣ ብቻህን አይደለህም።
ፊልጵስዩስ 4:13 ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
✍️ #tesfa #hope

#She gave attention to the conversation, and humanity was cursed. #Jesus shut down the conversation, and humanity was redeeme
#She gave attention to the conversation, and humanity was cursed. #Jesus shut down the conversation, and humanity was redeemed. The Word teaches us to be careful what we give our ears and hearts to. Deception brings destruction, but truth brings life.

Repost from Heart of Christ
✍️መታዘዝ ማለት ለራስህ ስሜት ጨክነህ ለእግዚአብሔር ፈቃድ እሽ ማለት ነው። አብርሃም ከቤቱ እስማኤልን ስያሰናብት ልቡ አዝኖ ነበር በልጁ በእስማኤል መጨከን ከብዶት ነበር
“ይህም ነገር በአብርሃም ዘንድ ስለ ልጁ እጅግ ችግር ሆነበት።” ዘፍጥረት 21፥11
ግን አብርሃም ይስሐቅን እግዚአብሔር ሰዋልኝ ባለው ጊዜ ለምን አልተከራከረም? ለምንስ ልቡ አልጨከነም? በተስፋ ያገኘውን የእርጅና ጊዜ ምርኩዙን ይስሐቅን የብዙ ጊዜ ጸሎቱን በብዙ ጥበቃ እና ትዕግሥት ወደ ቤቱ የመጣውን ይስሐቁን ሰዋልኝ ስለው ለምን አይሆንም አላለውም? ለእስማኤል የራራው የአባትነት ልቡ በይስሐቅ ለምን ዝም አለ? ለምን መሰላችሁ....
ጉዳዩ ስለ ልጁ አይደለም ጉዳዩ ስለ ጠያቂው ታላቅነት ነው።ጠያቂው እግዚአብሔር ነዋ።
እግዚአብሔር ስጠይቅ ርህራሄ ትዕዛዝ ይሆናል። እግዚአብሔር ስጠይቅ ፍቅር መታዘዝ ይሆናል። እግዚአብሔር ስጠይቅ ድጋሚ ማሰብ ክህደት ይሆናል። የጥያቄው ክብደት የሚለካው በጠያቂው ማንነት ነው። አብርሃም ለእስማኤል አዝኖ ለይስሐቅ የጨከነው ለጠያቂው ያለው ፍቅር ለልጁ ካለው ፍቅር ሰለበለጠ ነው።
እግዚአብሔር ስጠይቅ ድጋሚ ማሰብ አለመታዘዝ ነው።
አብርሃም ይስሐቅን ይዞ ወደ ተራራው ስወጣ ልጁን ስለጠላው ሳይሆን አምላኩን ስለወደደው ነበር። ዛሬ እኛስ ውድ ነው የምንለውን ነገር ለእግዚአብሔር በመታዘዝ እንሰዋ ይሆን? ጊዜያችንን፣ልጅነታችንን፣ነገያችንን፣ውድ ነው ማንንም አላስነካም ያልነውን፣በቤታችን ውድ ነው ያልነውን ለእርሱ እንተው ይሆን? እግዚአብሔር አምጣው የሚለን ነገር ያለ እርሱ መኖር አልችልም የምንለውን ነገራችንን ነው።
እግዚአብሔር የሚጠይቀን ያጣነውን የሌለንን ነገር ሳይሆን አጥብቀን የያዝነውን አንለቅም ያልነውን ነው
እግዚአብሔር ይስሐቅን የፈለገው እንዲሞት ሳይሆን በአብርሃም ልብ ውስጥ ያለውን የራሱን ቦታ ለማየት ነው። ወዳጆቼ እግዚአብሔር አንዳች ነገር ፈልጎ ሰዋልኝ ባለን ጊዜ በሙሉ መታዘዝ መሰዋት ይሁንልን። እርሱን የምንከለክለው ነገር አይኑረን። ጌታ ሆይ ዛሬ እንደ አብርሃም እነሆኝ የምልበትን ልብ ስጠኝ። ውድ ነው ማንንም አላስነካውም ብዬ አጥብቀ የያዝኩትን በልቤ ዙፋን ያስቀመጥኩትን ይስሐቄን እንድሰዋልህ ልቤን በመታዘዝ መንፈስ ባርክልኝ። ለዓለም ጉዳይ የምሮጥበትን የራሴን ስም ለማስጠራት የምለፋበትን ጊዜዬን ወስደህ አንተን ለማገልገልና ድምፅህን ለመስማት እንድጠቀም እርዳኝ። ጌታ ሆይ እውቀቴን ለአንተ ጊዜየን ለቃልህ ነገን ደግሞ ለታማኝነትህ አሳልፌ እሰጣለሁ። መታዘዝ ከመስዋዕት እንደ ሚበልጥ በምክንያት ከምከራከር ልብ ይልቅ ለቃልህ የሚገዛ የትህትና መንፈስ በውስጠ አሳድር። የምሳሳለትን ሁሉ በአንተ እጅ ማኖር ይሁንልኝ። ለአንተ እሽታን አስተምረኝ። በአብርሃም እምነትና መታዘዝ ባርከን።🙌

Repost from N/a
1 ቆሮንቶስ 1:8-9 8 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትገኙ እርሱ እስከ መጨረሻው ድረስ ##አጽንቶ ##ይጠብቃችኋል። 9 ወደ ልጁ፣ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ
1 ቆሮንቶስ 1:8-9 8 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትገኙ እርሱ እስከ መጨረሻው ድረስ ##አጽንቶ ##ይጠብቃችኋል። 9 ወደ ልጁ፣ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር ##የታመነ ነው። ይሁዳ 1:24-25 24 ##እንዳትወድቁ ##ሊጠብቃችሁና ያለ ነቀፋና በደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችለው፣ 25 እርሱ ብቻ አዳኛችን ለሆነው አምላክ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ከዘመናት ሁሉ በፊት፣ አሁንና እስከ ዘላለምም ድረስ ክብር፣ ግርማ፣ ኀይልና ሥልጣን ይሁን፤ አሜን። 1 ጴጥሮስ 5:10 10 በክርስቶስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ፣ ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ እርሱ ራሱ መልሶ ያበረታችኋል፤ ##አጽንቶም #ያቆማችኋል። 2 ጢሞቴዎስ 1:9 9 እኛ ##ስላደረግነው ##አንዳች ነገር ሳይሆን፣ ከዕቅዱና ከጸጋው የተነሣ ያዳነን፣ ወደ ቅዱስ ሕይወትም የጠራን እርሱ ነው። ##ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፤ ##በዚህ ልክ ሊጠብቀን የሚችል ታማኝ ሊቀካህናት ኢየሱስ ስላለልን ከቶ ስጋት አይገባንም ፤ ከመስቀሉ ላይም አይናችንን አናነሳም ፤ ኢየሱስ በልባችን እስክሳልም ምጥ ይይዘናል “(ገላትያ 4:19 19 የምወድዳችሁ ልጆቼ ሆይ፤ ክርስቶስ በውስጣችሁ እስኪቀረጽ ድረስ፣ ስለ እናንተ እንደ ገና ምጥ ይዞኛል፤...)” 🙏ይሄንን ለምታነቡ ሁሉ ፤ 🙏ፀሎቴ🙏 ይህ ነው ፣#ክርስቶስ በፊታችሁ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ይሳል፤ #ከምትዳሱት ፣ #ከጨበጣችሁት ነገር በላይ ፤ #ከራሳችሁ በላይ ፤ #በክርስቶስ ላይ መታመን ይሁንላችሁ 🙏 ✍️ወንድም አሻግሬ

ልጅ አባቱን፣ ባሪያም ጌታውን ያከብራል፤ #እኔ #አባት #ከሆንሁ#መከበሬ #የት #አለ? #ጌታስ #ከሆንሁ #መፈራቴ #የት #አለ?” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት፤ ሚልክያስ 1:6 አባት እንደ አባትነቱ ይከበራል ጌታም እንደ ጌትነቱ ይፈራል። እግዚአብሔር አባታችን ከሆነ ለስጋ አባቶቻችን እንኳን አክብሮት እንደምናሳይ በሰማይ ላለው አባታችን የበለጠውን አክብሮት ልናሳይ ይገባል። ኢየሱስ ጌታችን ከሆነ እንደጌትነቱ በፍርሃት እናገልግለው።

photo content

Repost from N/a
ደባል የለኝም ህይወቴን ሚጋራ ግማሹ በአንተ ግማሹን ሌላ የሚመራ መልሼ ላልወስደው ሰጥቼሃለሁ ራሴን ለውድድር የማትቀርብ ምርጫዬ ስለሆንክ      ለእኔ ህይወት ኢየሱስ ነህ         ፊልጵስዩስ 1:21 21 ለእኔ፣ መኖር ክርስቶስ ነው፤ ሞትም ማትረፍ ነው። መኖር የማልችለው ካላንተ ብቻ ነው ... ያለ #ሀብት ያለ #ዝና ያለ #ዘመድ... መኖር እችላለሁ ግን #ያላንተ(ኢየሱስ) #እስትንፋስ የለኝም !  ለእኔ ሌላ ትምክህት የለኝም 😭             ገላትያ  6:14 14 ነገር ግን ዓለም ለእኔ ከተሰቀለበት፣ እኔም ለዓለም ከተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር፣ ሌላው ትምክሕት ከእኔ የራቀ ይሁን። አንድአንዱ “ያላአንቺ መኖር አልችልም ይላል (ፍቅረኛውን)  ፤  ያላንተ መኖር አልችልም ትላለች (ፍቅረኛዋን) ”  ግን ተመልሰው አንቺን ማየት አልፈልግም ፤ አንተን ማየት አልፈልግም ይባላሉ ! ግን #ኢየሱሴ ያንተ ፍቅር ወረት የለበትም ፤ ለዚህ ነው ያላንተ ብቻ ባዶ የሆንኩት   ❤ፍቅሬን የማፈሰው አንተ ላይ ብቻ ነው  😭 እንባዬም የሚፈሰው በአንተ ላይ ብቻ ነው ከራሴ በላይ እወድሃለሁ ፤ ነፍሴ በአንተ ፍቅር   ⛓️ ታስራለች ⛓️  ወደሌላው እንደልሄድ የፍቅርህ ⛓️ሰንሰለት ⛓️ አስሮኛል ⛓️          ወደ ገላትያ ሰዎች 6:17 --- ¹⁷ እኔ የኢየሱስን ማኅተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ስንኳ አያድክመኝ።              ✍️ወንድም አሻግሬ

#መነሻ#ሃሳብ/ምክንያት/motives/intentions/driving force/desires:- **** Test your motives,,,,,,,,ask God to reveal your true motives to you,,,,,,,test why you are doing what you are doing......... መነሻ ሀሳባችሁን መርምሩ,,,,,,,,,የምታደርጉትን #ለምን እንደምታደርጉ መርምሩ,,,,,,,,, #ሩጫችሁ #በከንቱ #እንዳይሆን,,,,,,, ****** 👉 ከእያንዳንዱ ድርጊት ጀርባ ድርጊቱ የሚደረግበት #መነሻ #ሀሳብ በልብ አለ። 👉መልካም የሆኑ ድርጊቶች መነሻ ሃሳባቸው መልካም ላይሆን ይችላል። ስለዚህ ነው የድርጊታችንን መነሻ ሃሳብ ቁጭ ብለን መመርመር ያለብን። 👉በጎ የሆነው ድርጊት ትክክለኛ ባልሆነ መነሻ ሀሳብ ከተከናወነ በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ አይኖረውም። ✅ትሁት ስንሆን,,,,,በሰው ለመወደስ ወይስ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት❓ ✅ሌሎችን ስናገለግል,,,,,, በሰው ዘንድ ትሁት ለመባል ወይስ እግዚአብሔርን ለማገልገል❓ ✅ ካለን ስናካፍል,,,,,, ውይይይ እሱስ/እሷስ ለጋስ ናት ለመባል ወይስ እግዚአቅሔርንና መንፈሳችንን ደስ ለማሰኘት❓ ✅ቤተክርስቲያን ለመሄድ ስንነሳ,,,,, እሱ/እሷ ቤተክርስቲያን ትሄዳለች/ይሄዳል ለመባል ወይስ በህብረት ጌታን ለማምለክ❓ ✅ ቤተክርስቲያንንስናገለግል,,,,, ከሰው ጎሽ መባልን ከመፈለግ ይልቅ በሰማይ ሃብት ለማከማቸት❓ ✅ከሐጢያት ለመራቅ ስንወስን,,,,,, በሰው ዘዘንድ እንደ ቅዱስ (sacred)ለመታየት ወይስ ለእግዚአብሔር ክብር❓ ✅እውነት መናገር ስንጀምር,,,,,, በሰው ለመወደድ ወይስ በእግዚአብሔር ለመወደድ❓ ✅መንፈሳዊ ልምምድ ውስጥ ስንገባ,,,,,, በሌሎች ለመፍረድ ወይስ ተገበቢ እና በእግዚአብሔር ዘዘንድ ደስ የሚያሰኝ ስለሆነ❓ መጠነኛ የሆነ አለባበስ ስንለብስ,,,,,,, ሌሎችን ለመኰንን ወይስ ለእግዚአብሔር ክብር❓ ✅ወንጌል ለመስበክ ስንነሳ,,,,,,, ለራሳችን ክብር ወይስ ለእግዚአብሔር ክብር❓ ✅በsocial media መንፈሳዊ መልዕክት ስናጋራ,,,,,,, እራሳችንን promote ለማረግ ወይስ ጌታ ኢየሱስን ለማጉላ❓ ✅መፅሐፍ ቅዱስ ስናነብ,,,,,, ነገ ወጥተን ጥቅስ እየመዘዝን ለመከራከር ወይስ የውስጥ የውስጥ ማንነታችንን በእግዚአበብሔር ቃል እውቀት ለማሳደግ❓ አስራት ስንከፍል,,,,,,, በጎ ስጦታ ስንሰጥ,,,,,,, ለታይታ ወይስ ለጌታ ቤት❓ ✅ሌሎችን ስንመክር,,,,,,ሌሎችን ስንገስፅ,,,,,, ራሳችንን በበፊታቸው ለማመፃደቅ ወይስ በቅን ለብ ልንመልሳቸው❓ የታመመን፣ የታሰረን፣ የደከመን ስንጎበኝ,,,,,,,,,,,,,, አልቀረም ለመባል ወይስ ከልብ በሃዘኔታና በርህራሄ ❓ እነዚህን ሁሉ ለማድረግ ስንነሳ በልባችን ያለው መነሻ ሃሳብ ምንድነው የሚለውን ቁጭ ብለን ልንመረምር ይገባናል። ✅ምክንያቱም በእግዚአብሔር ዘንድ መጀመሪያ ዋጋ ያለው ድርጊቱ የተደረገበት መነሻ ሃሳብ ስለሆነ። ✅ሰው የተገለጠውን ድርጊት ብቻ ያያል እግዚአብሔር ግን በልብ ያለውን ሃሳብ ያያል። ***** ✅የልባችሁ ሃሳብ በእግዚአብሔር ዘንድ ቀና ካልሆነ የምታደርጉት ሁሉ ከግብዝነት እና እራስን ከመውደድ ከማክበር promote ከማድረግ እንጂ እግዚአብሔር ለማክበር ስላልሆነ ረጅም ርቀት መጓዝ #አትችሉም።ቶሎ ተፋ ትቆርጣላችሁ ትጋታችሁ ሁሉ ቀጣይነት የለውም። ✅ለአንድ ቀን ለሁለት ቀን ለታይታ ሳይሆን የሰማይን ሀገር ለመዝልቅ እንደሚጓዝ ሰው የሚያዘልቅን የማያዝልን የሚያበረታታን የልብ ሃሳብ ያዙ። አትከስሩም። ✅የበጎ ድርጊታችሁን ዋጋ ጠፊ በሆነው ምድራዊ ነገር አትመዝኑ ይልቁን ለሰው ፊት ሳያደላ ከሚከፍለው ከእግዚአብሔር በብዙ እጥፍ ታተርፋላችሁ። ✅ዋጋችሁን ከሰዎች ተቀብላችሁ እንደሆነ ግን ከእግዚአብሔር ምን አለኝ ትላላችሁ??? 🙏ስለዚህ ቁጭ ብላችሁ የልባችሁን ሃሳብ መርምሩ፤ እግዚአብሔር የልባችሁን መነሻ ሃሳብ እንዲገልጥላችሁ ለምኑት። ሃሳባችሁ መንፈስ ቅዱስን ደስ የማያሰኝ እግዚአብሔር የማያከብር ከሆነ ተመልሳችሁ መነሻ ሃሳባችሁን እስክታርሙ ድረስ አንዳች አታድርጉ። Your motives determine how far you can go.

Repost from N/a
አታንብብ 😁 ! በጣም ይጠቅምሃል 😁 🧒 አንድ ወጣት በከተማው ውስጥ ወደሚገኝ አንድ ትልቅ 🥬 የአትክልት ስፍራ ይሄዳል። በዚያም አንድ እጅግ የሚያምር፣ ቅጠሎቹ የለመለሙ፣ ግንዱ የጠነከረ እና ፍሬዎቹ ያማሩ ግዙፍ ዛፍ ይመለከታል። በዛፉ ግርማ ሞገስ እና ውበት ተደንቆ አትክልተኛውን ይጠይቀዋል። ​"ይህ ዛፍ እንዴት እንዲህ ሊያምርና ሊያፈራ ቻለ? ሌሎቹ ዛፎች በድርቅ ሲጠወልጉ ይህኛው ግን እጅግ ለምልሟል፤ ሚስጥሩ ምንድን ነው?" አለው። ​አትክልተኛውም ፈገግ ብሎ መለሰ፦ "ልጄ፣ ሚስጥሩ ከላይ በምታየው ቅርንጫፍ፣ አበባ ወይም ቅጠል ላይ አይደለም። ሚስጥሩ ከመሬት በታች፣ ከሰው እይታ ተሰውሮ በሚገኘው 'ስሩ' ላይ ነው። የዚህ ዛፍ ስሮች እጅግ ወደ ጥልቅ መሬት ስለገቡ፣ ከየትኛውም ዛፍ በላይ ውሃን ከሩቅ መሳብ ይችላሉ። ከላይ የምታየው ውበት ሁሉ፣ ከታች ከተደበቀው ስር የመጣ ነው።" 📚 መጽሐፍ ማንበብ ማለት ለአንድ ሰው አእምሮ ልክ እንደ ዛፍ ስር ነው። ሰዎች ክፍልህ ውስጥ ብቻህን ሆነህ 📚መጽሐፍ ስታነብ ላያዩህ ይችላሉ፤ የምታነበው 📚መጽሐፍም ወዲያውኑ ውጫዊ ለውጥ ላያሳይህ ይችላል። ነገር ግን የምታነባቸው 📚መጽሐፍት በአእምሮህ ውስጥ ጠንካራ ስር እየሰደዱ ይሄዳሉ። ​በመጨረሻም... አነጋገርህ፣ አስተሳሰብህ...ስብዕናህ ልክ እንደ ዛፉ ፍሬዎች አምረው እና ለምልመው ለሰዎች መታየት ይጀምራሉ። አእምሮውን በንባብ ያላጠነከረ እና የራሱ ስር የሌለው ሰው ግን፣ በህይወት ፈተና ንፋስ ቶሎ ይወድቃል። ​ጥልቅ ማንነት ያለው ሰው ለመሆን፣ 📖 በንባብ ጠንካራ ስር እንትከል! እኛ አማኞች ደግሞ ምርጫ ውስጥ የማናስገባው ፣ ብርሃን የሆነልን ፣ ክርሰቶስን ያገኘንበት ከሁሉ የሚበልጥ መጽሐፍ ፤ ህይወት ያለበት ብቸኛው መጽሐፍ 📖 #መጽሐፍ #ቅዱስ ብቻ ነው !  #መጽሐፍ  #ቅዱስ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ነው ! 📖2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:15-16📖 --- ¹⁵ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ #ኢየሱስን #በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን #ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። ¹⁶ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር #መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ #ለትምህርትና #ለተግሣጽ #ልብንም ለማቅናት #በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። ✍️ወንድም አሻግሬ ሰሞኑን የጠፋውት ለቅሶ ላይ ስለነበርኩ ነው 🙏