fa
Feedback
Heart of Christ

Heart of Christ

رفتن به کانال در Telegram

የሰማይ የምድር ጌታ ሆይ ለአብርሃም፣ለዳዊት፣ለዳንኤልና ለጳውሎስ ሰዎች ሁሉ ያውቁህ ዘንድ ራዕይን እንደሰጠሃቸው አሁን ላይ ያለነው እኛና ቤተክርስቲያን ራዕይን እንቀበል ዘንድ በልባችን ለህዝቦች ያለንን ቦታ እንደ ባህር አስፋልን። UPG10/40

نمایش بیشتر
410
مشترکین
+124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-530 روز

در حال بارگیری داده...

کانال‌های مشابه
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+1
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+9
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+37
در 3 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+392
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
13 ژوئیه0
12 ژوئیه+1
11 ژوئیه0
10 ژوئیه0
09 ژوئیه0
08 ژوئیه0
07 ژوئیه0
06 ژوئیه0
05 ژوئیه0
04 ژوئیه0
03 ژوئیه0
02 ژوئیه0
01 ژوئیه0
پست‌های کانال
ዘላለማዊ ሆይ ያንተ ሞኝነት ከእኛ ጥበብ ይበረታል ሰዎች አወቁ ጨረሱ ብባል የሞኝነትህን ያህል መች ይደረሳል ዝምታህ የብዙሃንን ድምጽ ይሸፍናል ነገሮችን ለመቀየር እዛ ቦታ መገኘትህ ብቻ ይበቃል ያወቀህ ያመነህ ይቅርና ለደቅቃ የተጠጋጋህ ለላ ይሆናል የነካሄው ይፈወሳል አንተን የነካህስ በጨርቅህ ይድናል አይንህ ሁሉን አስትቶ ያስከትላል ዝምታህ የበረታውን የጨከነውን ልብ ይቀይራል የፍትህ ብርሀን ምን አደርግልህ ዘንድ ትወዳለህ ያስብላል ዘላለም በአንተ ፍት ይሰንፋል ዘመናት በአንተ ፍት ይደክማል የአንተ ልክ የለህም አንተ ምጡቅ ነህ ዘላለምን ፈጥረህ በፈጠርከው ዘላለም ትኖራለህ ዘላለምም ልክ አይደለም አንተ ፈጥረሄዋልና አንተ መጽሐፍ ነግሮን ነብያት ተርከውልን ሐዋርያት አጫውተውን አባቶች አውግተው እስካሁን እንዳልተነካህ ነህ ትላንት ላይ ቀዳማዊ ዛሬ ላይ ኗር ነገ ላይ ዘላለማዊ ነህ የብርታትህ ልክ የትልቅነት ልክ አይደረስም በዝህ ሀሳብ ጨምርልኝ

2
ኢየሱስ በአንተ ቤት ስንት ያወጣል? ለይሁዳ ኢየሱስ ማለት ዕድል ነበር ለኪሱ መሙያ የሚሆን 30ዲናር(1,500 Br) በብር የሚመነዘር። ለማርያም ደግሞ በራሱ ላይ የሚፈስ ውድ ሽቶ ብቻውን 300ዲናር (15,000Br) የምያወጣ ነው (ማር 14:3)። ለዴማስ ኢየሱስ እስከ ተሰሎንቄ አሪፍ ኑሮ ድረስ ነበር። ዓለም ፈገግ ስትልለት ጌታውን ጥሎ ኮበለለ። ከአንዲት ቆንጆ ከተማ ጋር የምተካከል የሚቀየር ጌታው.. ለጳውሎስ ደግሞ ሞትም ቢሆን ሕይወትም ከእርሱ የማይለየው (ሮሜ 8:38) (በሰይፍ ተገሎ)ነፍሱን የሰጠው ወዳጁ ነው ሲሞን ክርስቶስን ያየው እንደ ቢዝነስ ነው። በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሸቅሎ ለመክበር ፈለገ። ለእርሱ ኢየሱስ ዝነኛ የሚያደርግ መሣሪያ ነበር ለጴጥሮስና ለጓደኞቹ ግን ኢየሱስ የሕልውና ጉዳይ ነበር። መረባቸውን (ኑሯቸውን) ጥለው የተከተሉት ጌታቸው ነው። ደግሞም ብዙዎች ኢየሱስን እንደ ታላቅ ሰው፣ እንደ ነብይ፣ እንደ አስተማሪ ያከብሩታል። ዳግም ለፍርድ እንደሚመጣም ያምናሉ። ይህ መልካም ቢሆንም ግን የነፍስ ጉዳይ አይደለም። ለአናሲሞስና ለሐዋርያት ግን ኢየሱስ ሰው የሆነ አምላክ ነው። ውድ ወዳጄ ሆይ ኢየሱስ በአንተ ቤት ባጣቆየኝ ነው ወይስ ባለቤት? • እንደ ይሁዳ በብር የምትቀይረው? • እንደ ዴማስ በምቾት የምትለውጠው? የዓለም ኑሮ ስታምር የምትተወው ነው ወይስ በሞትና በሕይወት መሃል የሙጥኝ የምትለው መዳኛህ? •እንደ ማርያም ውድ ነገርህን የምትሰብርለት? ለእኔ ደግሞ... ክርስቶስ እግዚአብሔር አባት ዓለምን ከራሱ ጋር ለማስታረቅ የዘረጋው የፍቅር ድልድይ ነው። ዳግም የተቋረጠውን ሰማያዊ ሕብረት ለመቀጠል፣አብ የላከው ፣ የተጠሉትን የወደደ፣ የጥሉን ግድግዳ ያፈረሰና በኛ ልክ ሰው ሆኖ የተገለጠ ታላቅ ምስጢር ነው። የጠፋሁ ዕለት ፈላግዬ፣ የቆሰልኩ ዕለት ፈውሴ የታረዘ ማንነቴን የሸፈነ የጽድቅ ልብሴ ነው። ለእኔ ሲል የታረደ፣ ለእኔ ሲል የሞተና ለእኔ ሲል የተነሳ የመስዋዕቱ በግ ነው። እናንተስ... ጋር ኢየሱስ?
285
3
ስንቴ ነው የደከሙት ክንዶቼ ከመውደቅ የተያዙት ባንተ በማያወላውል ክንድ? ስንቴስ ነው መኖር ያቃታት ነፍሴ የታመመው ልቤ በፍቅር የታከመው? ስንቱስ ይሆን አጥር፣ ከለላ ጋሻ የሆንክለት ህዝብ? ስንቴ አጽናናኸኝ የሕይወት ውሽንፍር ስመታኝ፣ የሐዘን ወጀብ የነፍሴን መርከብ በኃይል ሲያናውጥ፣ ሁሉም ነገር ሲመነምን፣ ስሜቶቼ በባዶነት ሲዋጡ ያሰብኩት ስቀር ትዕግስቴና ተስፋዬ ባለቁ ሰዓት ያንተ ደራሽነት፣ የጠፋውን ተስፋዬን መልሶ፣ የሞተውን ህልሜን ዳግም ቀስቅሶ፣ የቆመውን ጉዞዬን አስቀጥሏል። እያንዳንዱ ቀናቶቼ የመልካምነትህ ምስክሮች ናቸው። ያንተ የማይነጥፍ መልካምነት የማይቀንስ ፍቅርህ፣ የማያቋርጥ ቸርነትህ፣ በሕይወቴ ውጣ ውረዶች ሁሉ ውስጥ የዘላለም የመዳን መልሕቅ ሆነልኝ። የአንተን መልካምነት የሚተርክ ልሳን የአንተን ታማኝነት የሚመሰክር ብዕር፣ የአንተን ቸርነት የሚገልጽ ቃል አይገኝም። አንተ ከማንኛውም ውዳሴ በላይ ነህና በዚህ ሁሉ ውስጥ ያንተ እጅ ነበር። በአንተ ብቻ ነፍሴ እውነተኛ ሰላምን ታገኛለችና። 2 ቆሮንቶስ 1:3-4 "የጸጋ ሁሉ አባትና የመጽናናት ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ🥺🙌
218
4
ማቴዎስ 11 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁸ እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ²⁹ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳ
ማቴዎስ 11 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁸ እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ²⁹ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ³⁰ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።
299
5
ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳኖችን ሲገባ ኖሯል። እነዚያ ቃል ኪዳኖች በታማኝነቱ የተመሠረቱ ነበሩ። ከአብርሃም ጋር ከገባው ቃል ኪዳን አንስቶ እስከ አዲስ ኪዳን ድረስ፣ እግዚአብሔር የገባውን ቃል ሳይዘገይ ወይም ሳይረሳ ፈጽሟል። በመስቀል ላይ ኢየሱስ ክርስቶስን በመሰዋት ደግሞ ትልቁን የፍቅሩንና የታማኝነቱን ማረጋገጫ ሰጥቶናል። ይሄም ለእኛ ያለውን ጥልቅ ፍቅር እና ፈጽሞ ታማኝ እንደሆነ ያረጋግጥልናል። እግዚአብሔር ታማኝ ነው። "ጌታ ግን የታመነ ነው፤ እርሱም ያበረታችኋል ከክፉውም ይጠብቃችኋል።"2ኛ ተሰሎንቄ 3:3
271
6
እኛ ስለ ሁለተኛም መምጣት እናወራለን የዓለማችን ግማሹ ህዝብ ግን ስለ መጀመርያው መምጣት ሰምቶም አያውቅም!🥺🙌
421
7
በዘመናችን ያለው ክርስትና ለብዙዎቻችን ትርፍ ማጋበሻ፣ ኑሮ ማሻሻያ፣ የሚበልጥ ቁሳቁስ መሰብሰብያ፣ እንዲሁም የሥጋዊ ምኞቶቻችን መፈጸሚያ ብቻ የሆነ ይመስላል። የክርስቶስ ወንጌል ሕይወትን የሚቀይር፣ ነፍስን የሚታደግ፣ የዘላለም ሕይወትን የሚሰጥ ቅዱስ መልዕክት ከመሆን ይልቅ የቁሳዊ ብልጽግናንና ምቾትን የምናገኝበት መሳሪያ ተደርጎ ቀርቧል። ብዙዎች በወንጌል ለመኖር እንጂ ለወንጌል ለመኖር አይፈልጉም። በወንጌል መኖር ማለት ጥቅሞቹን ማጨድ፣ በረከቶቹን መቀበል፣ ከችግርና ከሥቃይ መዳን ማለት እንደሆነ ተወስዷል። ነገር ግን ለወንጌል መኖር ማለት የራስን ሕይወት ምኞትና ምቾት መስዋዕት ማድረግ ማለት ነው። ለወንጌል አገልግሎት ዋጋን መክፈል፣ ለክርስቶስ ስም ሲባል ሕይወትን አደጋ ላይ መጣል፣ የዓለማዊ ስኬትን ትቶ የመንፈሳዊውን መከተል – እነዚህ ሁሉ ከዘመናዊው አስተሳሰብ ጋር የሚጋጩ፣ እንደ ኋላቀርና ከመደበኛው አመለካከት የራቀ እንደሆነ መቆጠር ከተጀመረ ዉሎ አድሯል። የጥንቶቹ ቅዱሳንና ሰማዕታት የከፈሉትን ዋጋ፣ ዛሬ ብዙዎች ለመክፈል ፈቃደኞች አይደሉም፤ ይልቁንም ወንጌልን የራሳቸው የማሻሻያ መሳሪያ አድርገውታል። ኢየሱስ ሆይ፣ የዘመኑ የክርስትና ግንዛቤ ከወንጌሉ እውነተኛ ይዘት እየራቀ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ያ የቀራኒዮ ስቃይህ እለት እለት ትውስታዬ ይሁን። የያዝኩትን ሁሉ የምለቅበት፣ ከአንተ ውጭ ምንም ነገር የኔ የማይሆንበት፣ ሕይወቴ ሙሉ በሙሉ ለአንተ የምትሆንበት እውነት ይመጣ ዘንድ እለምንሃለሁ። ይህንን የራስ ወዳድነት ሰንሰለት የምቆርጥበት ብርታት ስጠኝ። በአንተ እጅግ ብርቱ እንድሆን። ጸጋህ ከመንፈሴ ጋር ይሁን🥺🙌
321
8
ለአንዲት በቅጠል ጫፍ ላይ ላለች የጤዛ ጠብታ፣ የውቅያኖስ ጥልቀትና የሞገዱ ግርማ እንደምን ሊታያት ይችላል? በዚያች ቅጽበታዊ በሆነች አካሏና በጠባብ ክበቧ፣ ጥልቁን ሰማይና አጥናፍ የሌለውን ባሕር በስሌቷ ልትለካው ትደፍር ይሆን? በፍጹም! ሰውም እንዲሁ ነው። አምላክ ሆይ እኔ ከምናምንቴ ያነስኩ በታላቅነትህ ፊት የጠፋሁ ምስኪን ነኝ። ያንተ ጥበብ ሞኝነት ቢባል እንኳ ከሰው ልጅ የጥበብ ጫፍ በላይ እጅግ የላቀ ነው። አንዲት የትቢያ ቅንጣት በሚዛን ላይ ብታርፍ የክብደት ታሪክ እንደማትለውጥ ሁሉ እኔም እልፍ ዘመን በግርማህ ፊት ተደፍቼ ውዳሴ ባበዛ ላንተ የምጨምርልህ ክብር የለም። ባዝንና ብከፋም ከአምላክነትህ የምቀንሰው ቅንጣት ፋይዳ የለም። አንተ በራስህ የከበርክ፣ በራስህ የጸናህ "አልፋና ኦሜጋ" ነህ። አንተ ከፍጥረት ተውሰህ የከበርክበት፣ ከእኛ ተቀብለህ የደመቅህበት የታሪክ ምዕራፍ የለህም። ሳታቅድ ግርምት ሳትፎርሽ ትክክል ነህ። አዋቅያን ትእዛዝህን የሚጠብቅ፣ በቀዳማዊነትህ እርጅና የማይሰለጥንብህ፣ በፊተኛነትህ ዘመን የማይቀድምህ የዘላለም ንጉሥ ነህ። በልጅህ ተምረንህ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተንህ ይኸው እስከ ዛሬ ምስጢር እንደ ሆንክብን አለን። አንተ እጅግ ረቂቅ እኛ ደግሞ እጅግ ውሱን ነን። በአንተ ላይ የሚያምፁ ራሳቸውን ከብርሃን ያገላሉ እንጂ አንተን አያቆሽሹህም። አንተን በጠባብ አእምሯቸውና በደረቅ ስሌታቸው ሊበይኑህ የሚሞክሩ የባሕርን አሸዋ በአንድ ጭልፋ ለመጨረስ እንደሚደክሙ ሞኞች ናቸው። አቤት ብክነት! አንተን በብዙ ቃል ሊያብራሩ የሚሞክሩ ደካማነታቸው ይገለጣል እንጂ መለኮትህን አይዘልቁትም። የሚገልጥህ ቋንቋ የሚመስልህ ምሳሌ የለህምና። "እነሆ፥ እግዚአብሔር ታላቅ ነው፥ እኛም አናውቀውም፤ የዘመኑም ቍጥር አይመረመርም።" (ኢዮብ 36:26)
384
9
ለአንዲት በቅጠል ጫፍ ላይ ላለች የጤዛ ጠብታ፣ የውቅያኖስ ጥልቀትና የሞገዱ ግርማ እንደምን ሊታያት ይችላል? በዚያች ቅጽበታዊ በሆነች አካሏና በጠባብ ክበቧ፣ ጥልቁን ሰማይና አጥናፍ የሌለውን ባሕር በስሌቷ ልትለካው ትደፍር ይሆን? በፍጹም! የለም፣ አይሆንም! ሰውም እንዲሁ ነው። አምላክ ሆይ እኔ ከምናምንቴ ያነስኩ በታላቅነትህ ፊት የጠፋሁ ምስኪን ነኝ። ያንተ ጥበብ ሞኝነት ቢባል እንኳ ከሰው ልጅ የጥበብ ጫፍ በላይ እጅግ የላቀ ነው። አንዲት የትቢያ ቅንጣት በሚዛን ላይ ብታርፍ የክብደት ታሪክ እንደማትለውጥ ሁሉ እኔም እልፍ ዘመን በግርማህ ፊት ተደፍቼ ውዳሴ ባበዛ ላንተ የምጨምርልህ ክብር የለም። ባዝንና ብከፋም ከአምላክነትህ የምቀንሰው ቅንጣት ፋይዳ የለም። አንተ በራስህ የከበርክ፣ በራስህ የጸናህ "አልፋና ኦሜጋ" ነህ። አንተ ከፍጥረት ተውሰህ የከበርክበት፣ ከእኛ ተቀብለህ የደመቅህበት የታሪክ ምዕራፍ የለህም። ሳታቅድ ግርምት ሳትፎርሽ ትክክል ነህ። አዋቅያን ትእዛዝህን የሚጠብቅ፣ በቀዳማዊነትህ እርጅና የማይሰለጥንብህ፣ በፊተኛነትህ ዘመን የማይቀድምህ የዘላለም ንጉሥ ነህ። በልጅህ ተምረንህ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተንልን ይኸው እስከ ዛሬ ምስጢርህ እንደ ተከደነብን አለን። አንተ እጅግ ረቂቅ እኛ ደግሞ እጅግ ውሱን ነን። በአንተ ላይ የሚያምፁ ራሳቸውን ከብርሃን ያገላሉ እንጂ አንተን አያቆሽሹህም። አንተን በጠባብ አእምሯቸውና በደረቅ ስሌታቸው ሊበይኑህ የሚሞክሩ የባሕርን አሸዋ በአንድ ጭልፋ ለመጨረስ እንደሚደክሙ ሞኞች ናቸው። አቤት ብክነት! አንተን በብዙ ቃል ሊያብራሩ የሚሞክሩ ደካማነታቸው ይገለጣል እንጂ መለኮትህን አይዘልቁትም። የሚገልጥህ ቋንቋ የሚመስልህ ምሳሌ የለህምና። "እነሆ፥ እግዚአብሔር ታላቅ ነው፥ እኛም አናውቀውም፤ የዘመኑም ቍጥር አይመረመርም።" (ኢዮብ 36:26)
1
10
አንተ የቆሰለውን ነፍስ በምሕረትህ ቅባት የምታክም፣ የተሰበረውንም ልብ በፍቅርህ ጠጋኝ የሆንክ ሐኪም ነህ። ዓለም በኃጢአትና በነውር ገፍታ ያራቆተቻቸውን አንተ በጽድቅህ ልብስ አልብሰህ በማዕድህ ላይ ያስቀመጥካቸው የቸርነት ምስክሮች ዕልፍ ናቸው። የሰው ፊት በሚጠቁርበት የሰው ደጅ በሚዘጋበት በዚያ በጭንቅ ሰዓት አንተ ግን የማያልቅ ይቅርታህን አበዛህላቸው። የሕይወት ዐውሎ ነፋስ ቤቴን ሲመታው ማዕበሉና ሞገዱ በዙሪያዬ ሲያደባ፣ አንተ ግን የሰላም ድምፅህን የምታሰማ የዝምታ ግዜ መጽናናት ነህ። አንተ ኃያል ነህ ነገር ግን ኃያልነትህ ደካሞችን ለመጨፍለቅ ሳይሆን የዛለውን ለማበርታትና የወደቀውን ለማንሳት የሚገለጥ የፍቅር ኃይል ነው። አባ ቸር ሆይ🥺 አንተ ባዶነቴን የምትሞላ ጥምነቴን የምታረካ፣ የጨለመውን መንገዴን የምታበራ የማይጠፋ ፋኖሴ ነህ። በትግልና በጦርነት በደከመችው ዓለም ውስጥ ያንተ ሰላም ብቻ ነው እውነተኛ እረፍት የሚሰጠው። የልቤ አምላክ ሆይ በአንተ መከለል ምንኛ መታደል ነው! ፍቅርህ ከቃላት በላይ ነው ቸርነትህም ከምድር በላይ ሰፊ ነው። ሕይወቴ በአንተ ተውባለች ነፍሴም አንተን ሰምታ በአንተ ጸንታለች። "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል።" (ምሳሌ 1፡33)🥺🙌
340
11
ሚስዮናዊ ህይወት ሚስዮናዊነት ዕድል ነው🥺🙌
281
12
ይህ ትውልድ ተማሪ መሆንን እንደ ውርደት፣ መሪ መሆንን ደግሞ እንደ ብቸኛ የክብር መንገድ ቆጥሮታል። በመሆኑም መምህራን በበዙበት መድረክ ላይ የሚማር ተማሪ ታጣ። ሁሉም ሰው የራሱ እውነት አለው፤ ሁሉም ሰው ሌላውን ሊያርም እንጂ ሊታረም አይፈልግም። ጆሮዎች ተዘግተው ምላሶች የረዘሙበት ዘመን ሆነ። በትዕቢት የተሞላ ልብ ደግሞ አዲስ እውቀትን ለመቀበል ቦታ የለውም። ሁሉም አዋቂ በሆነበት ቦታ፣ እውነተኛ እውቀት የትም አትገኝም። ሁሉም አባት በሆነበት ቤት ደግሞ ሥርዓትና በረከት የለም። የሚመክረው በዝቶ የሚሰማው በመጥፋቱ፣ ትውልዱ የገዛ ጩኸቱ አደንቁሮት በውድቀት አፋፍ ላይ ቆሟል። መሪ የሆነው ሁሉ መንገድ ጠፍቶታል፤ አባት የሆነውም ሁሉ ተተኪ አጥቷል። ልጅነትን ሳይጨርሱ ወደ አባትነት መዝለል፣ መሠረት ሳይኖረው ሰማይ ጠቀስ ፎቅ የመሥራት ያህል ከንቱ ልፋት ነው። ነገር ግን በዚህ ሁሉ ጫጫታና ትርምስ መካከል ልጅ መሆን በትሕትና ተማሪ ሆኖ ለሚቀመጥ ሰው ብቻ ነው። ከአባቶች ድምፅ ይልቅ የገዛ ድምፃቸውን ላደነቆራቸው ለዘመነው ለእኛ ትውልድ ከመማር ይልቅ ማስተማር ለሚቀድማቸው ትዕቢተኞች ውድቀት ቅርብ ነው። መስማት የሚችል ግን ከትውልዱ መናወጥና ከዘመኑ የሞራል ውድቀት ተጠብቆ በእርጋታና በሰላም ይኖራል። ልጅነት ይቀድማል ተማርነትም እንደዛው ከስብከት ይበልጣል ልጅነት🥺🙌
356
13
ይህን ትውልድ ይቅር ማለት መቻል አለብን። የጥላቻ ቃላት እና የጥፋት ተግባራት የፈፀሙትን ክፉ ሰዎች ብቻ ሳይሆን በልባቸው የከበረ እንቁ ተሸክመው ዝምታ የመረጡትን መልካም ሰዎችንም ጭምር። ስለዚህ ብዙ የተናገረም አዋቂ ዝም ያለም አላዋቂ አይሆኑም ማለት ነው።
239
14
ይህን ትውልድ ይቅር ማለት መቻል አለብን። የጥላቻ ቃላት እና የጥፋት ተግባራት የፈፀሙትን ክፉ ሰዎች ብቻ ሳይሆን በልባቸው የከበረ እንቁ ተሸክመው ዝምታ የመረጡትን መልካም ሰዎችንም ጭምር። ስለዚህ ብዙ የተናገረም አዋቂ ዝም ያለም አላዋቂ አይሆኑም ማለት ነው።
0
15
ፍቅር አካል ለበሰ በእኛም ውስጥ አደረ🥺🙌
0
16
ዛሬ ላይ ለሰው ብንሰጠው የምንለው ምን ይሆን? ውዱ ስጦታችንስ ምን ይሆን? ታላቋ የወንጌል አርበኛ ኤሚ ካርሚካኤል/Amy carmichael በአንድ ወቅት እንዲህ ስትል ተናግራለች። "ያለ ፍቅር መስጠ
ዛሬ ላይ ለሰው ብንሰጠው የምንለው ምን ይሆን? ውዱ ስጦታችንስ ምን ይሆን? ታላቋ የወንጌል አርበኛ ኤሚ ካርሚካኤል/Amy carmichael በአንድ ወቅት እንዲህ ስትል ተናግራለች። "ያለ ፍቅር መስጠት ይቻላል ያለ ስጦታ ግን ማፍቀር አይቻልም " የማፍቀር የመጨረሻ ጥጉ መስጠት ነው። በጣም የወደደ በጣም ይሰጣል።በጥቂቱ የወደደ በጥቂቱ ይሰጣል። የስጦታችንን ልክ የመውደዳችን ልክ ይወስነዋል። ለዛ ነው እግዚአብሔር በጣም ስለሚወደን በጣም ውድ የሆነውን ልጁን የሰጠን። “በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።”   — ኤፌሶን 1፥7 ዛሬ ላይ በጌታ ላልሆኑ ለምንወዳቸው ቤተሰቦቻችን፣ወዳጆቻችን፣ለስራ አጋሮቻችን፣ጎረቤቶቻችን ምን እየሰጠን ነው? ኢየሱስን የምንሰጣቸው ከሆነ በጣም እንደምንወዳቸው ማሳያ ነው።
286
17
የታማኝነትህ አሻራ ጉልህ ሆኖ ይታያል። የወጀቡን ብርታት አይተን ስንንገዳገድ፣ የነፍሳችን መርከብ ለመስጠም ሲያንዣብብ፣ የፊትህን ብርሃን አይተን ፀንተናል። በቀኝህ ብርቱ እጅና በኃያል ክንድህ ተደግፈንም ቆመናል፤ የወደቅን መስሎን ሳለ የፍቅርህ ክንድ ደግፎን ከመውደቅ አትርፎናል። ሻካራው የሕይወት ጎዳና ሁሉ እንዳያሻክረን፣ ርኅራኄህ እንደ ለስላሳ የምቾት ጉዝጓዛችን ሆነልን። የዘላለማዊ ደኅንነት ዓለታችን ሆነህ ከጉድጓድ አውጥተህ በዓለት ላይ አቁመኸናል። የአጣብቂኝ ሰፈሮቻችንን የጭንቀትና የፈተና ጊዜያችንን፣ ድንቅ የድል ቅኝት ጣቢያዎች አድርገህ ቀይረሃቸዋል። የጥፋት ኬላዎችን የሞትና የጥፋት አፋፍ የነበሩ ቦታዎችን የታዳጊነትህ ዘላለማዊ መዘክሪያና የታማኝነትህንም የማይጠፋ ትሩፋት ማብሰሪያ አድርገሃቸው አይተናል። ደግመን ደጋግመን በፅድቅህና በእውነትህ ታዛ ስር ተጠልለናል በረድኤትህ አውድማ፣ በሰላምህ መንደር ተጓደናል። በመልካምነትህም መናኸሪያ ባልጠፋውና በማያልቀው ቸርነትህም ማሰማርያ እነሆ ተዘልለን፣ በልበ ሙሉነት ተቀምጠናል ነፍሳችንም ዕረፍት አግኝታለች። የዓለም ውጣ ውረድ ሊያደክመን ቢሞክርም አንተ ያለኸን የፍጻሜያችን ደስታ በመሆናችን ወደፊት እንገፋለን። ብርቱ መታመኛችን ሆይ! የዘላለም የኃይላችን ምንጭ! የነፍሳችን ወዳጅ! ስምህ ከፍ ከፍ ይበል🥺🙌
293
18
ዋጋህን እወቅ! አንድ አባት ከሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ልጁን እንዲህ ሲል ተናገረው "ይህ የእጅ ሰዓት አባቴ የሰጠኝ ነው፤ 200 ዓመታት ሆኖታል። ነገር ግን ላንተ ከመስጠቴ በፊት ሂድ እና ሰዓት ቤቶች ስንት ሊገዙህ እንደሚችሉ ጠይቀህ ና።" አለው። ልጁም ጠይቆ መጣ እና "አሮጌ ስለሆነ 5 ብር እንገዛሃለን" እንዳሉት ነገረው። አባቱም ድጋሚ ሸቀጣሸቀጥ መሸጫ ሱቆች ጋር ሄዶ እንዲጠይቅ ይነግረዋል።ልጁም ጠይቆ ይመጣ እና አሁንም ከ5 ብር በላይ እንደማይገዙት ይነግረዋል።"ሙዚየም ሄደህ ጠይቅ" ይለዋል አባቱ። ልጁም ጠይቆ ከመጣ በኋላ "አንድ ሚሊዮን ብር እንደሚገዙኝ ነገሩኝ" አለ። አባቱም "እንድታውቅ የፈለኩት የአንተንም ትክክለኛ ዋጋ (ቦታ) የሚሰጥህ ትክክለኛ ቦታ ላይ እንድትገኝ እንጂ የተሳሳተ ቦታ ላይ ሄደህ ሳይሳካልህ ሲቀር እንዳትናደድ ነው።ምንጊዜም ያንተን ዋጋ የሚያውቁ ብቻ ናቸው ክብርም አድናቆትም የሚሰጡህ ስለዚህ የተሳሳተ ቦታ ላይ አትገኝ!!ውድ እቃ ያለ ቦታው ርካሽ ነው:: “ከዚህ ነገር በኋላም የእግዚአብሔር ቃል በራእይ ወደ አብራም መጣ፥ እንዲህ ሲል፦ አብራም ሆይ፥ አትፍራ እኔ ለአንተ ጋሻህ ነኝ፤ ዋጋህም እጅግ ታላቅ ነው።” — ዘፍጥረት 15፥1
0
19
ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ። — 1ኛ ቆሮንቶስ 15:58
ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ። — 1ኛ ቆሮንቶስ 15:58
316
20
“አቤቱ፥ ለልቤ እንደ መከራዋ ብዛት ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።” — መዝሙር 94፥19🥺🙌
333