fa
Feedback
የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች

የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች

رفتن به کانال در Telegram

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ሥርዓት እና ደንብን የጠበቁ ዝማኔዎች እና መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው

نمایش بیشتر
4 678
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-147 روز
-3930 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+19
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+89
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+72
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+69
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+77
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+57
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+47
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+66
در 1 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+51
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+89
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+83
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+76
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+116
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+147
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+148
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+204
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+251
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+162
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+165
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+148
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+131
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+181
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+272
در 7 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+421
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+524
در 5 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+298
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+228
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+251
در 8 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+154
در 9 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+86
در 7 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+44
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+161
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+185
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+149
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+156
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+227
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+258
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+235
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+186
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+179
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+190
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+173
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+229
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+202
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+182
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+173
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+301
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+391
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+71
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+83
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+507
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
08 ژوئیه+1
07 ژوئیه+5
06 ژوئیه+3
05 ژوئیه+1
04 ژوئیه+1
03 ژوئیه+3
02 ژوئیه+2
01 ژوئیه+3
پست‌های کانال
Repost from N/a
#የየኔታ_አንለይ_እግዜሩ_የቀብር_ሥነሥርዓት ታላቁ የቤተ-ክርስቲያን ሊቅ የኔታ አንለይ እግዜሩ በድንገተኛ ሞት ዛሬ ሐመሌ 1/2018 ዓ/ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል😭 #የቀብር_ሥነሥርዓታቸው_ነገ
+5
#የየኔታ_አንለይ_እግዜሩ_የቀብር_ሥነሥርዓት ታላቁ የቤተ-ክርስቲያን ሊቅ የኔታ አንለይ እግዜሩ በድንገተኛ ሞት ዛሬ ሐመሌ 1/2018 ዓ/ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል😭 #የቀብር_ሥነሥርዓታቸው_ነገ_ሐምሌ_2_ከቅዳሴ_በኋላ ለ15 ዓመታት ባገለገሉበት በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ/ክ ይፈጸማል የኔታ አንለይ እግዜሩ በደብራችን በነበራቸው የ15 ዓመት ቆይታ ብዙ ደቀመዛሙርትን ያፈሩ የደብራች የመጽሐፍት ትርጓሜ መምህር ነበሩ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን ነፍስ ይማር 😭 ©MZDA

2
🍀ምን ብዬ ልጀምር? እጄ ይንቀጠቀጣል፣ ብዕሬ በዕንባዬ ብዛት ታጥቦ መጻፍ አቅቶታል። ልቤ እንደ ሰም ቀልጧል፣ የውስጤ ጉልበት ሁሉ ከድቶኛል። አምላኬ ሆይ! የሰማሁት እውነት ነውን? ለመሆኑ ዛሬ እኔ በሕይወት አለሁ ወይስ ከዚህ መሪር መርዶ ጋር አብሬ ሞቻለሁ? እንደ እኔ ያለ ምስኪን፣ እንደ እኔ ያለ ተቅበዝባዥና የየካቲት ቅጠል ማን አለ? እሪ! ብዬ ብጮኽ፣ ሰማይና ምድርን በልቅሶዬ ብከፍል፣ ደረቴን ተመትቼ አጥንቴ እስኪሰበር ድረስ ባዝን ይህንን ስብራት የሚጠግነው ማን ነው? ወገኖቼ! ዛሬ እኔን የሚረዳኝ፣ የልቤን ስብራት መሪር ሐዘን የሚያቃልልልኝ ማን አለ? 🍀ትናንት ማታ እኮ ነው! ገና ጥቂት ሰዓታት እኮ ናቸው የራቁት! ገና የፊታቸው ወዝ፣ የዓይኖቻቸው ብርሃን፣ ያ መልአካዊና ገነትን የሚያሳየው ሳቃቸው ከዓይኔ ሳይጠፋ፣ ዛሬ ጠዋት “መምህር አንለይ አርፈዋል” የሚል መርዶ መስማት ሬሳን በቁም መቅበር አይደለምን? ትናንት ማታ እኮ ነው “ነገ እመጣለሁ” ያሉኝ። መምህር ሆይ! የትኛውን ነገ ነው የነገሩኝ? እኔ ምስኪኑ፣ የምድር ዕውሩ፣ ፀሐይ የምትወጣበትን ምድራዊ ነገ ስጠብቅ፣ እርስዎ ግን የማያልፈውን፣ ፀሐይ የማይጠልቅባትን የሰማያዊቷን ኢየሩሳሌምን ነገ ነበረ ለካ የነገሩኝ! 🍀“ምነው ጠፋህ? አትጥፋ!” ሲሉኝ፣ ለካስ “ልጄ ሆይ፥ እኔ ልሄድ ነውና አንተ ግን በቤተ ክርስቲያን ቅጽር አትጥፋ፣ አደራህን ጠብቅ” የሚሉኝ የመጨረሻ የስንብት ቃላቸው ነበረች። “ስልክህን ስጠኝ ወንጌል ላንበብበት” ብለው ስልኬን ሲቀበሉኝ፣ ለካስ በዚያች መሣሪያ ላይ የመጨረሻውን የሕይወት ቃል፣ የወንጌሉን ዘላለማዊ አሻራና መዓዛ አትመው ሊሰናበቱኝ ነበረ። እኔ አላወቅኩም! እኔ የማልረባ፣ እኔ የምድር ዕውር፣ የነገውን የማላውቅ ምስኪን አፈር መሆኔን አላሰብኩም። ማታ ወንጌልን ፈትፍተው አብልተውኝ፣ ጠዋት ግን የሞታቸውን መርዶ የሰማሁ እኔ እንዴት ልተንፈስ? እንዴት ልጽናና? ይህንን የሐሞት ጽዋ እንዴት አድርጌ ልጠጣው? 🍀መምህር አንለይ ማለት እኮ ለእኔ ከልጅነቴ ጀምሮ የማውቃቸው፣ የሕይወቴ መሠረት፣ የነፍሴ ጠባቂ፣ የእግሬ መሪ ነበሩ። እኔን በተክለ ሃይማኖት ደጅ ተክለው፣ በቅዱሱ ጻድቅ ጥላ ሥር እንድኖር፣ ከመቅደሱ እንዳልለይ አጥብቀው የያዙኝ እርሳቸው ናቸው። ለብዙ ዓመታት እየመከሩ፣ የተሳሳትኩትን በሰው ፊት ሳይሆን በድብቅ እያስተካከሉ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ጥናት ምስጢር፣ የብሉያትና የሐዲሳትን ጥልቀት በአፌ ውስጥ ያጎረሱኝ እርሳቸው ነበሩ። 🍀አርአያነታቸው እኮ ምድራዊ አልነበረም። ጥሩ ስሠራ እንዳልታበይ፣ በሰው ምስጋና ወደ ውድቀት እንዳልሄድ “ልጄ ሆይ፥ ውዳሴ ከንቱን ሽሽ፤ ሰይጣን በትዕቢት ነው የወደቀው” እያሉ በትሕትና የሚገስጹኝ፤ መጥፎ ነገር ስሠራና ስሳሳት ደግሞ ሰው ሳይሰማ፣ ክብሬ ሳይነካ፣ በድብቅ (በስውር) ጠርተውና ደውለው በብልሃትና በፍቅር የሚመክሩኝ ብቸኛ አባት ነበሩ። ዛሬ ግን ስልካቸው አይሠራም! ዛሬ ግን ያ ድምፅ ጠፋ! ዛሬ ግን መምህር አንለይ ዝም አሉ። ትናንት ማታ ስለ ቴዎፍሎስ ምስጢር፣ ስለ ልደትዬ ክብር፣ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ቅንዓትና ገዳማዊ ሕይወት እያነሱ በምስጢር ያጫወቱኝ ሊቅ፣ ዛሬ እንዴት ብለው በአንድ ጀምበር አፈር ውስጥ ይተኛሉ? ይህንን መራራ ዕረፍት ልቤ እንዴት አድርጎ ይመነው? 🍀ወዮ! ዋይ! ዘንድሮስ ፍልሰታ ስትመጣ ማንን እንሰማለን? የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ፍቅር በልባቸው ያሳደጉ፣ ስሟ ሲነሳ ዓይናቸው በዕንባ የሚሞላ ታላቅ አባት ነበሩ። የእመቤታችን የፍልሰታ ጾም በመጣና በደረሰ ቁጥር፣ ሰውነታቸውን በብርቱ ሕመም ይያዝ ነበር። ነገር ግን ያንን መሪር ሕመማቸውን ችለው፣ ሥጋቸውን ቀጥቅጠውና አድክመው፣ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በፍቅር ይተረጉሙልን ነበር። ያንን ጣፋጭ ትርጓሜ ስንሰማ ሕመማቸውን የምናውቅ እኛ እናለቅስ ነበር፤ እርሳቸው ግን በፍቅር ይነዱ ስለነበር ሕመሙ አይታያቸውም ነበር። 🍀ምነው መምህር? ምነው አባቴ? ዘንድሮስ የፍልሰታዋን ውዳሴ ሳይተረጉሙልን?፣ የፍልሰታዋን ቅዳሴ አንድምታ ሳይፈቱልን፣ ያንን ጣፋጭ የትርጓሜ ማር ሳይመግቡን፣ የሰማይና የምድርን መገናኛ ምስጢር ሳይገልጡልን ጥለውን ሄዱ? የዘንድሮውን ፍልሰታ ያለ እርስዎ ድምፅ፣ ያለ እርስዎ ምስጢር፣ ያለ እርስዎ ቀናኢነት እንዴት እናሳልፈዋለን? የቤተ ክርስቲያን ቅጽር ያለ እርስዎ መኖር እንዴት ይበረታል? 🍀እውነት እላለሁ፥ መምህር አንለይ በዘመናችን የነበሩ የቅዱሳን ሁሉ ማጠቃለያ ነበሩ። ​እንደ ቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴ ማርያምን በፍቅር፣ በዕንባና በንጽሕና የሚተረጉሙ፤ ​እንደ አባ ሕርያቆስ ቅዳሴ ማርያምን፣ ያንን ምስጢረ ሥጋዌ የሞላበትን አንድምታ ገልጠው አንጀታችንን የሚያርሱ፤ እንደ አራቱ ወንጌላውያን የወንጌልን ቃል ፈትፍተውና አጣፍጠው ለሕፃን ለታላቁ የሚያቆርሱ፤ ​እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ስናጠፋ ፊት አይተው ሳይፈሩ፣ ለነፍሳችን ጥቅምና ድኅነት ሲሉ ቆመው የሚገስጹ ድንቅ አባት፣ ድንቅ መምህር ነበሩ። 🍀መምህር አንለይ ​እንደ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅኔን የሚያወርዱና ልብን የሚያረሰርስ የወርቅ ቃልን የሚናገሩ፤ ​እንደ አባታችን እንደ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በአንድ እግራቸው ቆመው፣ መስቀሉን ይዘው፣ ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን እየተረጎሙ ወንጌልን የሰበኩ ታላቅ የዘመናችን ሊቅ ነበሩ! ​ይህንን ሁሉ ክብር ይዘው ግን፣ ከውዳሴ ከንቱ ይሸሹ ነበር። ልታይ ልታይ አይሉም ነበር፤ በምድራዊ መድረክ ላይ ዝናን አይፈልጉም ነበር። ተደብቀው፣ በብቸኝነት፣ በሱባኤና በጾም የወንጌልን ቃል በተግባር የኖሩ የዘመኑ ድብቅ ኮከብ ነበሩ። 🍀መምህር ሆይ! እኔ እኮ ልጅነቴን በሚገባ ሳላሳይዎት፣ በምግባሬና በትምህርቴ ደስ ሳላሰኝዎት፣ በቅጡ እንኳን ሳላቅፍዎትና የመጨረሻውን በረከትዎን ሳይጠግብ በድንገት ተለዩኝ። ዛሬ ምድር ለእኔ ጨልማለች። በተክለ ሃይማኖት ደጅ ስመላለስ የእርስዎን ጥላ ማጣቴ፣ ያንን በትርጓሜ የሰለጠነ አንደበት ማጣቴ ልቤን በሰይፍ ይወጋዋል። ማንን አባት ልበል? ማንን ጠግኜ ልማር? የማንን በር ላንኳኳ? ስሳሳት ማን ጠርቶ ይመክረኛል? ስሰበር ማን ያጽናናኛል? የመጽሐፍትን ቃላት ማነን ጠይቄ እረዳለሁ? ወዮልኝ! መምህሬን አጣሁት! አባቴን አጣሁት! 🍀መምህር ሆይ፥ ነገር ግን እርስዎ ወደ ፈለጉትና ወደ ወደዱት፣ ሁልጊዜ ወደሚያስተምሩን ሰማያዊው ዓለም ሄደዋል። አሁን ከደከመውና ከታመመው ሥጋዎ አርፈው፥ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከአባታችን ከተክለ ሃይማኖት፣ ከቅዱስ ኤፍሬምና ከድንግል ማርያም ጋር ሆነው ሰማያዊውን ቅዳሴ እየቀደሱ ነው። በልቤ ውስጥ ሁልጊዜ ይኖራሉ። ለወንጌል እንድተጋ፣ ቃሉን እንድማር፣ በእምነት እንድበረታ ያደረጉኝ ውለታዎ እስከ መቃብር አይረሳም። አባቴ ሆይ! እርስዎ እዚያ ከቅዱሳን ማኅበር ሲደርሱ፣ እኔ እዚህ በምድር መከራና ፈተና የምማቅቀውን ልጅዎን አይርሱኝ። በእግዚአብሔር ፊት በጸሎትዎ ያስቡኝ። እርስዎ እስከምመጣ ድረስ፣ በዚያ በብርሃን ማደሪያ ሆነው በጸሎትዎ ይጠብቁኝ። 🙏​ጌታዬ ሆይ! መምህራችንን በቅዱሳኑ ማኅበር አሳርፍልን፤ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹ፣ ለባልደረቦቹና ለመላው የቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች መጽናናትን ይስጥልን!!! ✍️ ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! ✨ ሐምሌ 01, 2018 ዓ.ም ✨ ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ ✨ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን። http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224
117
3
🌹የትርጓሜው ፀሐይ ጠለቀች፣ የወንጌሉ አርበኛ ዝም አለ!!!🌹 ✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! 🍀በቤተ ክርስቲያን ሰማይ ሥር አንጸባራቂ ኮከቦች ይወጣሉ፤ አንዳንዶቹ ግን መውጣት ብቻ ሳይሆን ሌሊ
🌹የትርጓሜው ፀሐይ ጠለቀች፣ የወንጌሉ አርበኛ ዝም አለ!!!🌹 ✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! 🍀በቤተ ክርስቲያን ሰማይ ሥር አንጸባራቂ ኮከቦች ይወጣሉ፤ አንዳንዶቹ ግን መውጣት ብቻ ሳይሆን ሌሊቱን የቀኑ ያህል ያበሩታል። መምህር የኔታ አንለይ እግዜሩ በዘመናችን ለታየው ስብከተ ወንጌል እንደ ማለዳ ፀሐይ ብርሃን፣ እንደ ገነት ሽቶ መዓዛ የነበረ የታላቅነት መገለጫ ነው። ዛሬ ይህ ድምፅ ሲዘጋ፣ ይህ መዓዛ ካለንበት ምድር ወደ ሰማያዊው ቤት ሲሸጋገር፣ ቤተ ክርስቲያን የሥጋ ልጇን ብቻ ሳይሆን፣ የቃል ኪዳን ጠባቂዋን፣ የወንጌል አርበኛዋንና የታማኝ አገልጋይነት ተምሳሌቷን አጥታለች። "ጻድቅ ቢሞት ዕረፍት ነው" ይባላል፤ ነገር ግን እንዲህ ዓይነት ጻድቅ መምህር ሲያልፍ ለቀሪው ትውልድ ስብራቱ መሪር፣ ሐዘኑም ድንበር የለሽ ነው።
102
4
ታላቁ የቤተ-ክርስቲያን ሊቅ የኔታ አንለይ እግዜሩ ከዚ ዓለም ድካም አረፉ በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን በትጋት በቅንነት በታዛዥነት ብዙ ደቀመዛሙርትን በማፍራት ለቤተክርስቲያን
ታላቁ የቤተ-ክርስቲያን ሊቅ የኔታ አንለይ እግዜሩ ከዚ ዓለም ድካም አረፉ በደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን በትጋት በቅንነት በታዛዥነት ብዙ ደቀመዛሙርትን በማፍራት ለቤተክርስቲያን የማይተካ አገልግሎት የሰጡት የኔታ አንለይ፤ በተወለዱ በ66 ዓመታቸው ዛሬ ሐምሌ 1 ቀን ከንጋቱ 10:00 ሰአት በድንገት አርፈዋል ነፍስ ይማር!
130
5
🗯ወዳጄ ሆይ! ነፍስህ በሰው ምስጋና ስትወፈር፣ መንፈሳዊነቷ እየቀጠነ ይሄዳል፤ ልብህ ግን በሰው ንቀት ሲሰበር፣ በክርስቶስ ዘንድ የከበረ ዕንቁ ይሆናል። ​ስለዚህ መብራትህ በሰው ፊት እንዲበራ፣ መቅለጥህ ግን በስውር በእግዚአብሔር ፊት ብቻ እንዲሆን አድርግ። በምድር ላይ ስምህን ለማግነን የገነባኸው ግንብ ሁሉ ያፈርሰሃል፤ ለእግዚአብሔር ብለህ በዝምታ ያፈሰስከው እንባ ግን የዘላለም ቤትህ ሆኖ ይጠብቅሃል። ✍️ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224
143
6
ዛሬ በአዳማ ሚጊራ ቅዱስ ዮሐንስ ካቴድራል የሕዝብ ማዕበል አስደናቂ ነበር ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ፈጥነው ይመልከቱ https://vt.tiktok.com/ZSCvRuaA9/ https://vt.tiktok.com/ZSCvRuaA9/ https://vt.tiktok.com/ZSCvRuaA9/
201
7
🏺የልብ ዕድሳት፥ ከመቅደስ እስከ ማኅበራዊ ሚዲያ!!!🏺 👉2 ቀናት ብቻ ቀሩት! በ2ተኛው ቀን ይጀምራል! ✍️አዘጋጅና ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! ✨​ከሰኔ 30 እስከ ነሐሴ 30 ድረስ የሚቆይ፣
🏺የልብ ዕድሳት፥ ከመቅደስ እስከ ማኅበራዊ ሚዲያ!!!🏺 👉2 ቀናት ብቻ ቀሩት! በ2ተኛው ቀን ይጀምራል! ✍️አዘጋጅና ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! ✨​ከሰኔ 30 እስከ ነሐሴ 30 ድረስ የሚቆይ፣ በቴሌግራም በጽሑፍ ብቻ የሚለቀቅ፣ የእያንዳንዳችንን ሕይወት የሚቃኝ ታከታታይ ትምህርት። ➥ለወጣቶች፣ ➥ለአገልጋዮች፣ ➥ለምዕመናን፣ ➥ለዲያቆናት፣ ➥ለካህናት፣ ➥ለሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና ➥ለበገና መዘምራን፣ 👉የእያንዳንዱን ሰው ሕይወት የሚዳስስና ዘመኑን ያማከለ ተከታታይ ትምህርት ነው። "ዘመኑን ዋጁ" እንዲል። (ኤፌ፦፭፥፲፮) ​📅 ትምህርቱ መቼና የት ይሰጣል? ➥መቼት፦ ከሰኔ 30 እስከ ነሐሴ 30 ➥​ቦታ፦ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ! ➥​ዋጋው፦ ሙሉ በሙሉ በነፃ! (ያለ ዋጋ የተቀበላችሁትን ያለ ዋጋ ስጡ! 🤭) ​🔗የቻናሉን የቴሌግራም Link ለሌሎች ወንድም እኅቶቻችሁ Share በማድረግ Join ብለው እንዲማሩ አድርጉ።                 👇👇👇 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 ➥​"እውነተኛ ለውጥ የሚጀምረው ከልብ ዕድሳት ነው!" ✍️በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! ©🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ]¹²🕊
246
8
መጋቤ ሐዲስ መልአክ አማረ በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን ያስተማሩት ድንቅ ትምህርት ለመመልከት ከታች ያለው ሊንክ ይጫኑ https://youtu.be/7Iut6k7RID0?si
መጋቤ ሐዲስ መልአክ አማረ በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን ያስተማሩት ድንቅ ትምህርት ለመመልከት ከታች ያለው ሊንክ ይጫኑ https://youtu.be/7Iut6k7RID0?si=2s8afAXMlMWVnVYZ https://youtu.be/7Iut6k7RID0?si=2s8afAXMlMWVnVYZ https://youtu.be/7Iut6k7RID0?si=2s8afAXMlMWVnVYZ
214
9
🍀በተፈጥሮ ውስጥ ምስጦች የሚሠሩት ኩይሳ (የምስጥ ክምር) እና ንቦች የሚሠሩት ቀፎ የተለየ የአሰራር ምስጢር አላቸው። ምስጦች ዕውሮች ናቸው፤ የሚሠሩት ክምርም በውስጡ ጨለማና አየር የማይገባው ጠባብ ቦታ ነው። ንቦች ግን ብርሃንንና አበቦችን እያዩ፣ በማር የተሞላና በሥርዓት የተደራጀ ቀፎ ይሠራሉ። ሰብአዊነት የሌለው መሪ የሚሠራው መዋቅር ልክ እንደ ምስጥ ኩይሳ ነው፣ ከውጭ ትልቅ ተራራ ይመስላል፣ በውስጡ ግን ጨለማና መታፈን ያለበት ሥርዓት ነው። ‘ሰው’ የሆነ መሪ ግን የሚመራውን ማኅበረሰብ እንደ ንብ ቀፎ ያደርገዋል። የሁሉም ድምፅ የሚሰማበትና ፍሬው ማር (ሰላም) የሆነበት መድረክ ይፈጠራል። 🍀አንድ ታላቅ የሰንደቅ ዓላማ ጨርቅ በሰማይ ላይ ከፍ ብሎ ሲውለበለብ ክብሩ የሁሉንም ዐይን ይስባል። ነገር ግን ከበስተጀርባው ሆኖ የሚያወለበልበው የማይታየው ‘ነፋስ’ ነው። ነፋሱ በሌለበት ጨርቁ ግዑዝ አካል ብቻ ነው። አንድ የዕንቁላል ቅርፊትም ከውጭ ሲታይ ጠንካራ ቢሆንም፣ አዲስ ሕይወት አውጥቶ ፍሬያማ የሚሆነው ከውስጡ ያለው አስኳል በሙቀት በስሎ ቅርፊቱን ሰብሮ ሲወጣ ብቻ ነው። ‘መሪነት’ ያ የሰንደቅ ዓላማ ጨርቅ ወይም የዕንቁላል ቅርፊት (ሥልጣን) ሲሆን፣ ‘ሰው መሆን’ ግን ከጀርባ ሆኖ ያንን ሥልጣን ሕያው የሚያደርገውና ከውስጥ የሚፈልቀው የርኅራኄና የእውነት ነፋስ (አስኳል) ነው። የውስጥህ ሰብአዊነት ሳይሞላ ወንበር ላይ አትቀመጥ። 🍀ወዳጄ! 'ሰው ከመሆንህ በፊት መሪ አትሁን' የሚለው መንፈሳዊ አዋጅ፣ የሰውን ልጅ ልብ ከወንበር ፍቅርና ከሥልጣን ስካር ጠብቆ በእውነተኛ የአገልግሎት መስመር ላይ የሚያቆም የብርሃን መመሪያ ነው። ወንበር ዛሬ የአንተ ቢሆን ነገ የሌላ ነው፤ የሰዎች አድናቆትም እንደ ጠዋት ጤዛ በኖ ይጠፋል። ነገ በታሪክና በእግዚአብሔር ፊት የምንጠየቀው ‘ምን ያህል ባለሥልጣን ነበርክ?’ ተብለን ሳይሆን፣ ‘በሥልጣንህ ስንት ሰዎችን አገለገልህ? ፍትሕንስ እንዴት አቆምክ?’ ተብለን ነው (ማቴ፦ ፳፭፥፴፩-፵)። 🍀ወዳጆቼ! ​እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ለምድር አፈር ሳይሆን ለሰማያዊው መንግሥት ነው። ምድራዊ ዕድሜያችንና ሥልጣናችን ምንም ያህል ቢረዝም፣ ያለ እግዚአብሔር ፍርሃትና ያለ ሰብአዊነት ፍጻሜው መራራ ውድቀት ነው፤ በትሕትና የተከበበች የአመራር ሕይወት ግን ዘመኗ ጥቂት ቢሆንም እንኳን ወደማያልፈው የገነት ክብር ታስገባለች። ስለዚህ ልባችንን ከምድር ከንቱ ስስትና ከሥልጣን ስካር አውጥተን፣ መጀመሪያ ራስናችንን በትሕትና፣ በቅንነትና ለሰው በማዘን ቀርጸን እውነተኛ ሰው እናድርገው። ያኔ አመራራችንና አገልግሎታችን በምድር ላይ የብዙዎችን ሕይወት የሚያቀና፣ በሰማይም በማይናወጠው በክርስቶስ ፊት ዘላለማዊ የክብር አክሊል ሆና የምትበረከት ፍጹም የምሕረት ማኅተም ናትና። ወዳጄ አንተስ ለአንተ መልካም እረኛ ነህን? መልሱን ለአንተ ትቼዋለው። ይቆየን!!! ✍️ ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! ✨ ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ ✨ ሰኔ 28, 2018 ዓ.ም 🙏ኃይለ ሚካኤል እያላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ። http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 http://t.me/Be_Gosa1224 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
236
10
​📜ሰው ከመሆንህ በፊት መሪ አትሁን!!!📜 ✍️ጸሐፊ፦ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!! 🍀ሥልጣን ሰውን ሰው አያደርገውም፤ ይልቁኑ በውስጡ ያለውን እውነተኛ ማንነት አውጥቶ ያሳያል እንጂ። ‘ሰው ሳይሆኑ መሪ መሆን’ ማለት ሕዝብን እንደ መጋቢ ሳይሆን እንደ ጨቋኝ መግዛት ማለት ነው። እውነተኛ ‘ሰው’ መሆን ሳይቀድም ወደ አመራር ወንበር የሚወጣ ሰው፣ ሥልጣኑን ለራሱ ክብርና ጥቅማጥቅም ማግኛ ያደርገዋል። ‘ሰው መሆን’ (ፍትሕን፣ ፍቅርንና እውነትን መያዝ) ሲቀድም ግን፣ አመራሩ በሰዎች ላይ የመሠልጠኛ ሳይሆን ሰዎችን የማገልገያ ታላቅ መድረክ ይሆናል። 🍀የግብፁ ፈርዖንና የባቢሎኑ ንጉሥ ነቡከደነፆር ታላላቅ የምድር መሪዎች ነበሩ። ነገር ግን በሥልጣን ብዛት በትዕቢት ተወጠሩ፤ ራሳቸውን እንደ አምላክ በመቁጠር ‘ሰብአዊነታቸውን’ (ሰው መሆናቸውን) ዘነጉ። ነቡከደነፆር ሰው መሆኑን በረሳ ጊዜ እግዚአብሔር አእምሮውን ወስዶ ልክ እንደ አራዊት ሳር እንዲበላ አደረገው (ዳን፦፬፥፴፫)። ይህ የሚያሳየው ሥልጣንና ዙፋን ብቻውን ለሰው ክብር እንደማይሰጠው ነው፤ ‘ሰው ከመሆንህ በፊት መሪ አትሁን’ የሚለው አዋጅ፣ መሪው በሥልጣን ሰክሮ ወደ አራዊትነት ባህሪ እንዳይለወጥ የሚያስጠነቅቅ የብርሃን አጥር ነው። 🍀ወጣቱ ንጉሥ ሰሎሞን በአባቱ በዳዊት ዙፋን ላይ በነገሠ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ‘ምን ልስጥህ?’ ብሎ ጠየቀው። ሰሎሞን የጠየቀው የጠላቶቹን ጥፋት ወይም ረጅም ዕድሜንና ባለጸግነትን አልነበረም፤ ይልቁኑ ‘ሕዝብህን በትክክል እመራ ዘንድ የሚሰማ ልብ (ጥበብንና ሰብአዊነትን) ስጠኝ’ አለ (፩ነገ፦፫፥፱)። ሰሎሞን ከመሪነቱ በፊት ‘ሰው’ መሆንን መረጠ። እግዚአብሔር የሚፈልገው በትርና ዘውድ የያዘ ጨካኝ መሪ ሳይሆን፣ የሰዎችን ሕማምና እንባ የሚረዳ፣ የሚራራ ልብ ያለውን ‘ሰው’ ነው። 🍀አባታችን ኖኅ ታላቁን የጥፋት ውኃ መርከብ እየመራ በማዕበል ላይ በተጓዘ ጊዜ በመርከቡ ውስጥ የነበሩትን እንስሳትና አራዊት በሙሉ በሰላም ማስተዳደር ችሎ ነበር። ኖኅ አራዊቱን መግራት የቻለው በትር ይዞ በመደብደብ ሳይሆን፣ ራሱ በእግዚአብሔር ፊት የዋህ፣ ጻድቅና ፍጹም ‘ሰው’ ስለነበረ ነው።(ዘፍ፦፮፥፱)። ‘ሰው ሳይሆኑ መሪ መሆን’ ማዕበል በሚበዛበት የሕይወት ባህር ላይ መርከብን እንደ መንዳት ነው። መሪው ራሱ በውስጡ ካልረጋ፣ ቁጣውንና ስስቱን ካልገራ፣ የሚመራውን ማኅበረሰብ ወደ ጥፋት ውኃ ይወስደዋል። አመራር መጀመሪያ ራስን መግራት (ሰው መሆን)፣ ከዚያም ሌላውን ወደ ሰላም ወደብ መምራት ነው። 🍀ነቢዩ ሙሴ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለመምራት ወደ ምድረ በዳ ከመውጣቱ በፊት፣ ለ፵ ዓመታት ያህል በምድያም በረሃ የዮቶርን በጎች እየጠበቀ ትሕትናንና ትዕግሥትን ተምሯል።(ዘጸ፦፫፥፩)። እርሱ በፈርዖን ቤት የነበረውን የመሪነት ትዕቢት ጥሎ፣ በበግ እረኝነት ‘ሰው’ መሆንን ተለማመደ። ለዚህም ነው መጽሐፍ ቅዱስ ‘ሙሴ በምድር ላይ ካሉ ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበረ’ (ዘኍ፦፲፪፥፫) በማለት የመሰከረለት። እውነተኛ መሪ በትር የያዘ እረኛ ሳይሆን፣ ለበጎቹ የሚራራ ልብ ያለው ‘ሰው’ ነው። የፈርዖን መሪነት በጭቆና ላይ ስለተመሠረተ በባሕር ውስጥ ሰጠመ (ዘጸ፦፲፬፥፳፰)፤ የሙሴ መሪነት ግን በትሕትና (በሰውነት) ላይ ስለቆመ ባሕሩን ከፍሎ አሻገረ። 🍀ነቢዩ ኢያሱ ታላቁን የእስራኤል ሠራዊት መርቶ ኢያሪኮን ሊወር ሲቃረብ፣ በፊቱ የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ (መልአክ) ቆሞ ተመለከተ። ኢያሱም ቀርቦ ‘ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?’ ብሎ ጠየቀው። መልአኩ ግን ‘እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቻለሁ’ አለው (ኢያ፦ ፭፥፲፫-፲፬)። ይህ ታሪክ የሚያሳየው መሪው ምንም ያህል ሥልጣንና ሠራዊት ቢኖረውም፣ እርሱ ራሱ ከበላይ አምላክ በታች ያለ ‘ተመሪና ተራ ሰው’ መሆኑን ማወቅ እንዳለበት ነው። ‘ሰው ከመሆንህ በፊት መሪ አትሁን’ ማለት ከወንበርህ ፊት የቆመውን መንፈሳዊ ፍትሕና ሰብአዊነት አስተውል፤ አንተ የሥልጣን ባለቤት ሳትሆን ጊዜያዊ መጋቢ ብቻ ነህ ማለት ነው። 🍀ንጉሥ ሳኦል መጀመሪያ ሲቀባ በትሕትና የተሞላ ሰው ነበረ፤ ነገር ግን የንጉሥነቱ ወንበር ላይ ሲቀመጥ ‘ሰው’ መሆኑን ዘንግቶ በትዕቢት እግዚአብሔርን በመናቁ የንጉሥነት መጎናጸፊያው ተቀደደ፣ ሥልጣኑም ተገፈፈ (፩ሳሙ፦፲፭፥፳፯-፳፰)። በአንጻሩ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ጴጥሮስን የቤተ ክርስቲያን መሪ (እረኛ) አድርጎ ከመሾሙ በፊት የጠየቀው ጥያቄ ‘ትወደኛለህን?’ የሚል ነበረ (ዮሐ፦፳፩፥፲፭)። ሦስት ጊዜ ደጋግሞ ፍቅሩን ከመረመረው በኋላ ነው ‘በጎቼን አሰማራ’ ያለው። ይህ ታላቅ የአመራር ምስጢር ነው፤ ጌታችን ጴጥሮስን መሪ ያደረገው በጥንካሬው ሳይሆን፣ በልቡ ውስጥ ላለው መንፈሳዊ ‘ሰብአዊነትና ፍቅር’ ዋጋ ሰጥቶ ነው። መሪነት በቅባት (በሹመት) ብቻ ሳይሆን፣ ያንን ሹመት በትሕትና ተሸክሞ በሚኖር ‘ሰውነት’ ይጸናል። 🍀​አንድ ታላቅ መሐንዲስ (አርክቴክት) ለሰዎች የሚኖርበትን ታላቅ ሕንጻ ከመንደፉ በፊት፣ የዓይኑ ብርሃን ፍጹም ጤናማ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት። እርሱ ራሱ ማየት የማይችል ዕውር ከሆነ፣ የሠራው ሕንጻ ተደርምሶ በውስጡ ያሉትን ነዋሪዎች በሙሉ ይጨርሳቸዋል። ‘ሰው ሳይሆኑ መሪ መሆን’ ማለት ራስን በፍትሕ፣ በቅንነትና በፍቅር ሳያንጹ የሰዎችን ሕይወት ለመንደፍ (ለመምራት) መነሳት ማለት ነው። መሪው ራሱ በውስጡ በክፋትና በጥላቻ የታወረ ‘ዕውር’ ከሆነ፣ የሚመራውን ማኅበረሰብ በሙሉ ወደ ጥፋት ጉድጓድ ይከተዋል። መጀመሪያ የራስህን የልብ ዐይን በእውነትና በሰብአዊነት ብርሃን አብራው። 🍀በሰማይ ላይ የምናያቸው ከዋክብትና ጨረቃ ብርሃን የሚሰጡት ከፀሐይ ተቀብለው ነው። ነገር ግን ጨረቃ በራሷ ትዕቢት ‘እኔ ራሴ ብርሃን ነኝ’ ብላ በፀሐይና በምድር መካከል ብትቆም፣ የፀሐይ ግርዶሽ ይፈጠራል፤ ምድርም በጨለማ ትዋጣለች። መሪነትም እንዲሁ ነው፤ መሪው ሰብአዊነቱን ዘንግቶ ‘ከእኔ በላይ ማንም የለም’ ብሎ በትዕቢት ሲቆም፣ የፍትሕና የፍቅር ብርሃን በሕዝቡ ላይ እንዳይደርስ ይጋርደዋል። መሪ ማለት የራሱን ክብር የሚያሳይ ሳይሆን፣ ከበላይ ካለው ከአምላክ የተቀበለውን የእውነትና የርኅራኄ ብርሃን ለሕዝቡ የሚያስተላልፍ ንጹሕ መስተዋት (ሰው) መሆን አለበት። 🍀በጥንታውያን ነገሥታት ዘመን፣ ምርጥ የወይን ጠጅ ከቦታ ቦታ የሚያጓጉዙ አገልጋዮች ማሰሮዎቹ የታሸጉ በመሆናቸው፣ እራሳቸው በጥም እየተቃጠሉ የጠጁን ጣዕም ሳያውቁ ለባለቤቶቹ ያደርሳሉ። ‘ሰው ሳይሆኑ መሪ መሆን’ ልክ እንደነዚህ የወይን ጠጅ አጓጓዦች መሆን ነው። መሪው ስለ ፍትሕና ፍቅር ታላላቅ መመሪያዎችን በወረቀት ላይ ጭኖ ሊያጓጉዝ ይችላል፤ ነገር ግን እርሱ ራሱ በውስጥ ማንነቱ ‘ሰው’ ካልሆነ፣ የፍትሕን ጣዕም የማያውቅ ደረቅ መያዣ ብቻ ይሆናል። አንድ እረኛም በትር የሚይዘው በጎቹን ከተኩላ ሊጠብቅባቸው እንጂ ሊቀጠቅጥባቸው አይደለም (ሕዝ፦፴፬፥፬)። አመራር ሕግን ማጓጓዝ ብቻ ሳይሆን፣ መጀመሪያ በራስ ሕይወት ውስጥ ፍትሕንና ርኅራኄን ቀምሶ (ሰው ሆኖ) ማሳየት ነው።
222
11
ሰኔ 24 ጉባኤላይ በዘማሪ ገብረዮሐንስ የተዘመሩትን ተወዳጅ መዝሙሮች ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ 👇👇👇👇👇👇👇 https://vt.tiktok.com/ZSCbU1d21/ https://vt.tiktok.com/ZSCbU1d21/ https://vt.tiktok.com/ZSCbU1d21/
253
12
ዘማሪ ገብረዮሐንስ ገብረጻድቅ በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን የዘመረው ድንቅ ዝማሬ ከታች ያለውን የዩቱብሊንክ በመጫን ይመልከቱ https://youtu.be/fyfyg_vQSI
ዘማሪ ገብረዮሐንስ ገብረጻድቅ በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን የዘመረው ድንቅ ዝማሬ ከታች ያለውን የዩቱብሊንክ በመጫን ይመልከቱ https://youtu.be/fyfyg_vQSIw?si=1NMbyy6JImZLMakA https://youtu.be/fyfyg_vQSIw?si=1NMbyy6JImZLMakA https://youtu.be/fyfyg_vQSIw?si=1NMbyy6JImZLMakA ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
360
13
📢#የተወወደው_የሐሙስ_ጉባኤ በዛው እለት ሰኔ 25/2018 ዓ/ም በደመቀ ሁኔታ ተከናወነ የደብራችን ሳምንታዊ የሐሙስ ጉባኤ በደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በውዳሴ ማርያም ተጀምሮ በተወዳጁ+3
📢#የተወወደው_የሐሙስ_ጉባኤ በዛው እለት ሰኔ 25/2018 ዓ/ም በደመቀ ሁኔታ ተከናወነ የደብራችን ሳምንታዊ የሐሙስ ጉባኤ በደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በውዳሴ ማርያም ተጀምሮ በተወዳጁ ዘማሪ  #ዘማሪ_ሙሉቀን_ከበደ ነፍስን የሚመስጡ ጥኡም ዝማሬዎች ከህቡጋር ተዘምሮ #በመጋቤ_ሐዲስ_መልአክ_አማረ "እግዚአብሔርን ፈልጉት" በሚል ርዕስ ነፍስን የሚያሳርፍ ትምህርት ተሰቶ የምህላ ጸሎት በአባታችን #በመላከ_ምህረት_ቆሞስ_አባ_ፀሐይ_ስመኝ ተደርሶ ተወዳጁ የሐሙስ ጉባኤ ተጠናቋል ለተጨማሪ ምስልና ቪዲዮ የቲክቶክ ገጻችንን ይመልከቱ ©MZDA የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/ የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇 https://t.me/mediazdebreamin
434
14
+9
بدون متن...
357
15
📢#የተክለዬ_ደጅ_በምስጋና_በእልልታ_ደመቀ ሰኔ 24/2018 ዓ/ም የጻድቁ አባታችን ወርሃዊ በዓል ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉባኤል በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ውዳሴ ማርያም በማድረ+2
📢#የተክለዬ_ደጅ_በምስጋና_በእልልታ_ደመቀ ሰኔ 24/2018 ዓ/ም የጻድቁ አባታችን ወርሃዊ በዓል ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉባኤል በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ውዳሴ ማርያም በማድረስ ተጀምሮ የእለቱ ተጋባዥ ዘማሪ በሆኑት #ዘማሪ_ገብረዮሃንስ_ገብረጻድቅ ልብን በሚመስጥ ጥኡም ዜማ ደንቅ ዝማሬዎችን ተዘምረው በእለቱ ተጋባዥ መምህር #መጋቤ_ሐዲስ_መምህር_አድነው  #ልባችሁ_አይታወክ #ዮሐ_14፥27 በሚል ርዕስ መንፈስን የሚያድስ ጥኡም የነፍስ ምግብ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረው በደብራችን አስተዳዳሪ በ #መልአከ_ምህረት_ቆሞስ_አባ_ፀሐይ_ስመኝ  ቃለምዕዳን ቡራኬ የምህላ ጸሎት ተደርሳ የዕለቱ ጉባኤ ተጠናቋል 👉ጉባኤው ነገም በደማቅ ሁኔታ ይቀጥላል! #ሚዲያ_ዘደብረ_አሚን https://t.me/mediazdebreamin https://t.me/mediazdebreamin https://t.me/mediazdebreamin
315
16
+9
بدون متن...
323
17
📢 የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወርሃዊ በዓል....... በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል በደብራችን አስተ+7
📢 የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወርሃዊ በዓል....... በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል በደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ፀሐይ ስመኝ መሪነት የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገድላቸው ተነቦ በመጋቤ ሃይማኖት መ/ር ቢንያም የመንበረ ጵጵስና ወረዳ ቤተ-ክህነት ሒሳብሹም የእለቱ ትምህርት ተሰቶ ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያደረጉትን ገብረ ተአምራት ምስክረት ተሰቷ የጠዋቱ መርሃግብር በጸሎት ተፈጽሟል https://t.me/mediazdebreamin https://t.me/mediazdebreamin https://t.me/mediazdebreamin
338
18
📢በአዳማ ለምትገኙ ለጻድቁ ወዳጆች እና ለኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ! 👉ወደ እግዚአብሔር መንግስት የምታገባ የመንግስተ ሰማያት ወንጌል እነሆ ተባላችኋል። ሰኔ 24 በዕለተ ዕረቡ እና ሰኔ 25 በዕለ
📢በአዳማ ለምትገኙ ለጻድቁ ወዳጆች እና ለኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ! 👉ወደ እግዚአብሔር መንግስት የምታገባ የመንግስተ ሰማያት ወንጌል እነሆ ተባላችኋል። ሰኔ 24 በዕለተ ዕረቡ እና ሰኔ 25 በዕለተ ሐሙስ  በዳግማዊው ደብረ ሊባኖስ በአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን አውደ ምሕረት ወንጌል እንደ ወንዝ ዥረት ይፈሳል አንደበት ሁሉ ለምስጋና ይከፈታል። የጭንቃችን ደራሽ የሕይወታችን አምላጅ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ጧፍ እያበራን እናስባቸዋለን በብዙ በረከት በምልጃቸው እንባረከለን። 👉መቅረት አይደለም ማረፈድ ያስቆጫል። ዕረቡ እና ሐሙስ ከ10:-30 እስከ1:-30 መልእክቱን ሼር በማድረግ ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን እናድርስ ! አምላክ ለጉባኤው በሰላም ያደርሰን ዘንድ ሁላችን ስለ ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በማድረግ ለመንፈሳዊ እና ፈጣን መረጃ ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅዎም ያጋሩ የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/ የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇 https://t.me/mediazdebreamin
319
19
የቲክቶክ አካውንታችንን አቅም እንዲኖረው ሪፖስት ኮፒሊንክ በማድረግ ለሁሉም አዲደርስ አድርጉልን https://vt.tiktok.com/ZSCyXxj81/ ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በ
የቲክቶክ አካውንታችንን አቅም እንዲኖረው ሪፖስት ኮፒሊንክ በማድረግ ለሁሉም አዲደርስ አድርጉልን https://vt.tiktok.com/ZSCyXxj81/ ሁሉንም የሚዲያ አማራጮቻችንን ሰብስክራይብ ፎሎ በማድረግ ለመንፈሳዊ እና ፈጣን መረጃ ቤተሰብ ይሁኑ! ለወዳጅዎም ያጋሩ የዩቱብ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.youtube.com/@MediaZdebreAmin የቲክቶክ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.tiktok.com/@mediazdebreamin?_r=1&_t=ZS-97ZErsj8fMC የፌስቡክ ገጻችንን ለማግኘት👇 https://www.facebook.com/share/1CqPayGume/ የቴሌግራም ገጻችንን ለማግኘት👇 https://t.me/mediazdebreamin
306
20
በአስደናቂ ፍጥነት አየተገነባ ያለውን የአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕንጻ ቤተክርስቲያን የደረሰበትን ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ቪዲዮዎን ሪፖስት ሼር ኮፒሊንክ በማድረግ ለሁ+4
በአስደናቂ ፍጥነት አየተገነባ ያለውን የአዳማ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕንጻ ቤተክርስቲያን የደረሰበትን ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ቪዲዮዎን ሪፖስት ሼር ኮፒሊንክ በማድረግ ለሁሉም እንዲደርስ አቅም ስጡት! https://vt.tiktok.com/ZSCUHooqg/
352