የሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዝሙሮች
前往频道在 Telegram
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ሥርዓት እና ደንብን የጠበቁ ዝማኔዎች እና መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው
显示更多4 672
订阅者
+124 小时
+377 天
+4230 天
数据加载中...
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+39
在0个频道中
八月 '26
+113
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+74
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+89
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+72
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+73
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+69
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+77
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+33
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+57
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+47
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+66
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+42
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+51
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+89
在1个频道中
Get PRO
六月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+76
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+116
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+147
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+148
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+240
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+204
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+251
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+162
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+165
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+148
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+131
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+181
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+272
在7个频道中
Get PRO
四月 '24
+421
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+524
在5个频道中
Get PRO
二月 '24
+298
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+228
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+251
在8个频道中
Get PRO
十一月 '23
+154
在9个频道中
Get PRO
十月 '23
+86
在7个频道中
Get PRO
九月 '23
+44
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+161
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+185
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+149
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+156
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+227
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+240
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+258
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+235
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+186
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+179
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+190
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+173
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+229
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+202
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+182
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+173
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+301
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+391
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+39
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+14
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+71
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+83
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+507
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 06 九月 | +2 | |||
| 05 九月 | +3 | |||
| 04 九月 | +10 | |||
| 03 九月 | +11 | |||
| 02 九月 | +5 | |||
| 01 九月 | +8 |
频道帖子
Repost from 🕊¹²[ የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች ፔጅ ]¹²🕊
+ መድኃኒዓለም ታማኝ ወዳጅ ነው!!! +
✍️በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
ወዳጆቼ! በምንወዳቸውና በጥብቅ በምናምናቸው ሰዎች መከዳት ልብን አምርሮ ያደማል፤ አእምሮንም በቁስል ይሞላል። ብዙዎች በሕይወት ጉዟቸው በብዙ ታመኑ በሚባሉ ወዳጆቻቸው ይከዳሉ፣ ብቻቸውን ይቀራሉ። ነገር ግን ጌታችን መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በወዳጁ በይሁዳ በመሳም ተሸጦ፣ በደቀ መዛሙርቱ ተትቶ የመስቀልን መከራ የተቀበለ ታማኝ አምላክ ነው። ሰዎች ቃላቸውን አጥፈው ቢርቋችሁ፣ በእምነታችሁ ላይ ምራቅ ቢተፉ እንኳን፣ መድኃኒዓለም ከጎናችሁ አይልይም። እርሱ በጨለማችሁ ጊዜ የማይሸሽ፣ እምነታችሁን የማይሰብር፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር የሚኖር ብቸኛው ታማኝ ወዳጃችሁ ነው። የሰዎች ክደት ወደ እርሱ ያልተናወጠ ታማኝነት እንድትቀርቡ በር ይክፈትላችሁ።.........
ሙሉውን ለማንበብ.................
| 2 | https://youtu.be/Pwuob1_w4-0?si=UUYyipXOTa85W1ce | 142 |
| 3 | + እኔን መሸከም አይደክምህምን!? +
✍️በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
....ጌታዬ ሆይ! እኔ በቀንና በሌሊት በኃጢአት የምወድቅ፣ በየዕለቱ በበደሌ ቅዱስ አካልህን የማደማ፣ እንደ ይሁዳና ጴጥሮስ በምድራዊ ጥቅም አሳልፌ የምሸጥህ ከንቱ ፍጡር ነኝ! ነገር ግን አንተ የቸርነትህ ባህር የማይደርቅ፣ የትዕግሥትህ ድንበር የማይወሰን፣ ይቅር ባይነትህ በበደላችን ብዛት የማይደክም ፍጹም አባት ነህ!......... ሙሉን ለማንበብ ይጫኑ!
👇
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224 | 219 |
| 4 | 🔥#የጥንቃቄ_መልዕክት
ለሁሉም እንዲደርስ በደንብ ሼር አድርጉ
የእናታችንን የእመቤታችን የቅድስ ድንግል ማርያምን ስዕለ አድኅኖ የዳቦ መጠቅለያ አድረጉት😭
ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ሙሉ ቪዲዮውን ይመልከቱ
https://vt.tiktok.com/ZSqdLnQJj/
https://vt.tiktok.com/ZSqdLnQJj/
https://vt.tiktok.com/ZSqdLnQJj/ | 249 |
| 5 | ወዳጆቼ! አምላካችን እኛን የሚወድበት ፍቅር ከማንኛውም ምድራዊ ወላጅ ፍቅር እጅግ ይበልጣል። ኃጢአታችን ምንም ያህል ቢበዛ፣ የእርሱ የምሕረት ባሕር ከኃጢአታችን ታላቅነት በላይ ነው። የባሕር ውኃ አንዲትን የቆሻሻ ጠብታ አጥልቆ እንደሚያጠፋት ሁሉ፣ የእግዚአብሔርም ቸርነት በንስሐ የሚቀርበውን ሰው በደል ሙሉ በሙሉ ያጥባታል። በየትኛውም የኃጢአት ማዕበል ውስጥ ብንሆንም በፍቅር ወደ እርሱ እንምጣ፣ አምላካችን ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን አይጠላምና።
✍️ ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
ነሐሴ 27, 2018 ዓ.ም
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224 | 293 |
| 6 | https://youtu.be/TshkuZX4xIo?si=NBbpsFa5yBnsaYwf | 373 |
| 7 | + ሰላም ለእነዚያ መልካም ሰዎች +
✍️【በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!】
በስሜትና በሩጫ በተሞላው የሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ፣ አብዛኞቻችን በዙሪያችን የሚደረጉትን አነስተኛና ምስጢራዊ የፍቅር ምልክቶች ሳናስተውላቸው እናልፋለን። ዓለም በራስ ወዳድነት፣ በጥቅምና በውጫዊ ሽኩቻ በተወጠረችበት በዚህ ዘመን፣ ከምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታና የግል ጥቅም ባሻገር የሌሎችን ሕይወት በጸጥታ የሚያበሩ መልካም ሰዎች አሉ። እነዚህ ሰዎች የሰው ልጅ ሕሊናና የመንፈስ ልዕልና አልሞተም ለማለት በምድር ላይ የተተከሉ የሕይወት መብራቶች ናቸው። በሰው ልጅ ግንኙነት ውስጥ አብዛኛው ፍቅር "ብታደርግልኝ አደርግልሃለሁ" በሚል ስሌት ላይ የተመሠረተ ነው። መልካም ሰዎች ግን ፍቅራቸውንና ግንኙነታቸውን ከስሌት የጸዳ ያደርጉታል። እኛ በምናሳየው ባህሪ፣ ምላሽ ወይም አቀባበል ላይ ተመስርተው አይወዱንም። የፍቅራቸው ምንጭ በውጭ ያለው የእኛ ማንነት ሳይሆን፣ በውስጣቸው ያለው ጥልቅ የልብ ንጽሕና ነው። በዚህም ምክንያት እኛ ብንረሳቸውም፣ ብናስቀይማቸውም ወይም በሕይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ብንርቃቸውም፣ የፍቅራቸው ምንጭ አይደርቅም።
እነዚህ ሰዎች ፍቅራቸውን በጩኸት ወይም ለሰው ዕይታ አያስተውቁም። እኛ ልብ ሳንላቸው፣ በሕይወታችን ውስጥ ስላለው ችግርና ጭንቀት በስውር ያስባሉ፤ በጸሎታቸው ያሰቡናል፤ በውድቀታችን በምስጢር ይቆጫሉ። እኛ ስናዝን ያለ ምክንያት የከበደንን ሸክም ተካፍለው በልባቸው ይሸከሙታል። በዓለም ፊት አጨብጫቢ ሳይሆኑ፣ በጸጥታ የሕይወታችን ደጋፊዎችና የመንፈሳችን ጠባቂዎች ሆነው ይኖራሉ። በሰው ልጅ ተፈጥሮ ውስጥ የሌሎችን ስኬት ማየትና አብሮ መደሰት ታላቅ የመንፈስ ቅድስናን ይጠይቃል። ብዙ ሰዎች በሌሎች ውድቀት ሊያዝኑ ይችላሉ፤ በሌሎች ከፍታ ግን በቅናት ሊቃጠሉ ይችላሉ። መልካም ሰዎች ግን በእኛ ስኬትና ከፍታ ላይ እውነተኛ ፈገግታ ያሳያሉ፤ ደስታችን የራሳቸው ደስታ ያደርጉታል። በሕመማችንና በሐዘናችን ጊዜ ደግሞ ከእኛ በላይ አልቅሰውና ተክዘው የልብ እፎይታን ይሰጡናል።
በአስቸጋሪ የሕይወት አጋጣሚዎች፣ በንዴት ወይም በግል ጭንቀታችን ምክንያት ሰዎችን ልንገፋ፣ ፊታችንን ልናዞር ወይም ልንሸሻቸው እንችላለን። ተራ ሰዎች ሲገፉ ይርቃሉ፣ ሲጠሉ ይበቀላሉ። መልካም ሰዎች ግን በእኛ መገፋት ውስጥም ቢሆን የውስጣችንን ስቃይና ድካም ተረድተው አይሸሹም። ገፍተናቸው ያልገፉን፣ ርቀናቸው የፈለጉን እና በሩን ስንዘጋባቸው ከበሩ በስተጀርባ ሰላማችንን ሲጠብቁ የሚኖሩ ታላቅ የመንፈስ ጀግኖች ናቸው። እነዚህ ሰዎች "ለምን አስቀድሞ አልደወለልኝም?" ወይም "ለምን አስቀድሞ ሰላም አላለኝም?" የሚል አደገኛ የትዕቢት ስሌት የላቸውም። ክብራቸውን ከፍቅር በታች ያደርጋሉ። ረጅም ጊዜ ተራርቀን እንኳን ብንቆይ፣ ያለ ምንም ቅሬታና ኩራት አስቀድመው ይደውላሉ፤ ስለ ጤንነታችን፣ ስለ ሰላማችንና ስለ ሕይወታችን ይጠይቃሉ። የእነርሱ ጥያቄ ከጉጉት ወይም ከመረጃ ፍላጎት የመጣ ሳይሆን፣ ከእውነተኛ የልብ ሥጋትና አክብሮት የሚመነጭ ነው።
በምንወድቅበት፣ በምናፍርበትና በዓለም ፊት ዋጋ አጥተን በምንቆምበት ጊዜ አብዛኛው ሰው ይርቀናል። መልካም ሰዎች ግን በውድቀታችን ጊዜ ይበልጥ ይቀርቡናል። ውድቀታችንን አይተው እንዳላዩ ሆነው፣ የጠፋውን ስብእናችንንና ክብራችንን መልሰው እንድናገኝ በምስጢር ይደግፉናል። የእነርሱ መኖር እኛ የቱንም ያህል ብንሳሳትም አሁንም የተወደድንና ዋጋ ያለን ሰዎች መሆናችንን ያሳስበናል። ዓለም ሁልጊዜ በሁኔታዎች፣ በሀብትና በደረጃ ላይ ተመስርታ ሰዎችን ትመዝናለች። ዛሬ የተቀበለችውን ነገ ትጥላለች። መልካም ሰዎች ግን በተለዋዋጩ የዓለም ማዕበል ውስጥ የማይናወጡ የሕይወት መደገፊያዎች ናቸው። ሁኔታዎች ቢቀየሩ፣ ሀብት ቢጠፋ፣ ዝና ቢረግፍ፣ እነርሱ ግን ያው ናቸው። የማይቀያየርና የማይናወጥ ባህሪያቸው ለሕይወታችን ትልቅ የሥነ-ልቦናና የመንፈስ ደኅንነትን ይሰጠናል።
እግዚአብሔር ሰዎችን ለመንከባከብና ለማጽናናት ሁልጊዜ በዓይን የሚታዩ መላእክትን አይልክም፤ ይልቁንም የእግዚአብሔር ርኅራኄው መግለጫ የሚሆኑ እንደነዚህ ያሉ መልካም ሰዎችን በሕይወታችን መንገድ ላይ ይተክላል። የእነርሱ ደግነት፣ ይቅር ባይነትና ትዕግሥት ፈጣሪ እኛን ምን ያህል እንደሚወደንና እንደሚያስበን የምናይበት ሕያው መስተዋት ነው። እኛ በቸልተኝነት ወይም በስሜት የምናደርጋቸውን ስህተቶች፣ የምንናገራቸውን ከባባድ ቃላትና የምናሳየውን መቀዝቀዝ በሰፊ ልባችው ይሸፍኑታል። ስህተታችንን መዝግበው አይይዙም፤ በበደላችን አይፈርዱብንም። ይልቁንም ለስህተታችን እራሳቸው ምክንያት በመፈለግ፣ በልባቸው ውስጥ ይቅር ይሉናል። ይህ በደልን የማለፍና የመሸፈን አቅማቸው የልባቸውን ስፋትና ቅድስና ያሳያል።
ትልቁ አደጋና ቁስል የሚሆነው እነዚህ መልካም ሰዎች በሕይወታችን አጠገብ እያሉ ዋጋቸውን አለመረዳታችን ነው። በሞኝነታችንና በውጫዊ ሩጫችን ምክንያት እንደ ቀላል ነገር እንቆጥራቸዋለን። ነገር ግን የሰላም ይሁን ጥሪ የሚጀምረው ከራሳችን ንቃት ነው። እነዚህን ሰዎች ማወቅ፣ ማመስገን፣ በሕይወታቸው መባረክ እና እኛም ለሌሎች ሰዎች እንደዚህ ዓይነት መልካም ሰዎች ለመሆን መጋደል አለብን። ሰላም ለእነዚያ ስለ እኛ ድኅንነት ለሚጨነቁ ለሚያስቡ መልካም ሰዎች ይሁን።
✍️ በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
ነሐሴ 25, 2018 ዓ.ም
ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ
➜የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች የቴሌግራም ፔጅ ይቀላቀሉ!!!
👇👇👇👇👇
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224 | 376 |
| 8 | + ትሕትና ሞኝነት የሚመስላቸው አሉ!!! +
✍️ 【ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!】
ትሕትና የጥልቅ ስብእና፣ የውስጣዊ ጥንካሬ እና የመንፈሳዊ ብስለት መገለጫ እንጂ የከንቱነት ወይም የመፍራት ምልክት አይደለም። ነገር ግን የጮኸና የጎበጠው ባለበት፣ እውቀትና ጥበብ በታካኪነት በሚለኩበት ዓለም ውስጥ ትሑት ሆኖ መመላለስ አንዳንዴ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል። ሰዎች የትሕትናን ጥልቅ ምስጢር ስለማይረዱት፣ ዝምታህን እንደ አለማወቅ፣ ይቅር ባይነትህን እንደ ፍርሃት፣ እና መስዋዕትነትህን ደግሞ እንደ ተላላነት በመቁጠር ሊንቁህ ወይም ለመጠቀሚያነት ሊያውሉህ ይሞክራሉ። በትሕትናህ ምክንያት በሰዎች ዘንድ ልትገፋና ልትናቅ የምትችልባቸው ጊዜያት ብዙ ናቸው።
በትሕትና እና በሞኝነት መካከል ያለው ልዩነት ሰፊ ቢሆንም፣ አብዛኛው ሰው ግን ይህንን ድንበር መለየት ያቅተዋል። እውነተኛ ትሕትና ኃይልና እውቀት እያለህ እራስህን ዝቅ ማድረግና ሌሎችን ማክበር ሲሆን፤ ሞኝነት ግን ነገሮችን የመረዳትና የመወሰን አቅም ማጣት ነው። አእምሯቸው በጥበብ ያልበሰለ ሰዎች አንድ ትሑት ሰው ዝም ሲል፣ መብቱን ሳይጠይቅ ሲቀር ወይም ለሌሎች ቅድሚያ ሲሰጥ፣ ያንን የሚያደርገው አቅም አጥቶ ወይም ተታሎ ይመስላቸዋል። ይህ የተሳሳተ ምልከታ ትሑቱን ሰው እንደ ቀላልና ምንም እንደማያውቅ አድርገው እንዲቆጥሩት ያደርጋቸዋል።
በትዕቢትና በውጫዊ ጫጫታ በተሞላ ማኅበረሰብ ውስጥ ጨዋነትና ትሕትና ብዙ ጊዜ እንደ ድክመት ይቆጠራሉ። ሰዎች እራሱን የሚያወድስን፣ በሰው ላይ የሚጮኸውንና የበላይነቱን ለማሳየት የሚታገለውን ሰው እንደ "ጠንካራ" እና "በቁም ነገር ሊወሰድ የሚገባው" አድርገው ሲመለከቱ፤ እራሱን ዝቅ የሚያደርገውንና ሰላማዊውን ሰው ግን እንደ "ደካማ" ያዩታል። በዚህም ምክንያት በትሕትናህ ቦታ በሚገባህ አክብሮት ፈንታ ንቀት፣ መገለል እና ዝቅ ተደርጎ መታየት ሊገጥምህ ይችላል።
መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ፣ የሰዎችን ትሕትና አጋጣሚ አድርገው የሚጠቀሙ አጋጣሚ ጠባቂዎች አሉ። አንድ ሰው ትሑትና ይቅር ባይ መሆኑን ሲያውቁ፣ ያንን ትሕትና እንደ ድልድይ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎት ይፈጽሙበታል። የእሱን ጊዜ፣ ጉልበት፣ ገንዘብና ደግነት ያለ ምንም እፍረት ይበዘብዛሉ። ትሑቱ ሰው ላለመጋጨትና ሰላምን ላለማጣት ሲል የሚከፍለውን መስዋዕትነት፣ እነሱ እንደ ግዴታው ወይም እንደ መብታቸው አድርገው በመቁጠር አላስፈላጊ ሸክም ይጭኑበታል።
በሥራ ቦታም ሆነ በማኅበራዊ ግንኙነቶች ውስጥ፣ ትሑት የሆኑ ሰዎች ከጀርባ ሆነው ትልቁን ሥራ የሚሠሩት ቢሆኑም፣ እውቅናውና ክብሩ ግን እራሳቸውን በጮኸ ድምፅ የሚያስተዋውቁት ሰዎች ዘንድ ይሄዳል። ትሑቱ ሰው "ሥራዬ ይናገር" ብሎ በጸጥታ ሲሠራ፣ ሌሎች ግን የእሱን ድካም የራሳቸው አድርገው ያቀርቡታል። በዚህም ምክንያት ትሑት በመሆኑ ብቻ የሚገባውን የዕድገት ደረጃ፣ አክብሮትና ቦታ ሳያገኝ ይቀራል፤ ይባስ ብሎም እንደ ተራና ምትክ እንደሌለው ሰው ተቆጥሮ ወደ ጎን ይገፋል።
ትሕትና ማለት የራስን ክብር አልፎ ለሌሎች መስጠት ወይም ማንኛውንም የበደልና የንቀት አይነት በዝምታ መቀበል ማለት አይደለም። ድንበር የሌለው ትሕትና እራስን ወደ ማጥፋትና ለበደለኞች መንገድ ወደ መክፈት ይለወጣል። አንድ ሰው ትሑት ሲሆን ነገር ግን "አልቀበልም"፣ "ይህ መስመር አልፎብኛል" የሚል ግልጽ ድንበር ካላበጀ፣ ትሕትናው ለሌሎች ሰዎች መጠቀሚያነት በር ይከፍታል። እውነተኛ ትሕትና እራስን ከማክበርና መብትን በጥበብ ከማስጠበቅ ጋር አብሮ መሄድ አለበት።
በሰዎች ዘንድ ትሕትናቸው ዋጋ ያጣና መጠቀሚያ የሆኑ ሰዎች በውስጣቸው ትልቅ የሥነ-ልቡና ስቃይ ያስተናግዳሉ። "ሰዎችን ስላከበርኩና ስለወድድኩ ለምን ተጎዳሁ?" የሚል የምሬት ድምፅ በውስጣቸው ሊመላለስ ይችላል። ይህ ሁኔታ ደግሞ ቀስ በቀስ ትሑቱ ሰው በሰዎች ላይ እምነት እንዲያጣ፣ ወደ መራረር እንዲያደላ ወይም ደግሞ እራሱን እንዲጠራጠር ሊያደርገው ይችላል። እውነተኛው መንፈሳዊ ትግል የሚጀመረው ከዚህ በደል በኋላም ቢሆን ትሕትናንና የልብ ንጽሕናን አሳልፎ አለመስጠት ላይ ነው።
ትሑት የሆነን ሰው የሚበዘብዙና የሚንቁ ሰዎች፣ ጊዜያዊ ድል ያገኙ ይመስላቸዋል። ትሑቱ ሰው ስለ ተወላቸው ብቻ "አታለልኩት" ወይም "በላይነቴን አረጋገጥኩ" ብለው እራሳቸውን ያታልላሉ። ነገር ግን ትሑቱ ሰው ዝም ያለው ባላወቀ ወይም ስለተሸነፈ ሳይሆን፣ ለሰላሙና ለራሱ ሕሊና ሲል መሆኑን አይረዱም። ይህ የበደለኞች ጊዜያዊ የበላይነት ስሜት በውስጣቸው ታላቅ የሞራል ውድቀትንና ዕውርነትን ይፈጥርባቸዋል።
ሰዎች ትሕትናን እንደ ፍርሃት የሚያዩት፣ የትሕትናን እውነተኛ ምንጭ ስለማያውቁ ነው። እውነተኛ ትሕትና ማለት ኃይል፣ እውቀትና የመበቀል አቅም እያለህ ያንን ኃይል ለሰላምና ለበጎ ነገር ለመግራት ማድረግ የምታደርገው ጥበብ ነው። አንበሳ እራሱን ስለተቆጣጠረ ብቻ እንደ በግ አይቆጠርም። ትሑት ሰው የሚታገሠው ስለሚፈራ ሳይሆን፣ የመንፈስ ልዕልና ስላለው ነው። ይህንን እውነት የተረዱ ሰዎች ብቻ ናቸው የትሑቱን ሰው ዝምታና ትዕግሥት አክብረው የሚቀርቡት።
ትሕትናህ መጠቀሚያ እንዳይሆን ከተፈለገ፣ ከእባብ ብልሃትና ከርግብ የዋህነት ጋር መጣመር አለበት። ትሑት መሆን ማለት ዕውር መሆን ማለት አይደለም። የሰዎችን አካሄድ፣ ፍላጎትና ተንኮል በጥበብ ማስተዋል ያስፈልጋል። ትሑት ሆነህ ሳለህ፣ በደል ሲፈጸም ወይም መስመር ሲታለፍ በቆራጥነትና በሥልጣን "አይሆንም" ለማለት መቻል አለብህ። ትሕትናህ በጥበብና በቆራጥነት ሲታጀብ፣ ሰዎች እንደ አሻንጉሊት ሊጫወቱብህ አይችሉም።
ትዕቢተኞችና ሰዎችን የሚንቁ አጋጣሚ ጠባቂዎች ለአጭር ጊዜ ያሸነፉ ቢመስሉም፣ መጨረሻቸው ግን ውድቀትና የሕሊና ባዶነት ነው። ትሕትና ግን ምንም እንኳን በጊዜያዊነት ዋጋ ቢያስከፍልም፣ ዘላቂና የማይናወጥ ድልን ያጎናጽፋል። ትሑት ሰዎች በታሪክ፣ በሰዎች ልብ እና በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ለዘላለም የሚኖር ትልቅ ስምና አክብሮት ይተዋሉ። ትሕትናህ በሰው ዘንድ ቢናቅም፣ በእውነትና በሕሊና ፊት ግን ትልቁ የከበረ ዘውድ ነው።
✍️ በዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
ነሐሴ 24, 2018 ዓ.ም
ናዝሬት (አዳማ)፡ ኢትዮጵያ
➜የዲያቆን ጐሥዓ ቶላ ትምህርቶች የቴሌግራም ፔጅ ይቀላቀሉ!!!
👇👇👇👇👇
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224
http://t.me/Be_Gosa1224 | 327 |
| 9 | በሰማይ ከእመቤታችን ቀጥላ "በትረ ማርያም" የተባለች የጸጋ ዘውድ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ናት። ተጋድሎዋ የእግዚአብሔርን መንገድ፣ ምልጃዋ የእግዚአብሔርን ፍጹም ይቅርታ የሚያበስር ሕያው የሃይማኖት መስታወት ነው።
✍️ ዲያቆን ጐሥዓ ቶላ!!!
ነሐሴ 24, 2018 ዓ.ም
http://t.me/Be_Gosa1224 | 356 |
| 10 | https://youtu.be/Jx81WE12wyY?si=q3emFxHoQisyCWbv | 379 |
| 11 | ✝️ሰላም ለኪ እያለ✝️
ሰላም ለኪ እያለ /2/
ሐርና ወርቁን ስታስማማ
የገብርኤል ድምፅ ተሰማ
ተሰማ የመልአኩ ድምፅ ተሰማ
ተሰማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ
አዝ
ውሃ ስትቀጂ ክንፉን እያማታ
ሊያበስርሽ የመጣው በታላቅ ደስታ
ከሞገስሽ ብዛት /2/ ሲታጠቅ ሲፈታ
አቅርቦልሽ ነበር የክብር ሰላምታ
አዝ
የምሥራቹን ቃል ምስጢር ተሸክሞ
ገብርኤል ተላከ ሊያረጋጋት ደግሞ
እርጋታን ተሞልታ/2/ ነገሩን መርምራ
የመልአኩን ብሥራት ሰማችው በተራ
አዝ
ይደሰታል እንጂ መንፈሴ በአምላኬ
በምስጋና ሳድር ዘወትር ተንበርክኬ
ሃሳቤ ለቅፅበት/2/ሌላ መች ያስባል
ለእኔ ልጅን መውለድ እንዴት ይቻለኛል
አዝ
ከአንቺ የሚወለደው ልዑል ነው ክቡር
የተመሰገነ በሰማይ በምድር
ምስጢሩ ኃያል ነው /2/ ይረቃል ይሰፋል
ከአንቺ በቀር ይኼን ማን ይሸከመዋል
አዝ
እጹብ ነው ድንቅ ነው አንቺን የፈጠረ
አንቺን በመውደዱ ሰውን አከበረ
ዓለም ይባረካል /2/ በማሕፀንሽ ፍሬ
ክብርሽን አልዘልቅም ዘርዝሬ ዘርዝሬ
መዝሙር
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
| 454 |
| 12 | ፲፮.ውኃ አጠጭኝ አላት (ይልማ ኃይሉ).mp3 | 326 |
| 13 | ፈያታዊ ዘየማን
ፈያታዊ ዘየማን አምላኩን ለመነ
በቀኝ ያቆመው ዘንድ ጌታን ተማጸነ
ወንበዴ ብሆንም ሽፍታ ወንጀለኛ
መምጣትህን አሰብኩ ለድህነት ወደኛ
አልሰማሁም እኔ የነቢያትን ቃል
አላወቅኩም በእርግጥ አብሮኝ እስኪሰቀል
ኢሳይያስ ሲናገር ዳዊት ሲመሰክር
የመሲሁን መምጣት አልሰማሁም ነበር
# አዝ= = = = =
በመስቀል ላይ ሳለ አምላኬን ለየሁት
ትሁት ነበር ፍጹም በደል የሌለበት
ስለ በደላችን እኛ ተሰቅለናል
እሱ ግን በማን ላይ ወንጀልን ፈጽሟል
# አዝ= = = = =
ጨረቃ ደም ሆና ፀሐይዋ ስትጨልም
ከዋክብት ረግፈው ሰማይ ሲያጉረመርም
አምላክ መሰቀሉን ተፈጥሮ ነግራኝ ነው
በመንግሥትህ ጌታ አስበኝ የምለው
አዝ==========
አወይ ቀያፋ ሆይ አወይ ሀና ሆይ
ደስ ብሏችሁ ዋለ በጌታ ስቃይ
ተፈጥሮ ምስክር ሆኖ ሲያስተምራችሁ
እንዴት አላመነም ደንዳናው ልባችሁ
መዝሙር
ይልማ ኃይሉ
መዝሙር 04 | 352 |
| 14 | ♡ አረሳት ኢትዮጵያን ♡
አረሳት ኢትዮጲያን በእርፈ መስቀል
አባ ተክለሃይማኖት ሰባኪ ወንጌል
የእግዚአብሔር ሰው ነው ተወዳጅ በ ሰማይ
የተረማመደ በጽድቅ አደባባይ
ፈውስና ጸሎቱ ቃሉ የተሰማ
ወንጌል የሰበከ በገጠ ከተማ
የእቲሳው ኮከብ የደብረ አስቦቱ
ለወንጌል ተዋጋች ንጽህት ሕይወቱ
አዝ= = = = =
ፋናው እስከ ዛሬ ሲያበራ የኖረ
የእቲሳው አባት ፍስሐጽዮን
እግዚአርያ እናቱ ማህፀነ ብሩክ
ወለደች ኮከብን ሲኦልን የሚያውክ
አዝ= = = = =
ዲያቢሎስ እስካሁን ስሙ ሲጠራበት
ሲረገጥ ይኖራል በእሳት ሰንሰለት
አዲስ ሐዋርያ የኢትዮጵያ አባት
ደጋ ና ቆላውን በመስቀል ባረካት
አዝ= = = = =
ምንጩና ፏፏቴው ተራራው ቅዱስ ነው
የአባታችን መስቀል ጽኑ ስለነካው
የተራመደበት የዳሰሰው ሁሉ
ድውይ ይፈውሳል ሳርና ቅጠሉ
መዝሙር
ይልማ ኃይሉ | 247 |
| 15 | በርተሚዮስ_ነኝ.mp3 | 207 |
| 16 | የሀብከ ዮም
የሀብከ ዮም የሀብከ መድኃኔዓለም /2/
ዕድሜ ማቱሳላ ወአብርሃም /2/
ይስጣችሁ ዛሬ ይስጣችሁ መድኃኔዓለም /2/
ዕድሜ ማቱሳላ የአብርሃም /2/
በቅዱስ ጋብቻ ሙሽሮች የተወሰናችሁ /2/
ክርስቶስ ተገኝቷል በመካከላችሁ /2/
የድንጋዮቹን ጋን ወይኑን (2) ሊሞላበት /2/
ከድንግል ማርያም ጋር ተገኝቷል ከዚህ ቤት /2/
አዝ (ግእዝ) ---------------------
ደስታውን አይቶ አምላክ ፍፁም ተደስቷል /2/
ሊባርካችሁም እጆቹን ዘርግቷል /2/
በሕይወታችሁም ፍቅር (2) ቅመም ሆኖ /2/
ትህትናን ይስጣችሁ እግዚአብሔር በቶሎ /2/
አዝ (አማርኛ) -------------------
ሰርጋችሁ እንዲሆን ደስታ ፍቅር የተሞላበት /2/
በሕይወታችሁ ውስጥ ክርስቶስ ይግባበት
በሕይወታችሁ ውስጥ አምላክ ይኑርበት
አዝ (ግእዝ) -----------------
የበረከት ፍሬ በጸጋው እንዲያበዛላችሁ /2/
ዛሬ ተደሰቱ አምላክን ይዛችሁ /2/
ራስን በመግዛት እውቀት(2) ለመላችሁ
ዛሬ ተደሰቱ አምላክን ይዛችሁ /2/
ለሥጋ ወደሙ እግዚአብሔር ስለመረጣችሁ /2/
የመንፈስ ቅዱስ ሕፃናቶች ናችሁ /2/
አዝ (ግእዝ) ------------------
አዝ (አማርኛ) ----------------
መዝሙር በሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
መዝሙር፦15 | 264 |
| 17 | #መዘንጋት_ባለበት_የንስሐ_መዝሙር
መዘንጋት ባለበት በታናሽ ህሊና
መዘመር ልጀምር ለድንግል ምስጋና
እኔስ በውዳሴሽ ባህር እዋኛለው
ገናንነትሽን ክብርሽን እያሰብኩ
የትትናሽ ነገር ቢወሳ አያልቅም
ታነቢያለሽ እና ለዚ ክፉ አለም
ድንግል ሆይ ለሀጣን ታስቢያለሽ እና
ልቦናዬ ባንቺ በምልጃሽ ተፅናና
ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን
አንቺን ተማጽነናል እንድታማልጂን
ዘወትር እጆችሽ ተዘርግተዋል እና
ስለበደለኞች ሊያቀርቡ ልመና
እሳታውያኑ ሱራፌል ኪሩቤል
ሊነኩት ያልቻሉት የሳቱን ነበልባል
አንቺግን ታቀፍሽው ሳምሽው በከንፈርሽ
ከፍጥረት ለይቶ ፍፁም ስላጸናሽ
ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን
አንቺን ተማጽነናል እንድታማልጂን
ዘወትር እጆችሽ ተዘርግተዋል እና
ስለበደለኞች ሊያቀርቡ ልመና
ሊቀ-መዘምራን:- ይልማ ሀይሉ
| 193 |
| 18 | ቅያሜው ይቅርና አምላክ ሆይ ታረቀን
አንተ ስለራከን ሞት ነው የከበበን /2/
እስከመቼ ድረስ ህዝብህ ተጎሳቁሎ
በረከሰ መንፈስ ለእርኩሰት ተጥሎ
ምድር እያለቀሰች ደም እየሸተታት
እባክህ አምላኬ ኢትዮጵያን ታረቃት /ሀገሬን/
የዘመኑ ጣዖት ገንዘብ እያሳተን
ይህ ደካማ ስጋ አምላክን አስተወን
ግብዝነት ሞልቶት ፈራሹ አካል
በነፍስ በሽታ ህዝባችን ታሟል /2/
ክንፋችን ተመትቶ መብረር አቅቶናል
በመንፈስ በሽታ ህዝባችን ታውኳል
ራዕይ የሌለው ተራ ሰው ስለሆን
እባክህ ጌታችን በፍጥነት ታረቀን /2/
ጸጋህ የተለየን ባዶነት የሞላን
ፍቅር የተነፈግን ሰላም የጎደለን
ሆነን ስለቀረን እግዚአብሔር ታረቀን
ጽድቅህን አድለን ጽድቅ እንደተመኘን /2/
07 | 163 |
| 19 | ርእስ : ከንቱ ነኝ
ከንቱ ነኝ የከንቱ ከንቱ ነኝ
ዋስትና መከታ እግዚአብሔር ካልሆነኝ
ተስፋዬ የሚሆነኝ ሕይወት የሚሰጠኝ
እግዚአብሔ ብቻ ነው የሚያስተማምነኝ
አምላኬ ብቻ ነው የሚያስተማምነኝ
እኔ ንጉሥ ነበርኩ በክብር ያጌጥኩኝ
ሁሉን በምድር ላይ በጥበብ ፈፀምኩኝ
የዚህ አለም ደስታ ምንም አላዋጣኝ
በመጨረሻው ቀን በሞት ተወሰድኩኝ/2/
ከፀሐይቱ በታች አዲስ ነገር የለም
ሰዎች ይደክማሉ እስከ ዘለዓለም
ጥበቡን ፍለጋ ደክሜ ነበረ
ሁሉም ከንቱ ሆኖ በመቃብር ቀረ/2/
ከእኔ አስቀድመዉ የከበሩ ሁሉ
አፈር ተጭኗቸዉ የከበሩ ሁሉ
እብደትና እዉቀት ሁሉን አወቅኳችሁ
ምንም ቋሚ የለም ሁሉም ከንቱ ናቸዉ/2/
ልቤን የሰተሁት ተስፋ የጣልኩበት
አልጨበጥ ብሎኝ አለሁኝ በጭንቀት
የጥበቡም ብዛት ለትካዜ ሰተኝ
እኔ በዚህ ምድር እጅግ ጐስቋላ ነኝ/2/
ልቤንም ፈተንኩት በደስታ በዛት
የዚህን አለም ለውጥ ጣውት አቀመስኩት
ሳቅም በልቤ ዉስጥ ይፍለቀለቅ ነበር
ሁሉም ከንቱ ሆነ ገብቶ ከመቃበር/2/
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ | 145 |
| 20 | ያዕቆብ ከቤርሳቤህ
ያዕቆብ ከቤርሳቤህ ወደ ካራን ሲሄድ
የለውም ነበረ አማካሪ ዘመድ
ፀሐይ ጠልቃ ነበር ከዚያ እንደ ደረሰ
ከእራሱም በታች ድንጋይ ተንተራሰ
አዝ
ህልምንም አለመ ታላቁን ራዕይ
መሰላል ተተክሎ ከምድር እስከ ሰማይ
ሲወጡ ሲወርዱ መላዕክት በእርሷላይ
እግዚአብሔርም ቆሞ ከላይ ከጫፏላይ
አዝ
የአባቶችህ አምላክ እኔ እግዚአብሔር ነኝ
ይህንን ምድር ለእርስትህ እሰጥሀለሁኝ
ዘርህ እንደ አሸዋ በምድር ይዘራል
በአራቱም ማዕዘን ህዝብህም ይሆናል
አዝ
አበው በምሳሌ እንደ ተናገሩት
ከምድር እስከ ሰማን አምላክ የዘረጋት
በላይዋ ተቀምጦ በግልፅ የታየባት
የያዕቆብ መሰላል እመቤታችን ናት
አዝ
ሰማይና ምድር የሚታረቁባት
ወልደ እጓለ እምሕያው የተወለደባት
መላእክት ከሰማይ በአንድ የዘመሩባት
ታላቋ መሰላል እመቤታችን ናት
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ | 148 |
