Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
Use This Link For More Information https://twitter.com/EthiopiaFeacc https://www.youtube.com/channel/UCO_WiCAiDIkMMwqsZGK47nw/?guided_help_flow=5/ https://www.facebook.com/feaccOfficial/
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
کانال Federal Ethics And Anti- Corruption Commission (@feacc) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 087 مشترک است و جایگاه 5 066 را در دسته سیاست و رتبه 3 305 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 087 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 200 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 1 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 11.04% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.71% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 114 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 576 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Use This Link For More Information https://twitter.com/EthiopiaFeacc https://www.youtube.com/channel/UCO_WiCAiDIkMMwqsZGK47nw/?guided_help_flow=5/ https://www.facebook.com/feaccOfficial/”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته سیاست تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | በመልካም ሥነምግባር የታነጸ ትውልድ ለሀገር ግንባታ መሠረት ይሆናል!
************************
በመልካም ሥነምግባር የታነጸ ትውልድ ለአንዲት ሀገር ዘላቂ ዕድገት፣ ሰላምና ሉዓላዊነት ዋነኛው ምሰሶ ነው። በዕውቀት ብቻ ሳይሆን በላቀ ሥነ-ምግባር፣ በታማኝነትና በሀገር ፍቅር የታነጸ ትውልድ ሲፈጠር የሀገር ግንባታ ጉዞ አስተማማኝ መሠረት ይኖረዋል።
በመልካም ሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ለሀገር ግንባታ የሚኖረው ሚና በዋናነት በሚከተሉት ዓምዶች ላይ ይገለጻል፡፡
👉🏿 ጠንካራና ታማኝ ተቋማትን መገንባት፦ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን የሚጸየፍ፣ ለሕግ የበላይነት የሚገዛ እና ተጠያቂነትን የሚያከብር ትውልድ ጠንካራና ተዓማኒነት ያላቸውን ብሔራዊ ተቋማት ለመገንባት ቀዳሚው ኃይል ነው።
👉🏿 ማኅበራዊ ፍትሕና አንድነትን ማጠናከር፦ እርስ በርስ መከባበር፣ እውነትን መፈለግ እና ለጋራ ጥቅምና ለሕዝብ ደህንነት ቅድሚያ መስጠት የሚቻለው ሥነ-ምግባራዊ እሴቶች በማኅበረሰቡ ውስጥ ስር ሲሰዱ ብቻ ነው።
👉🏿 ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ፦ በሥራ ወዳድነት፣ በቅንነት እና በኃላፊነት ስሜት የሚንቀሳቀስ የሰው ኃይል የሀገርን ሀብትና ንብረት ሳያባክን ለታለመለት የልማት ዓላማ በማዋል የፈጠራና የዕድገት ሞተር ይሆናል።
በአጠቃላይ፣ ሥነ-ምግባር የሌለው ዕውቀት መሪ እንደሌለው መርከብ ነው፤ በመሆኑም የትውልድ ግንባታ ላይ የሚደረግ ማንኛውም ኢንቨስትመንት በቀጥታ የሀገርን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የመወሰን አቅም አለው።
ይህንን ዓላማ ለማሳካት ደግሞ የቤተሰብ፣ የትምህርት ተቋማት፣ የባህልና የሃይማኖት እሴቶች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነው።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 903 |
| 3 | بدون متن... | 815 |
| 4 | ፍትሐዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው ከሙስና የጸዳ አሠራር ሲሰፍን ነው!
************************
ሙስና በሌለበትና ግልጽነት በሰፈነበት ሥርዓት ውስጥ አገልግሎቶች የሚሰጡት በብቃት፣ በሕግና በቅደም-ተከተል ላይ ተመስርቶ ነው። ይህ ሲሆን እያንዳንዱ ዜጋ ወይም ሠራተኛ ያለ አድልዎ እኩል ተጠቃሚ ይሆናል።
በተቃራኒው ሙስና ባለበት ቦታ ውሳኔዎች የሚወሰኑት በሕግ ሳይሆን በዝምድና፣ በወቅታዊ ጥቅም (ጉቦ) ወይም በውስጥ መተዋወቅ ላይ ተመስርቶ ነው። ይህ ደግሞ መብትና ብቃት ያላቸው ሰዎች እንዲገለሉና ተገቢው ጥራት የሌላቸው ግለሰቦች ብቻ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል። ከሙስና የጸዳ አሠራር ሲኖር ግን ይህ የአድልዎ በር ሙሉ በሙሉ ይዘጋል፤ በዚህም ፍትሐዊነት ይነግሣል።
አንድ ተቋም ከሙስና የጸዳ አሠራርን ሲዘረጋ፣ ሁሉም ተገልጋይ ምንም ዓይነት የማኅበራዊ ወይም የኢኮኖሚ ደረጃ ልዩነት ሳይደረግበት እኩልና ፈጣን አገልግሎት ያገኛል። እንዲሁም አሠራሮችና ውሳኔዎች በግልጽ የሚታዩ በመሆናቸው ማንም ሰው መብቱን በቀላሉ ማስከበር ይችላል።
ይህ ካልሆነ ሙስና የሀገርንና የተቋምን ሀብት በጥቂት ግለሰቦች እጅ እንዲከማች በማድረግ አብዛኛውን ማኅበረሰብ ለድህነት ይዳርጋል። አሠራር ከሙስና የፀዳ ሲሆን ግን የተመደበው በጀትና ሀብት በቀጥታ ለታለመለት የልማትና የአገልግሎት ሥራ ይውላል። ይህ ደግሞ የጋራ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ማኅበራዊ ትስስርንና መተማመንን ያጠናክራል።
በአጠቃላይ፣ ፍትሕ ተጠቃሚነት ዝም ብሎ የሚመጣ ሳይሆን፣ ተቋማዊ አሠራሮች ከሙስና፣ ከሕገ-ወጥነትና ከግል ፍላጎት በፀዳ መልኩ ተግባራዊ ሲያደርጉ ነው።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 869 |
| 5 | بدون متن... | 793 |
| 6 | ሙስናና ብልሹ አሰራርን ማስወገድ የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አይነተኛ ሚና ይጫወታል - ክብርት ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)
*****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ዘርፍ ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል።
ስልጠናዊ ውይይቱ በሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭትን መከላከልና ማስተዳደር ላይ ግንዛቤ በማስጨበጥ ተቋማት ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዝና አመራሮች የፀረ-ሙስና ትግሉን በባለቤትነት እንዲመሩ የሚያስችል ነው።
በስልጠናው የተገኙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ማንኛውም የመንግስት ተቋም የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት መወጣት የሚችለው ማህበረሰቡን በታማኝነትና በቅንነት ሲያገልግልና የተቋሙን ሀብት በቁጠባና በውጤታማነት ሲጠቀም ብቻ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አያይዘውም በየደረጃው የሚገኘው አመራር ራሱን ወደ ውስጥ በመመልከትና ክፍተቶቹን ፈጥኖ በማረም ለሕዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል በሙሉ ቁርጠኝነት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የመንግስት አገልግሎት ሪፎርም በዋናነት የህዝብን እርካታ ከፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ጠቅሰው፥ በአሁኑ ወቅት የትኛውም ተቋም በትላንትናው የቢሮክራሲ አስተሳሰብ ዛሬ ላይ ውጤታማ ሊሆን ስለማይችል ሙስናና ብልሹ አሰራርን ማስወገድ የዜጎችን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አይነተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የአሰራር ስርዓትን ለመዘርጋትና ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም፣ አሁንም በአመራሩና በፈጻሚው ላይ የሚስተዋሉ የአመለካከትና የክህሎት ክፍተቶችን መሙላት የግድ እንደሚል ተናግረዋል።
ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በስራ ክፍላቸው ላሉ ኃላፊዎችና ፈጻሚዎች በማካፈል፣ ተቋሙን ከሙስና የጸዳ፣ ተገልጋይን የሚያረካና ሀብትን በቁጠባ የሚጠቀም በማድረግ የዘላቂ ማህበራዊ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፤ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ! በሚል መሪ ቃል ከሚኒስቴር መስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በተካሄደው ስልጠናዊ ውይይት የተገኙት ተሳታፊዎች ሀሳብ፣ አስተያየቶችና ጥያቄዎች አንስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 998 |
| 7 | بدون متن... | 999 |
| 8 | የምክክር ጉባዔው ከሚመክርባቸው 8ቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ አጀንዳ ቁጥር 7 (ሙስና እና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች) በምን በምን ጉዳዮች ላይ ይመክራል?
******
7.1. የመልካም አስተዳደር ችግር እና የሙስና ጉዳዮች
7.2. የፀረ-ሙስና ስርዓት ግንባታ
7.3. የመልካም አስተዳደር ስርዓት ግንባታ
7.4. ፍትሀዊ ፓብሊክ ሰርቪስ
7.4.1. ፍትሀዊና አካታች ፓብሊክ ሰርቪስ
7.4.2. በብቃት ላይ የተመሰረተ የሰው ሀብት አመዳደብ እና ቅጥር
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 016 |
| 9 | ሥነምግባር ያለው እና በባህሉ የሚኮራ ትውልድ ማፍራት ከሁሉም ይጠበቃል - ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ
*
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከባህልና ስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ዘርፍ ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል።
ስልጠናዊ ውይይቱ የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፤ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ! በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን፤ በሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭትን መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
በስልጠናው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ዘርፉ በሀገረ-መንግስት ግንባታ ውስጥ ትልዕቅ ተልዕኮ የተሰጠው ዘርፍ ነው። ለዚህ ደግሞ ሥነምግባር ያለው እና በባህሉ የሚኮራ ትውልድ ማፍራት አንዱ በመሆኑ ስራውን መስራት ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል።
በዘርፋችን ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ አሰራሮችን በመለየት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፣ ይህ ስልጠና ከፍተኛ አመራሮች በዕለት ተዕለት በሚሰሯቸው ስራዎች ውስጥ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲሰሩ ግንዛቤ ይፈጥራል ብለዋል።
አክለውም ሙስናን ከመፈጸሙ በፊት ለመከላከል ግንዛቤ መፍጠር በሀገራችን የተጀመረውን የፀረ-ሙስና ትግል ይበልጥ ውጤታማ ያደርገዋል ሲሉ ተናግረዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው አመራሮች ውሳኔ የመስጠት ጉዳይ የዕለት ተዕለት ተግባራቸው በመሆኑ ሲወስኑ ሥነምግባራዊ እና ከጥቅም ግጭት የጸዱ መሆን እንዳለባቸውም ተናግረዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ዘርፉ ለሙስናና ብልሹ አሰራሮች ተጋላጭ በመሆኑ አመራሩ በተቀናጀ መልኩ በትኩረት መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።
ተቋማት የፀረ-ሙስና ትግሉን ቅንጅት በመፍጠር መስራትና በባለቤትነት መምራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
በስልጠናዊ ውይይቱ በዘርፉ ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ አሰራሮች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን፣ ከተሳታፊዎችም ሀሳብ፣ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 984 |
| 10 | بدون متن... | 900 |
| 11 | አምባሳደሮች፣ ቆንስል ጄኔራሎች እና በየደረጃው የሚገኙ የዲፕሎማሲ ሥራ ፈጻሚዎች የበይነ-መረብ ስልጠናዊ ውይይት አካሄዱ
*****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በውጭ ጉዳይ ዘርፍ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሚሲዮኖች ለሚገኙ የሚሲዮን መሪዎችና የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ፈጻሚዎች የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፤ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ! በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል።
ስልጠናዊ ውይይቱ በሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭትን መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በስልጠናዊ ውይይቱ በሁሉም ክፍለ ዓለማት የሚገኙ አምባሳደሮችን፣ ቆንስል ጄኔራሎችን እና በየደረጃው ያሉ የዲፕሎማሲ ስራ ፈጻሚዎችን ያሳተፈ ነው።
በበይነ-መረብ ዘዴ በተሰጠው ስልጠና የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ የስልጠናው ዋና አላማ ዲፕሎማቶቻችን የውጭ ግንኙነት ሥራቸውን ሲያከናውኑ ሁልጊዜም የአገራችንን ብሔራዊ ጥቅም በላቀ ሁኔታ ባስቀደመና በታማኝነት መርህ ላይ በተመሰረተ መልኩ እንዲሆን ተጨማሪ ግንዛቤና አቅም መፍጠር ነው ብለዋል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 818 |
| 12 | بدون متن... | 866 |
| 13 | #ሙስና የምክክር ጉባዔው ከሚመክርባቸው 8 ዋና ዋና አጀንዳዎች መካከል አንዱ ነው! | 1 151 |
| 14 | ሙስና በሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ ሆኖ መካተቱ ምን አስተዋጽኦ ይኖረዋል?
*****
ሙስና በሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ እንደ አንድ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ መካተቱ፣ ለአገር ግንባታ እና ለዘላቂ ሰላም እጅግ ከፍተኛና ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አለው። ይህ ታላቅ መድረክ በሙስና መከላከል ረገድ በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
👉 ተቋማዊ ታማኝነትን እና የህዝብ እምነትን ለመገንባት፡- ሙስና በመንግስትና በህዝብ መካከል ያለውን እምነት የሚሸረሽር ዋነኛ መንስኤ ነው። አጀንዳው በምክክሩ መድረክ መቅረቡ የዜጎች በመንግስት ተቋማት ላይ ያላቸው እምነት እንዲጨምር በር ይከፍታል። እንዲሁም ግልጽነትና ተጠያቂነትን የማስፈን ስራ የአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን የጋራ ብሄራዊ ስምምነት እንዲሆን ያደርጋል።
በምክክር መድረኮች አማካኝነት በተቋማት ውስጥ ያሉ የሙስና ስጋቶችን በግልጽ በመለየት፣ ተቋማቱ ከፖለቲካዊና ከግል ጥቅም ነፃ ሆነው ሙያዊ ሥነምግባርን ብቻ መመሪያቸው አድርገው እንዲሠሩ ሕዝባዊ መሠረት ይጥላል።
👉 ለግጭቶች መንስኤ የሆኑ ኢኮኖሚያዊ ኢ-ፍትሃዊነቶችን ለመቅረፍ፡- በብዙ ሃገራት ለፖለቲካዊ አለመረጋጋት እና ለህዝባዊ ቅሬታዎች መነሻው የሀብት ክፍፍል ኢ-ፍትሃዊነት ነው። ሙስናን በምክክሩ በግልጽ መወያየት በሀብት ዘረፋ፣ በግዥ ሥርዓት ግድፈቶች እና በፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ዙሪያ ያሉትን ስር የሰደዱ ችግሮች ለመፈተሽ ይረዳል።
የሃገር ሀብት ለጥቂቶች ሳይሆን ለልማትና ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል የሚያስችል ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠርም ያግዛል።
👉 ሙስናን የመከላከል ስራን ከፖለቲካዊ ፍጆታ ለማውጣት፡- ብዙውን ጊዜ የሙስና ክሶች ከፖለቲካዊ ፍላጎቶች ጋር የመያያዝ ዝንባሌ ይታይባቸዋል።
ጉዳዩ በሃገራዊ ምክክሩ ሲካተት ግን፣ ሙስናን የመዋጋት ጉዳይ የጋራ ሥነ-ምግባር እና ብሄራዊ እሴት ተደርጎ እንዲወሰድ ያደርገዋል። የፀረ-ሙስና ተቋማት ከፖለቲካዊ ጫና ነፃ ሆነው የሚሰሩበትን ጠንካራ መዋቅራዊ መሰረት ለመጣል ያስችላል።
👉 ሁሉን አቀፍ የዜጎች ተሳትፎን ለማጠናከር፡- ሃገራዊ ምክክር የሲቪክ ማህበራት፣ የሙያ ማህበራት፣ የወጣቶች እና የብዙሃን ድምጽ የሚሰማበት መድረክ ነው። ዜጎች በሙስና ምክንያት የሚደርስባቸውን ተጽዕኖ በግልጽ እንዲናገሩ እና የበኩላቸውን የመፍትሄ ሃሳብ እንዲያበረክቱ እድል ይሰጣል።
እንዲሁም ሙስናን የመታገል ስራ የመንግስት ብቻ ሳይሆን የዜጎችም የባለቤትነት ስሜት እንዲሆን ያደርጋል።
👉 ለዘላቂ ልማትና አስተማማኝ መዋቅር ዋስትና ለመሆን፡- አንድ ሃገር በዲጂታል ኢኮኖሚ፣ በታዳሽ ሃይልም ሆነ በሌሎች መሰረተ-ልማቶች ለማደግ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ከሙስና የፀዱ መሆን አለባቸው። ይህ አጀንዳ በምክክሩ መፍትሄ ሲበጅለት፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን እና የዓለም አቀፍ ተቋማትን አመኔታ ለመሳብ ትልቅ አቅም ይፈጥራል።
በአጠቃላይ፣ ሙስናን በሃገራዊ ምክክር ውስጥ መካተቱ ችግሩን ከነቅድመ-ሁኔታው አምኖ በመቀበል፣ ለወደፊቷ ሃገር አስተማማኝ፣ ፍትሃዊ እና በሥነ-ምግባር የታነጸ ተቋማዊ መዋቅር ለመዘርጋት አስተዋጽኦው የላቀ ይሆናል።
እንዲሁም ሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ መግባባት መፍጠሪያ ብቻ ሳይሆን፣ ሀገርን ከውስጥ የሚበላውን የሙስና ወረርሽኝ በዘላቂነት ለመከላከልና የሕዝብን የሥነምግባር እሴት ከፍ ለማድረግ የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊ ዕድል ነው።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 204 |
| 15 | بدون متن... | 905 |
| 16 | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከለያቸው 8 ዓበይት አጀንዳዎችን መካከል አንዱ ሙስና መሆኑን አስታወቀ
*****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 17/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከቀረቡለት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ጉዳዮች መካከል ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው 8 ዓበይት አጀንዳዎችን መለየቱን አስታውቋል።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ የሀገር ግንባታ፣ የመንግስት አደረጃጃትና ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባ እና ድሬድዋ ከተሞች፣ የሐይማኖት፣ የተቋማት ግንባታ የህግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብቶች፣ የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች፣ ሙስና እና የመልካም አስተዳዳር እንዲሁም የሰላም ግንባታ የለያቸው 8 አባይት ጉዳዮች ናቸው።
እነዚህ አጀንዳዎች በመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚጀምረው ታላቅ ጉባኤ ላይ 130 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ሕዝብን የሚወክሉ ተሳታፊዎች በሰፊው የሚመክሩባቸው ዋና ዋና ጭብጦች መሆናቸው ተገልጿል።
ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ የተመረጡት 8 አጀንዳዎች በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች የተካሄዱ ሰፊና ግልጽ የውይይት ሂደቶች ውጤቶች መሆናቸውን ጠቁሟል።
በሂደቱም ከውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ከሲቪል ማኅበረሰብ፣ ከፌደራል ተቋማት እስከ ክልላዊ መንግሥታት ድረስ ሁሉም አካላት ተሳትፈዋል።
እነዚህ አጀንዳዎች ሙሉ በሙሉ የሕዝቡ ድምፅ፣ ቅሬታ፣ ተስፋ እና ፍላጎት የተንጸባረቁባቸው መሆናቸውም ተገልጿል።
የምክክሩ ስኬት የሁላችንንም በጎ ተሳትፎ ይጠይቃል ያሉት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አረዓያ፥ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በሂደቱ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 093 |
| 17 | بدون متن... | 1 125 |
| 18 | የትውልድ ሥነምግባር ማነጽ የሁላችንም ድርሻ ነው!
**********************
የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ለአንድ አገር ዘላቂ ልማት፣ ሰላም፣ ፍትሕ እና መልካም አስተዳደር መረጋገጥ መሠረታዊ አካል ነው። ጤናማ፣ ኃላፊነት የሚሰማው፣ ታማኝና አገር ወዳድ ትውልድ ለመቅረጽ የሚከናወነው ይህ የሥነምግባር ግንባታ በዋናነት በሚከተሉት ቁልፍ ምሶሶዎች ላይ ይደገፋል፡፡
1. ቤተሰብ፡- ቤተሰብ የማኅበረሰብ መሠረት እና የመጀመሪያው የሥነምግባር መቅረጫ ማዕከል ነው። ልጆች መልካም እሴቶችን (ታማኝነት፣ አክብሮት፣ ሩኅሩኅነት እና ታጋሽነት) በመጀመሪያ በተግባር የሚያዩትና የሚቀስሙት ከወላጆቻቸው ወይም ከአሳዳጊዎቻቸው በመሆኑ ቤተሰብ አርዓያ ሊሆኑ ይገባል።
ከዚህ ባሻገር ቤተሰብ ከልጆች የሚያስተውሉትን ስህተቶች በወቅቱ የማረም እና መልካም ባህሪን የማበረታታት ኃላፊነት አለባቸው።
2. የትምህርት ተቋማት፡- ከመዋዕለ ሕፃናት እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሉት መዋቅሮች መደበኛ ዕውቀትን ከማስጨበጥ ባለፈ የዜግነት ባህሪን የሚገነቡባቸው ቦታዎች ናቸው።
በተለይ የሥነዜጋና ሥነምግባር ትምህርት ሕግ አክባሪነትን፣ ሰብአዊ መብቶችን፣ ብዝሃነትን ማክበርንና ተጠያቂነትን በስርዓተ ትምህርት ውስጥ አካቶ ማስተማርን የያዘ ነው። እንዲሁም የአካዳሚክ ትምህር ደግሞ ታማኝነት በፈተናና በምርምር ሥራዎች ላይ ማጭበርበርን መዋጋት፣ የራስ ጥረትና ጥራትን ያካትታል።
3. የሃይማኖት ተቋማት፡- በማኅበረሰቡ ሕሊና እና የሞራል እሴት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የማሳደር አቅም አላቸው። የሕሊና ዳኝነት ሲኖር ከሕግ አስገዳጅነት ባለፈ፣ በፈሪሃ እግዚአብሔር/በሞራል የታነጸ እና ውስጣዊ እምነትን መሠረት ያደረገ በጎ ባህሪን ያላብሳል።
ከዚህ ባሻገር አገር በቀል እሴቶችም እንደ ዕርቅ፣ አብሮነት፣ ማኅበራዊ ኃላፊነት እና ታማኝነት ያሉ አገር በቀል የባህል እሴቶችን ለትውልድ ማሻገር ሌላኛው ኃላፊነት ነው።
4. የመንግሥት ተቋማት፡- መንግሥታዊ ተቋማት ሥነምግባርን በተግባር የሚተረጉሙበት እና ሥርዓት የሚያስይዙበት ምሶሶ ነው። ተቋማዊ ታማኝነትና ግልጽነት ሲፈጠርና የመንግሥት አሠራሮች ከሙስና እና ከአድልዎ የጸዱ ሲሆኑ፣ ትውልዱ በተቋማት ላይ እምነት ያሳድራል፤ የአሠራር ሥርዓቱንም ያከብራል።
እንዲሁም ጥፋት ያጠፋን የመቅጣት እና በታማኝነት ያገለገለን የማበረታታት የተጠያቂነት ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡
5. የሚዲያ ተቋማት፡- በአሁኑ ዘመን የትውልድን አስተሳሰብ፣ አመለካከትና የትርክት አቅጣጫ በመቅረጽ ረገድ ሚዲያ በተለይም ማኅበራዊ ሚዲያ ትልቅ ድርሻ አለው። በዚህም አርዓያ ሊሆኑ የሚችሉ ግለሰቦችን ታሪክ ማጉላት እና የጋራ ብሔራዊ እሴቶችን ማስተዋወቅ ይገባል።
በተለይ የሐሰት መረጃዎችን፣ ጥላቻንና አምባገንነትን በመዋጋት ረገድ ትውልዱ ኃላፊነት የሚሰማው የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆን ማገዝም ያስፈልጋል።
6. ማኅበረሰብ፡- "አንድ ልጅ በባህልና በማኅበረሰብ አብሮነት ያድጋል" እንደሚባለው፣ ግለሰቡ የሚኖርበት አካባቢ ሥነምግባር በትውልዱ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ አለው። ማኅበረሰቡ መጥፎ ድርጊቶችን በጋራ የሚያወግዝበት እና በጎ ተግባራትን የሚደግፍበት ማኅበራዊ እሴት ማጠናከር ጠቀሜታው የጎላ ነው።
እንዲሁም ወጣቶች በማኅበረሰብ ልማትና በበጎ ፈቃድ ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ በማድረግ የርኅራኄና የኃላፊነት ስሜትን ማሳደግ ያስፈልጋል።
በአጠቃላይ፣ የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ የአንድ ወገን ሥራ አይደለም። እነዚህን ምሶሶዎች በተቀናጀ፣ በተደጋጋፊ እና እርስ በርስ በተሳሰረ መልኩ ሲሠሩ ጠንካራና አስተማማኝ አገራዊ ስብዕና ያለው ትውልድ ማፍራት ይቻላል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 212 |
| 19 | بدون متن... | 1 054 |
| 20 | የሀገር ሀብት ለልማት እንዲውል፤ ሙስናን በጋራ እንከላከል!
*********************
የአንድ ሀገር የተፈጥሮ ፀጋዎች፣ የህዝብ ታክስ እና ልዩ ልዩ ገቢዎች በአግባቡ ስራ ላይ ሲውሉ የሀገር ኢኮኖሚያዊ አቅም ያድጋል። የህዝብ ሀብት ሳይባክን ለታለመለት አላማ ሲውል ደግሞ ጥራት ያላቸው ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ መንገዶች እና የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦቶች ይገነባሉ።
ለትውልድ የሚተርፍ ጠንካራ ተቋማዊ አቅም መገንባት የሚቻለው እያንዳንዱ ሀብት ለልማት ፕሮጀክቶች በቁጠባ እና በልዩ ትኩረት መዋል ሲችል ነው።
በአንፃሩ ለህዝብ ጥቅም መዋል የነበረበት በጀት በጥቂት ግለሰቦች እጅ ሲገባ የልማት ፕሮጀክቶች ይስተጓጎላሉ ወይም ጥራታቸውን ያጣሉ። ይህ ደግሞ የሙስናና ብልሹ አሰራር ምልዕክትና መገለጫ ነው፡፡ ሙስና በድሆችና በባለጸጎች መካከል ያለውን ልዩነት በማስፋት፣ ማህበራዊ ቀውስና አለመረጋጋትን ይፈጥራል። ይህ እንዳይሆን ደግሞ በቁርጠኝነትና በጽናት መታገል ግድ ይላል፡፡
ሆኖም ሙስናን እና የአሰራር ብልሹነትን መዋጋት የአንድ አካል ወይም የአንድ ተቋም ብቻ ኃላፊነት አይደለም። ጠንካራ ማህበረሰብ እና ተቋማትን ለመገንባት የጋራ ትብብር ያስፈልጋል፤ እያንዳንዱ ዜጋም የሀገር ሀብት የራሱ መሆኑን ተገንዝቦ ጠባቂና ተቆጣጣሪ መሆን ይኖርበታል።
እንዲሁም በአሰራሮች ላይ ግልፅነት እንዲሰፍን መጠየቅ፣ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ማጋለጥ እና ለታማኝነትና ለሙያ ሥነ-ምግባር እሴቶች ቅድሚያ መስጠት የጋራ ትግሉ አካል ነው።
ስለሆነም፣ ሌብነትን ማስወገድ ማለት ቀጥተኛ የልማት በሮችን መክፈት በመሆኑ የሀገርን ሀብት ከብክነትና ከዘረፋ በመጠበቅ፣ ዜጎች በጋራና በቁርጠኝነት በመቆም፣ በጎ ሥነ-ምግባር ያለውና የበለፀገ ማህበረሰብ መገንባት ይኖርባቸዋል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 344 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
