Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
前往频道在 Telegram
9 948
订阅者
+1324 小时
+577 天
-230 天
数据加载中...
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+96
在2个频道中
五月 '26
+259
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+314
在2个频道中
Get PRO
三月 '26
+207
在2个频道中
Get PRO
二月 '26
+189
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+188
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+135
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+342
在1个频道中
Get PRO
十月 '25
+270
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+64
在2个频道中
Get PRO
八月 '25
+36
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+33
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+50
在2个频道中
Get PRO
五月 '25
+86
在2个频道中
Get PRO
四月 '25
+35
在2个频道中
Get PRO
三月 '25
+56
在3个频道中
Get PRO
二月 '25
+20
在1个频道中
Get PRO
一月 '25
+28
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+100
在2个频道中
Get PRO
十一月 '24
+410
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+538
在2个频道中
Get PRO
九月 '24
+531
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+657
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+944
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+670
在3个频道中
Get PRO
五月 '24
+838
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+955
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+974
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+629
在2个频道中
Get PRO
一月 '24
+404
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+331
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+212
在4个频道中
Get PRO
十月 '23
+104
在2个频道中
Get PRO
九月 '23
+89
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+172
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+140
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+138
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+212
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+163
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+107
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+84
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+104
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+200
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+245
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+197
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+172
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+59
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+51
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+80
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+137
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+143
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+238
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+74
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+92
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+556
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 11 六月 | +9 | |||
| 10 六月 | +14 | |||
| 09 六月 | +10 | |||
| 08 六月 | +5 | |||
| 07 六月 | +8 | |||
| 06 六月 | +12 | |||
| 05 六月 | +15 | |||
| 04 六月 | +10 | |||
| 03 六月 | +6 | |||
| 02 六月 | +7 | |||
| 01 六月 | 0 |
频道帖子
ኮሚሽኑ ለተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚዎች በዲጂታል ሀብት ምዝገባ አተገባበር ላይ ስልጠናዊ ውይይት አካሄደ
*********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚዎች በዲጂታል ሀብት ምዝገባ አተገባበር ላይ ተግባር ተኮር ስልጠናዊ አካሂዷል።
የስልጠናው ዓላማ የዲጂታል ሀብት ምዝገባ አተገባበር ምን ላይ እንዳለ በመገምገም ያጋጠሙ ችግሮችን ለመለየት እና የቀጣይ ውጤታማነቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል ትኩረት ያደረገ ነው።
በመድረኩ ንግግር ያደረጉት በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ዲጂታል የሀብት ምዝገባ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ እየተተገበረ ያለና ውጤታማ የሆነ ስርዓት ነው። በዚህም የተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ሀብታቸውን በዲጂታል ስርዓት እያስመዘገቡ ይገኛሉ ብለዋል።
የዲጂታል ሀብት ምዝገባ ሥርዓት ሙስናን ለመከላከል አንዱ መንገድ ነው ያሉት ም/ኮሚሽነሩ ይህን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግና አቅሙን ለማሻሻል ሲስተሙን ወደ ክላውድ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል።
በኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የሀብት ምዝገባ ሥራ በባህሪው አስቸጋሪ በመሆኑ ቴክኖሎጂን መጠቀም ውጤታማ ያደርጋል። ለዚህ ደግሞ የዲጂታል ሀብት ምዝገባ ስርዓት ትልቁ ማሳያ ነው ብለዋል።
አክለውም ሀብታቸውን ማስመዝገብ ያለባቸው የተቋማት አመራርና ሰራተኞች ሁሉ ሥርዓቱን ተጠቅመው እንዲያስመዘግቡ ግንዛቤ መፍጠሩ ላይ ትኩረት ተደርጎ መሠራት እንዳለበት ተናግረዋል።
የዲጂታል የሀብት ምዝገባ ስርዓቱን ውጤታማነቱን ለማስቀጠል ምዝገባውን በካላንደር መምራት የበለጠ ውጤታማ ያደርጋል ያሉት ደግሞ በኮሚሽኑ የሀብት ምዝገባና የጥቅም ግጭት መከላከል መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ኮከብ አንበርብር ናቸው።
በመድረኩ በበጀት ዓመቱ የተቋማት የዲጂታል ሀብት ምዝገባ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በሪፖርቱ ከ128 ሺህ በላይ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ሀብታቸውን በዲጂታል ሥርዓቱ እንዳስመዘገቡም ተገልጿል።
ከእነዚህ ወስጥ ከዕቅዳቸው በላይ የሰሩ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ ከዕቅድ በታች የሰሩ በመኖራቸው ለምን ወደኃላ ቀሩ የሚለውን ማየት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
በመድረኩ በዲጂታል ሥርዓቱ ላይ እስካሁን ያጋጠሙ ችግሮችን በየጊዜው በመለየት መፍታት መቻሉም ተመላክቷል።
በስልጠና መድረኩ የዘርፎችና ተጠሪ ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚዎች የተገኙ ሲሆን፤ ከተሳታፊዎች ጥያቄ፣ ሀሳብና አስተያየቶች ተነስተው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።
| 2 | 没有文字... | 331 |
| 3 | 没有文字... | 333 |
| 4 | ኮሚሽኑ የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሄደ
**********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የሰጣቸውን ስልጠናዎች ጥንካሬና ክፍተት የገመገመበት የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሂዷል።
ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ ደረጃዎች ለሚገኙ አካላት የሰጣቸውን ስልጠናዎች ከቅድመ-ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ በስልጠና አሰጣጥ ሂደት እና ድህረ-ስልጠና ስራዎች አንጻር ተገቢነቱንና ጥራቱን ገምግሟል።
በመድረኩ ሙስናን ለመከላከል የሥነ-ምግባር ግንባታ ስራ ዋነኛውና ቀዳሚው መሆኑ ተገልጿል፡፡ የሥነ-ምግባር ግንባታ ስልጠናዎችም ከመርሃ-ግብር ባለፈ በሰልጣኞች ላይ የባህሪና የአመለካከት ለውጥ የሚያመጡ መሆን እንዳለባቸው ተመላክቷል።
የሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የስልጠናዎችን ጥራትና ተገቢነት በየደረጃው ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል።
የስልጠና ጥራትና ተገቢነት ማረጋገጥ በቀጣይ ለሚሰሩ የትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎች ስኬታማነት ጠንካራ መሰረት የሚጥል መሆኑም መገለጹን በኮሚሽኑ የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 491 |
| 5 | ኮሚሽኑ የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሄደ
**********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የሰጣቸውን ስልጠናዎች ጥንካሬና ክፍተት የገመገመበት የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሂዷል።
ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ ደረጃዎች ለሚገኙ አካላት የሰጣቸውን ስልጠናዎች ከቅድመ-ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ በስልጠና አሰጣጥ ሂደት እና ድህረ-ስልጠና ስራዎች አንጻር ተገቢነቱንና ጥራቱን ገምግሟል።
በመድረኩ ሙስናን ለመከላከል የሥነ-ምግባር ግንባታ ስራ ዋነኛውና ቀዳሚው መሆኑ ተገልጿል፡፡ የሥነ-ምግባር ግንባታ ስልጠናዎችም ከመርሃ-ግብር ባለፈ በሰልጣኞች ላይ የባህሪና የአመለካከት ለውጥ የሚያመጡ መሆን እንዳለባቸው ተመላክቷል።
የሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የስልጠናዎችን ጥራትና ተገቢነት በየደረጃው ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል።
የስልጠና ጥራትና ተገቢነት ማረጋገጥ በቀጣይ ለሚሰሩ የትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎች ስኬታማነት ጠንካራ መሰረት የሚጥል መሆኑም መገለጹን በኮሚሽኑ የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov. | 470 |
| 6 | ከሙስናና ብልሹ አሰራር የጸዳ የግብር ሥርዓት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መሠረት ነው!
*********************
ግብር የአንድ ሀገር የልማትና የሉዓላዊነት የጀርባ አጥንት ነው። ይሁን እንጂ ይህ የገቢ ምንጭ ለሀገር ዕድገት እውነተኛ መሠረት መሆን የሚችለው የግብር ሥርዓቱ ከሙስናና ከብልሹ አሰራር የጸዳ ሲሆን ብቻ ነው።
የግብር ሥርዓቱ ግልጽና ታማኝ ሲሆን፣ መሰብሰብ ያለበት የመንግሥት ገቢ ሳይባክንና በጥቂት ግለሰቦች እጅ ሳይገባ ለመሠረተ-ልማቶች ግንባታ ይውላል።
ብልሹ አሰራር ባለበት ሥርዓት ውስጥ ሕግ አክባሪ ግብር ከፋዮች ይጎዳሉ፤ ታማኝ ያልሆኑት ደግሞ ያለአግባብ ይበለጽጋሉ። ከሙስና የጸዳ አሰራር ግን ለሁሉም ግብር ከፋይ እኩልና ፍትሐዊ መድረክ ይፈጥራል።
ይህም የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች በሥርዓቱ ላይ እምነት ጥለው በስፋት እንዲሳተፉ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ያበረታታል።
የግብር አሰባሰቡ ሂደት ዘመናዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሲሆን፣ ሕብረተሰቡ የሚከፍለው ግብር ለሀገር ልማት በትክክል መዋሉን ይረዳል። ይህም ዜጎች በግዴታ ሳይሆን በባለቤትነትና በኃላፊነት ስሜት ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ያደርጋል።
ስለሆነም የግብር ሥርዓታችንን በማጽዳት፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በጋራ በመታገል የሀገራችንን የኢኮኖሚ በማሳደግ የብልጽግና ጉዟችን ማፋጠን ይኖርብናል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 706 |
| 7 | 没有文字... | 696 |
| 8 | የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ በቤተሰብ እና ማህበራዊ ተቋማት አማካኝነት ለማጎልበት በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ምክክር ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ አመራሮች ጋር ተደርጓል
*****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ በቤተሰብ እና ማህበራዊ ተቋማት አማካኝነት ለማጎልበት በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ምክክር ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ አመራሮች ጋር አድርጓል፡፡
ኮሚሽኑ አገራዊ የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ እና ዘላቂ እንዲሆን በትኩረት ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ነው።
በዚህ ወሳኝ አገራዊ አጀንዳ በርካታ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉ ቢሆንም፣ በቀጣይ በትብብር የሚመራበት የአሰራር ሥርዓት እየተዘረጋ ይገኛል።
ትውልዱን በሥነምግባር ማነጽ ከሥር መሠረቱ መሆን እንዳለበት እና ቤተሰብ እንዲሁም ቅድመ-መደበኛ እና መደበኛ የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ከተለመደው የዕውቀት እና ክህሎት ግንባታ ባሻገር የመልካም ባህሪ ግንባታ በአርዓያነት የሚፈጽሙበት ተገማች አገራዊ የአሰራር ሥርዓት ማጠናከር የትብብሩ ትኩረት ጉዳይ እንደሆነ በውይይቱ ተመላክቷል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 827 |
| 9 | 没有文字... | 678 |
| 10 | 没有文字... | 649 |
| 11 | የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት 50 ሺህ ብር መደለያ የተቀበሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
****************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ህንፃ ውስጥ ነው።
ዘነበ ንጉሴ የተባለው ግለሠብ በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ የህንፃ መጠቀሚያ ባለሙያ ሲሆን፣ የግል ተበዳይ የግንባታ ፍቃድ ለማውጣት 100 ሺህ ብር ተጠይቀው በድርድር 50 ሺህ ብር ይዘው እንዲመጡ ተስማምተዋል።
የግል ተበዳይ የደረሰባቸውን በደል ለክፍለ ከተማው ፖሊስ የወንጀል መከላከል መምሪያ በሰጡት ጥቆማ ተጠርጣሪው በክትትል አባሎች ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል።
ከጉዳዩ ጋር ተሳትፎ የነበረው በክፍለ ከተማው የግንባታ ፈቃድ የመጠቀሚያ ፈቃድ ባለሙያ የሆነው አድምቀው ውቤ የተባለው ግለሰብ የግል ተበዳይን ጉቦ ካልከፈልክ አገልግሎት እንደማይሰጠው በመንገርና ለአንድ ወር በማጉላላት 50 ሺህ ብሩን እንዲሰጥ በማድረግ የማግባባት ስራ ሲስራ እንደነበር ፖሊስ ገልጿል።
ህብረተሰቡ መብቱን በገንዘብ መግዛት እንደሌለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መሰል የወንጀል ድርጊት ሲፈጸም ጉዳዩን በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (citizen engagement application) በመጠቀም መረጃ መስጠት እንደቻልም የከተማው ፖሊስ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 057 |
| 12 | 没有文字... | 843 |
| 13 | አዋጅ ቁጥር 1425/2018 ዓ.ም ለሙሰኞች ወሳኝ መድሃኒት ነው!
********
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 24ኛ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን ቁጥር 1425/2018 ዓ.ም መርምሮ አፅድቋል።
እንዲህ አይነት የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚወጡ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎች የሀገርን ሀብትና የሕዝብን ጥቅም ለማስጠበቅ ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይም ተጠያቂነትን በማስፈን፣ የአሰራር ግልጽነትን በመፍጠር እና የሀገርን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ የዕድገት ጉዞ በመደገፍ ረገድ ፋይዳቸው ከፍተኛ ነው።
እንዲሁም የሰውና የገንዘብ ግንኙነትን የሚቀንሱ የዲጂታል አሰራሮችን በስፋት መዘርጋት ለሙስና ቀዳዳዎችን ሁሉ ይደፍናሉ። ግልጽ የሆኑ የቴክኖሎጂ አሰራሮች መረጃን ለሕዝብ ተደራሽ ስለሚያደርጉ የተጠያቂነት ስርዓቱን ያጠናክራሉ።
ለዚህ ደግሞ ሕጉን የሚያስፈጽሙ አካላት ሙሉ በሙሉ ነፃ፣ ገለልተኛና በጠንካራ የሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ የተደራጁ መሆን አለባቸው። ሕግ ባለበት አቅምና ቁርጠኝነት ሲታከልበት ለውጡ ፈጣን ይሆናል።
ዛሬ የጸደቀው አዋጅ እቃዎችን ለመደበቅ የሚያስችል ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ሲሆን፣ ተሽከርካሪ እና ሙሉ በሙሉ የኮንትሮባንድ እቃ ጭኖ ሲጓጓዝ የተገኘ አካል ንብረቱ እንዲወረስ ደንግጓል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 022 |
| 14 | 没有文字... | 802 |
| 15 | ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ(ፒ.ኤች.ዲ) ከኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (KOIKA) የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሄዱ
************************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 02/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ(ፒ.ኤች.ዲ) ከኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (KOIKA) የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ቀጣይነት ያለው ሥራ በጋራ ለመስራት ውይይት አካሂደዋል፡፡
በውይይቱም በፀረ-ሙስና ህጎች ትግበራ፣ በተቋማት የጥቅም ግጭት መከላከል፣ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፣ በሀብት ምዝገባ መረጃ የማጣራት አፈጻጸም፣ በተቋማት ኃላፊዎች የሥነምግባር ኮድ አፈፃፀም፣ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ተመላክቷል።
የኮሪያ የሥነምግባር ግንባታና የፀረ-ሙስና ትግል ልምድ ለሀገራችን ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለውና ትግሉን በውጤታማነት ለመምራት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል፡፡
እንዲሁም ሙስናን ለመከላከል ዲጂታል አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የተጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የሀገር ውስጥ ኢንቨስትምንትን ለመሳብ አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጠርና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ እንዳለው ተገልጿል፡፡
ኮሚሽኑ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (KOIKA) በትብብር የሚሰሩ ሲሆን፣ በዚህም ለኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች በኮሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 872 |
| 16 | 没有文字... | 839 |
| 17 | ማዕከሉ የብልሹ አሰራርና የሙስና ስጋቶችን በመቅረፍ ረገድ ያለውን ሚና ከፍተኛ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
************************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 02/2018 ዓ.ም) በክልሉ ሁለተኛ የሆነው የአርባምንጭ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገልጿል።
በምረቃው የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ማዕከሉ መጀመሩ በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው ብለዋል።
«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተበታተነ መልኩና በባህላዊ አሰራር ሲሰጡ የነበሩ በርካታ የመንግስት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማስደገፍ በአንድ ጣሪያ ስር የሚያስተሳስር በመሆኑ፣ ለዘመናት ህብረተሰቡን ሲያማርሩ የነበሩ የቢሮክራሲ ማነቆዎችን ሙሉ በሙሉ እንደሚፈታ ተናግረዋል።
ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና አላስፈላጊ ወጪያቸውን እንዲቆጥቡ ያደርጋል ብለዋል።
አገልግሎቱ የመንግስትን አገልግሎት ተደራሽነትና ቀልጣፋነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የህዝብን እርካታ እንደሚያረጋግጥ ያብራሩ ሲሆን፣ ማዕከሉ የብልሹ አሰራርና የሙስና ስጋቶችን በመቅረፍ ረገድ ያለውን ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አብራርተዋል።
የ«መሶብ» ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መሠረተ ልማትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ በመሆኑ፣ የአገልግሎት ሰጪና የነዋሪዎችን ቀጥተኛ ንክኪ በመቀነስ የአገልግሎት አሰጣጡን ግልጽ፣ ተጠያቂነት የሰፈነበትና ከሙስና የጸዳ እንደሚያደርገውም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።
ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት መዘርጋቱ ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በመግለጽ፣ በማዕከሉ የሚመደቡ አመራሮችና ባለሙያዎች የህዝብ አገልጋይነት ስሜትን በተግባር ሊያሳዩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበው፤ ይህንን የተቀናጀ አሰራር በላቀ የኃላፊነት ስሜትና በታማኝነት በመምራት የክልሉን ነዋሪዎች የዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የኢፌዴሪ ሲቭል ሰርቪስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ወ/ሮ አልማዝ መሰለ ፥ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ራዕይ ከማሳካት አንጻር እስካሁን 51 የ'MESOB' አንድ ማዕከላት በ11 ክልሎችና በ2ቱ ከተማ መስተዳድሮች ተመርቀው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን፣ ዛሬ የሚመረቀው የአርባምንጭ ማዕከል ሲጨመር ቁጥሩን 52 እንደሚደርስ ገልፀዋል።
በክልሉ ከወላይታ ሶዶ ማዕከል ቀጥሎ የአርባምንጭ መሶብ 2ኛው ወደ አገልግሎት የገባ ማዕከል ሲሆን፣ ይህም ሃገራችን አገልግሎቶችን ተደራሽ እና ግልጽ ከማድረግ አንጻር አንድ ደረጃ ከፍ ያደርጋታል ነው ያሉት።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቃሬ በበኩላቸው ይህ ማዕከል የዲጂታል ሕልም ፍቺ ነው ያሉ ሲሆን፣ መንግስት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የገባውን ቃል መተግበሩን የሚያሳይ ምስክር መሆኑን አስገንዝበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አራት የፌደራል እና አምስት የክልሉ ቢሮዎች 32 አገልግሎቶች እንደሚሰጡ ገልፀው፤ ከዚህ በፊት ዜጎች የሚገጥማቸውን እንግልት በጥራትና ፍጥነት የሚሰጥ መሆኑን መገለፃቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 874 |
| 18 | 没有文字... | 792 |
| 19 | መልካም ሥነምግባርን መርህ ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ያለው አስተዋጽኦ ላቅ ያለ ነው!
*******
መልካም ሥነምግባርን መሠረት ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ ለአንድ ተቋምም ሆነ ለሀገር ዕድገት የጀርባ አጥንት ነው። ይህ መርህ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ከጅምሩ ለማጥፋት የሚኖረው አስተዋጽኦ እጅግ ላቅ ያለ ከሚሆንባቸው ምክንያቶች የሚከተሉት ተጠቃሽ ናቸው።
👉 ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል፦ የሥነምግባር መርሆዎች በሥራ ቦታ ላይ ሲሰርጹ፣ እያንዳንዱ የሕዝብ አገልጋይ ለሚሰጠው ውሳኔና አገልግሎት ኃላፊነት መውሰድን ይለምዳል። አሠራሮች ግልጽና ለሕዝብ ክፍት ሲሆኑ፣ በምስጢርና በድብቅ የሚሰሩ የሙስና እና የጥቅም ግጭት ዕድሎች ይዘጋሉ።
👉 ለአድሎዓዊ አሰራር በር ይዘጋል፦ ሙስና የሚፈጸመው "ሰውን በሰው" አሊያም ባልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ነው። መልካም ሥነ-ምግባር ደግሞ ሁሉንም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅንነት እና በፍትሃዊነት ማስተናገድን ያስገድዳል። ይህም አድሎዓዊነትን ያስቀራል።
👉 የተቋማትን ታማኝነትና የሕዝብ አመኔታን ይገነባል፦ አንድ ተቋም ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ከሙስና የፀዳ አገልግሎት ሲሰጥ፣ ተገልጋዩ ማኅበረሰብ በተቋሙ ላይ ያለው አመኔታ ይጨምራል። ይህ አመኔታ ደግሞ ሕዝቡ ራሱ የብልሹ አሠራር ተባባሪ ከመሆን ይልቅ፣ ሙስናን በጋራ የሚዋጋና የሚያጋልጥበትን ንቃተ-ሕሊና ይፈጥራል።
👉 የሀብት ብክነትን ይከላከላል፦ ሙስና እና ብልሹ አሠራር የሀገርንና የሕዝብን ውስን ሀብት ለጥቂት ግለሰቦች ፍላጎት ማሟያ ያደርጋሉ። በአንጻሩ በሥነ-ምግባር የታነጸ አገልጋይ የሕዝብን ሀብትና ንብረት እንደ ገዛ ንብረቱ በመቆጠብ፣ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ያደርጋል።
በአጠቃላይ፣ ሙስናን በሕግና በቅጣት ብቻ ማጥፋት ስለማይቻል፤ ዘላቂው መፍትሔ በየደረጃው በሚገኘው አመራርና ሠራተኛ ልብ ውስጥ መልካም ሥነ-ምግባርን እና የሐቀኝነትን ባህል መገንባት ነው።
ስለሆነም ተቋማት መልካም ሥነምግባርን መርህ ያደረገ አገልግሎት ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በመስጠት እና ሙስናና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ተቋማቸውን ውጤታማ ማድረግ ይኖረባቸዋል።
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን። | 1 022 |
| 20 | 没有文字... | 979 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
