fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 365 مشترک است و جایگاه 1 754 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 531 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 365 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 19 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 119 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 19 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 40.59% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 423 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 060 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 361
مشترکین
+1924 ساعت
+677 روز
+11930 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለሰራተኞቹና አመራሮቹ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየሰጠ ነው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና አመራሮች የአቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሰልጠና ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማ ተጀመረ። ስለጠናው በአራት የተለያዩ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሲሆን እነሱም Project management፣ Project planning and implementation፣ Good governance in public sector administration እና 4.Human resource management ናቸው፡፡ ስልጠናው እየተሰጠ የሚገኘው አሀጉር አቀፈ እውቅና ባለው East and South Africa Training Management Institute (ESAMI) እና ሌሎች የስለጠና እና ምርምር ተቋማት በጣምራ ነው። በዘርፉ የረጅም አመታት ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች በመሰጠቱ ስለጠናው የበለጠ ውጤት ተኮር ይሆናል። የስለጠናው በቨርቿል እና በአካል እየተሰጠ ይገኛል። በዛሬ እለት በቢሾፍቱ ከተማ የተጀመረው ይህ ስልጠና ተቋሙ መንግስትና ህዝብ የጣለውን አገራዊ ሀላፊነት ይበልጥ በብቃት እንዲወጣ ይረዳዋል። በስልጠናው ከ110 በላይ የተቋሙ ሰራተኞች እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን የቀሰሙትን ዕውቀት ለሌሎችም በማካፈል ስራን ለማቀላጠፍ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ኢመአ በክረምት ወራት አቅዶ እያከናወናቸው ከሚገኘው በርካታ ስራዎች አንዱ የሰራተኞቹን አቅም በተለያዩ ስልጠናዎች በማዳበር በአዲሱ የስራ አመት ውጤታማ ስራ ማከናወን ነው። ስለጠናውም እንደየ ኮርሱ ይዘትና ስፉት ከአንድ እስከ ሶስት ሳምንት የሚቆይ ይሆናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

Supply, installation, training, commissioning, integration, and maintenance support of the ITS & Toll Collection systems, and their Power supply and Communication infrastructures of the Modjo-Hawassa Highway በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST Individual Consultancy Service for the Implementation of the Livelihood Restoration Plans for the Modjo-Hawassa Expressway Project በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST Individual Consultancy Service for the Implementation of the Livelihood Restoration Plans for the Modjo-Hawassa Expressway Project

ውድ የገጻችን ተከታዮች፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከነባሩ ሚዲያ በተጨማሪ በተለያዩ የበይነ መረብ ሚዲያ አውታሮች የመንገድ አስተዳደርና ልማት መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ በያዘው ዕቅድ መሰረት
ውድ የገጻችን ተከታዮች፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከነባሩ ሚዲያ በተጨማሪ በተለያዩ የበይነ መረብ ሚዲያ አውታሮች የመንገድ አስተዳደርና ልማት መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ በያዘው ዕቅድ መሰረት እስካሁን በዌብ ፖርታልና ፌስ ቡክ መረጃዎችን ተደራሽ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡ አሁን ደግሞ ይፋዊ የቲዊተር አካውን በመክፈት ለደንበኞቻችን መረጃዎችን ተደራሽ የማድረግ ሥራ እየራን ስለሆነ የቲዊተር ገጻችን ተከታይ በመሆን ቤተሰብ እንዲሆኑ ስንጋብዛችሁ በታላቅ ደስታ ነው፡፡ ለተቀናጀ የመንገድ ልማት እና ሁለንተናዊ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ተግተን እንሰራለን!! ዘላቂና አስተማማኝ የመንገድ መሠረተ ልማት ለበለጸገች ኢትዮጵያ!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መላው ሰራተኞች እና አመራሮች ሁለተኛ ዙር የችግኘ ተከላ መርሃ-ግብር ዛሬ አከናወኑ ። የዋናው መስሪያ ቤት፤ የአለም ገና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞች እና አመራሮች ናቸው በእንጦጦ ፖርክ አካባቢ 3ሺህ ችግኞችን ዛሬ በስፍራው የተከሉት ። የበጀት አመቱን ሁለተኛ ዙር የችግኘ ተከላ መርሃ-ግብር ሁሉም በተቋሙ ስር የሚገኘው ምርምር ማዕከልን ጨምሮ ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላትም ሶስት መቶ ሺህ ችግኞችን በዛሬው ዕለት በየአካባቢያቸው ተክለዋል ። ኢመአ ባለፋት ዓመታት ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ሀላፊነቱን ይበልጥ እየተወጣ ነው ። በኢመአ የጊንጪ ማሰልጠኛ ጣቢያም የራሱን የችግኘ ማፍያ ፕሮጀክትን እውን በማድረግ ለአካባቢው ህብረተሰብ ፣ለተቋማት፣ የተለያዩ የችግኘ አይነቶችን በማበርከት ላይ ይገኛል። የተቋሙ ሰራተኞችም አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ በመሆኑና ሀገራዊ ባህል እየሆነ በመምጣቱ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ባለፉት ዓመታት በኢመአ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከ3ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። ዘንድሮም አንድ ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ የተያዘ ሲሆን ከወዲሁ በስኬት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው ኢመአ የችግኝ ተከላ-መርሃ ግብሩ ተገቢውን ሳይንሳዊ ሂደት ጠብቆ እንዲተከል፤ ከአካባቢው ስን- ምህዳር ጋር የሚጣጣሙ ሀገር በቀል ችግኞች እውን እንዲሆኑ፤ ከተተከሉም ብኋሏ የመጸደቅ ምጣኔው እንዲረጋገጥ፤ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው።

Advert.jpg8.89 MB

የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ ግንባታ
+5
የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ ግንባታ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልልን ፣ከኦሮሚያናጋምቤላ ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተሰራ ነው። የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ በመስክ የስራ ቅኝት ተጎበኝቷል ። የግንባታው አጠቃላይ አፈፃፀምም ከ35 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን፥ በቀጣይ ዓመት መጀመሪያ ወደ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ይሸጋገራል። ቀደም ብሎ ፕሮጀክቱ ከመንገድ ወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ የገጠሙትን ተግዳሮቶች፣ የነበሩበት ሲሆን የኢመአ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሥራ ተቋራጩ፣ የክልል የዞንና የወረዳ አመራር አካላት ከተለያዮ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በመቀናጀት መቅረፍ ተችሏል። አካባቢው ከፍተኛ ዝናብ የሚበዛበት በመሆኑ የስራ መቀዛቀዝ እንዳያጋጥም ፥ የሥራ ተቋራጩ ተጨማሪ ማሽነሪዎችን በማሰማራትና የድንጋይ ሙሌት ሥራ በማከናወን እየተሰራ ነው። 140 ነጥብ 2 ኪ.ሜ የሚረዝመው ፕሮጀክቱ ፥ በእስከአሁኑ የግንባታ ሥራ፤ የአፈር ጠረጋና ሙሌት፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ፣ የሰብቤዝ ንጣፍ፣ የጠጠር መፍጨት እና የነባር መንገድ ለትራፊክ ምቹ የማድረግ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። የደቡብ ኮሪያው ሃይንዳይ ዴቨሎፕመንት ካምፓኒ ግንባታውን በ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ውጪ እያከናወነ ነው። የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ሱሰንግ ኢንጅነሪንግና ዳሳን ኮንሰልታንት እንዲሁም ሀገር-በቀሉ ኔት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ በንዑስ ተቋራጭነት በጥምረት ይሰራሉ። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንግስትና በኮሪያው ኤግዚም ባንክ ወጪ ይሸፈናል። ነባሩ የጎሬ-ማሻ-ቴፒ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ባለመሆኑ ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት አሽከርካሪዎችን ለጊዜ ወጪ እና ብክነት የዳረገ ሲሆን፣ ካለው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን ከ6-8 ሰዓት የጉዞ ጊዜ በግማሽ ያሳጥረዋል። በተጨማሪም ከአዲስ አበባ በጅማ መቱ አድርጎ ጋምቤላ የሚዘልቀውን አውራ ጎዳና እና ከአዲስ አበባ በጅማ ሚዛን ቴፒ የሚሄደውን ሌላ ዋና መንገድ በአቋራጭ የሚያስተሳስር የጎላ ሚና ያለው ፕሮጀክት ነው። የኢሉአባቦር እና የሸካ ዞኖችንም በቅርበት ያቆራኛል። የመንገዱ መገንባት በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የማር፥ ቡና፥ ቅመማቅመም እንዲሁም የሻይ ተክል ምርቶች በተገቢው ፍጥነትና ጥራት ወደ መሃል ገበያ ለማድረስ ያስችላል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ከማሳለጡም ባሻገር፣ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማሕበራዊ አገልግሎት ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል። በሥፍራው የሚገኘውን ሰፊ የቱሪዝም ሃብት የሚነቃቃበትን ምቹ ዕድልም ይፈጥራል።የመንገዱ የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በዞን ከተማ 21 ነጥብ 5 ሜትር፣ በወረዳ 19 ሜትር እና በገጠር 10 ሜትር ነው።

የሀገራችንን የቀጣይ የመሰረተ ልማት ዕድገት ታሳቢ ያደረገ ዘርፉ የሚመራበትን ግልፅ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ እረቂቅ ፖሊሲ ላይ ምክክር ተካሄደ ። በሂልተን ሆቴል በተዘጋጀው የመንገድ ፖሊሲ እና የመንገድ አዋጅ እረቂቅ ሰነዶች ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፣ከሁለቱም ምክር ቤቶች ፣ ከክልል ባለድርሻ አካላት ፣ከተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ፥እንዲሁም ከልዩ ልዩ ተቋማት የተወጣጡ ተሳታፊዎች ታድመዋል ። በዚሁ መድረክ ላይ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እረቂቅ ፖሊሲው ከመንገድ ዘርፍ ጋር ተያይዞ ቀጣይ አገራዊ ግብን ታሳቢ አድርጎ የሚነሱ ችግሮችን የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡ በዘርፉ ያሉ ውስብስብ ችግሮችን መፍታት በቀጣይ የሚኖረውን እድገት ታሳቢ አድርጎ የባለድርሻ አካላትን ሚና እና ሀላፊነትን በግልጽ ማስቀመጥ ፥ ላይ ፖሊሲው በዝርዝር ማመላከቱን ሚኒስትሯ አብራርተዋል ። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ የዘርፉን እድገት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር የሚያስችል ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል ። ሀገራዊ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች የሚሰተናገዱበትን አግባብ ፣ የተፈጠረውን ኃብት በአግባቡ የመጠበቅ ፣ የአገር ውስጥ የስራ ተቋራጮች እና አማካሪዎች አቅም በሚፈለገው መልኩ ከማሳደግ አኳያ ሰነዱ የጎላ ሚናን እንደሚያበረክት ተናግረዋል ። ክልሎች በመንገድ ዘርፍ ልማቱ ላይ ያላቸውን ሚና እና ሀላፊነት ማሳደግ ላይም የላቀ አበርክቶት እንዳለው ገልጸዋል ። የወሰን ማስከበር ፣ የግብዓት ችግሮች እና ሌሎችንም የዘርፉን ባለድርሻ አካላት ተሳትፍና ማነቆዎች ለመፍታት ፖሊሲው በላቀ ደረጃ ያግዛል ብለዋል፡፡ የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ዘርፉ የሚመራበትን ግልጽና አቅጣጫ ቀጣይ ግብና ተልዕኮን በግልጽ ያመላከተ ሀገራዊ ሰነድ መዘጋጀቱን አድንቀዋል ። በረቂቅ ፖሊሲውና በህግ ሰነዱ ላይ ቢካተቱ ያሏቸውን የማዳበሪያ ምክረ ሀሳቦችንም አክለዋል ።

የኢትዮጵያ - ጁቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር አካል የሆነው የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ- ኪ.ሜ 60 የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም የግንባታ ሂደት ላይ ነው ። አጠቃላይ የፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ በመስክ የስራ ቅኝት ተጎበኘቷል ። ፕሮጀክቱ 60 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ከ11 ወራት በፊት ነበር በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የተጀመረው ። መንገዱ የሚገነባው ከ6 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ ሲሆን በጀቱ የሚሸፈነው በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግሥት ነው። ፕሮጀክቱ የገቢ እና ወጪ ንግድን በማሳለጥ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ፋይዳው የጎላ ነው። ግንባታውን እያከናወኑ የሚገኙት ጂ. ኤም. ሲ. እና ኤል. አር. ቢ. ሲ. ኤል. የተሰኙ ዓለም አቀፍ ተቋራጮች በጋራ ነው ። በ ጂ. ኤም. ሲ. የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሱባረዲ ባሲረዲ እንደተናገሩት፤ ድርጅቱ መንገዱን በ4 ዓመት ተኩል ለማጠናቀቅ የሚያስችል በርካታ ስራዎች ከወዲሁ እያከናወነ ነው ። ድርጅቱ ግንባታውን ከተያዘው ጊዜ አስቀድሞ በመጨረስ ለማስረከብ ለግንባታው የሚያስፈልጉትን ባለሙያዎችና መሳሪያዎች በማሟላት ሥራ መጀመሩን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። የካምፕ ግንባታ የስትራክቸር ስራዎች የዲዛይንና መሰል ተግባራትን በተቀመጠው እቅድ መሰረት ለማከናውን ተችሏል ። ይሁን እንጂ የወሰን ማስከበር ችግሮች ግንባታው በሚፈለገው ፍጥነት ለማስኬድ ጫና እያሳደረ ነው። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የወሰን ማስከበር ችግር ካለበት ውስጥ 18 ኪሎ ሜትር ቦታ ነጻ በማድረግ ማስረከብ የቻለ ሲሆን ቀሪ ቦታዎችን ለግንባታው ነጻ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው። ፕሮጀክቱ ካለው ሀገራዊ ፋይዳ አኳያ ቀሪ ቦታዎቹን ነጻ በማድረግ ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ ርብርብ እንዲያደረጉም ኢመአ ጠይቋል ። ለግንባታው የሚውል ሲሚንቶ በሚፈለገው መጠን አለመገኘት ሌላው ትልቅ ፈተና መሆኑን ተቋራጮቹ ጠቁመው፤ ኢመአ አቅርቦቱ በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው። የግንባታው ተቆጣጣሪ መሃንዲስ ኢንጂነር ራጁማ ቱር በበኩላቸው፤ የግንባታው ጥራት አስተማማኝ እንዲሆን በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ለግንባታው ጥቅም ላይ የዋሉት መሳሪያዎች የመንገዱን ጥራት ለማረጋገጥ የሚረዱ መሆኑንም በመጠቆም ግንባታውን በከፍተኛ ኃላፊነት እያካሄድን ነው ብለዋል። የምዕራፍ አንድ አዳማ -አዋሽ ኮንትራት አንድ አዳማ - ኪ.ሜ 60 የፍጥነት መንገድ 34 ሜትር ስፋት አለው ፡፡ እያንዳንዱ የተሸከርካሪ መጓጓዣ መስመር 3.6 ሜትር ስፋትና 9 ሜትር ሜዲያን (የመንገድ አካፋይ) ያካተተ ነው :: የመንገድ አካፋዩ በዚህ ደረጃ እንዲሰፋ የተደረገው በተቃራኒ አቅጣጫ ያለን ተሸከርካሪን በመለየት አደጋን ለማስወገድ አልያም ለመቀንስ ነው፡፡ የ መንገዱ ትከሻ ስፋት ከ1.5 ሜትር እስከ 3 ሜትር ነው፡፡ አራት መኪኖችን በአንድ ጊዜ በግራና በቀኝ በኩል ያስተናግዳል፡፡ የፍጥነት መንገዱ ሲገነባ ከእንስሳት እና ከሰዎች እንቅስቃሴ ነጻ በመሆኑ ለአሽከርካሪ ፍጹም ምቹ የማሽከርከር እድል እና ነጻነትን የሚያድል ከመሆኑም ባለፈ በነባሩ መንገድ በተደጋጋሚ የንጹሃን ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለውን እና የንብረት ውድመት እያስከተለ የመጣውን የትራፊክ አደጋ በመቀነስ ረገድ ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው ፡፡ እስካሁን ፕሮጀክቱ መሃንዲሶችን፣ ኦፕሬተሮችን፣ ሾፌሮችንና የጉልበት ሠራተኞችን ጨምሮ ከ 550 በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ እድል ፈጥሯል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና አመራሮች በእንጦጦ ፖርክ አካባቢ የመጀመሪያ ዙር የችግኘ ተከላ መርሃ-ግብር አከናወኑ ። የዋናው መስሪያ ቤት፤ የአለም ገና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞች እና አመራሮች ናቸው በጋራ በመሆን 2ሺህ ችግኞችን በስፍራው የተከሉት ። በተቋሙ ስር የሚገኘው ምርምር ማዕከልን ጨምሮ ሁሉም ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላትም ችግኞችን በየአካባቢያቸው መትከል ጀምረዋል። ኢመአ ባለፋት ዓመታት ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ሀላፊነቱን ይበልጥ እየተወጣ ነው ። በኢመአ የጊንጪ ማሰልጠኛ ጣቢያም የራሱን የችግኘ ማፍያ ፕሮጀክትን እውን በማድረግ ለአካባቢው ህብረተሰብ ፣ለተቋማት፣ የተለያዩ የችግኘ አይነቶችን በማበርከት ላይ ይገኛል። የተቋሙ ሰራተኞችም አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ በመሆኑና ሀገራዊ ባህል እየሆነ በመምጣቱ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ባለፉት ዓመታት በኢመአ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከ3ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። ዘንድሮም አንድ ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ የተያዘ ሲሆን ከወዲሁ በስኬት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው ኢመአ የችግኝ ተከላ-መርሃ ግብሩ ተገቢውን ሳይንሳዊ ሂደት ጠብቆ እንዲተከል፤ ከአካባቢው ስን- ምህዳር ጋር የሚጣጣሙ ሀገር በቀል ችግኞች እውን እንዲሆኑ፤ ከተተከሉም ብኋሏ የመጸደቅ ምጣኔው እንዲረጋገጥ፤ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው።

የኦሞራቴ - ኦሞ ድልድይ - ኛንጋቶም- ካንጋተን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+7
የኦሞራቴ - ኦሞ ድልድይ - ኛንጋቶም- ካንጋተን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

64 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የኦሞራቴ - ኦሞ ድልድይ - ኛንጋቶም- ካንጋተን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። በደቡብ ክልል ግንባታው እየተከናወን በሚገኘው በዚሁ ስፍራ የመስክ የስራ ቅኝት ተካሂዷል ። በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል። ከነዚህም መካከል የምንጣሮ፣ የልል አፈር ቁፋሮ፣ የአፈር ሙሌት፣ በርካታ የእሰትራክቸር ስራዎችም ተሰርተዋል ። የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ሌየር የአስፋልት ስራዎችም ተጠናቀዋል። የዋና አስፋልት የሙከራ ስራም ተጠናቆ የአስፋልት ኮንክሪት ስራው በጅምር ላይ እንደሚገኝ ተመልክቷል። ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ኦሞራቴ ከተማ ላይ ጀምሮ ካንጋታን ከተማ ላይ የሚያበቃ ነው። መንገዱ በገጠር 10ሜ፣ በከተማ 19ሜ እና በወረዳ 19ሜ ስፋት ያለው ሆኖ እየተገነባ ነው። ግንባታው የሚከናወነው በ "NKH ኮንስትራክሽን ፒኤልሲ‘’ ሲሆን የማማከር ስራውን የሚያከናው ነው ደግሞ ክላስኪ ኮንሰልቲንግ አማካሪ ድርጅት ነው። ለመንገዱ ግንባታ የተበጀተው ብር 965,890,930,37 ሲሆን ወጪው ሙሉ በሙሉ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። የመንገድ ግንባታው መጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት ሲሆን ፤ ከነዚህም ቀደም ሲል የነበረውን የጉዞ እርዝማኔ በ2 ሰአት ይቀንሳል፣ በአካባቢው የሚገኘውን ከፊል አርብቶ አደርና ከፊል አርሶ አደር ማህበረሰብን መሰረታዊ ፍላጎት ተደራሽ ያደርጋል፣ በአከባቢው የሚገኘውን ዕምቅ የግብርና አቅም ተደራሽ ከማድረግም ባሻገር በአካባቢው የሚገኙ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ተደራሽ ከማድረግ አኳያም የሚኖረው ፋይዳ እጅግ የላቀ ነው።