fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 365 مشترک است و جایگاه 1 754 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 531 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 365 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 19 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 119 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 19 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 40.59% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 423 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 060 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 361
مشترکین
+1924 ساعت
+677 روز
+11930 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጽያ መንገዶች አስተዳደር ለአብርሆት ቤተ-መፅሐፍ ከ1000 በላይ መፅሐፍትን አበረከተ፡፡ ሚሊዮን መፅሐፍት ለሚሊኒየሙ ትዉልድ በሚል መሪ ቃል በቅርቡ በሀገር ደረጃ ይፋ በተደረዉ የመጽሐፍ ማሰባ
+4
የኢትዮጽያ መንገዶች አስተዳደር ለአብርሆት ቤተ-መፅሐፍ ከ1000 በላይ መፅሐፍትን አበረከተ፡፡ ሚሊዮን መፅሐፍት ለሚሊኒየሙ ትዉልድ በሚል መሪ ቃል በቅርቡ በሀገር ደረጃ ይፋ በተደረዉ የመጽሐፍ ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ኢመአ በቀጣይ ትዉልድ ላይ የበኩሉን አሻራ አሳርፏል፡፡ በዛሬዉ የርክክብ መርሃ-ግብር ላይ የኢትዮጽያ መንገዶች አስተዳደር የስራ ሃላፊዎች፤ የጠቅላይ ሚንስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ የሆኑት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተገኙበት አስረክበዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮርፖሬት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክትር አቶ ሲሳይ በቀለ ኢመአ ሀገራዊ ጥሪዉን ተከትሎ ባደረገዉ ተሳትፎ ደስታቸዉን ገልጸዋል፡፡ “በዛሬዉ ዕለት መስሪያ ቤታችን በምህንድስና እና የተለያዩ ዘርፍ ላይ ያተኮሩ መፅሐፍት በማበርከቱ በዘርፉ ላይ ተጨማሪ ጥናት እና ምርመር ለሚያደርጉ ተማሪዎች የበለጠ እንደሚያግዛቸዉ ጠቁመዋል፡፡” ከአሁን በኋላም ኢመአ ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልፀዋል። የጠቅላይ ሚንስተሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ የሆኑት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በበኩላቸዉ “ ኢመአ ያበረከታቸዉ መፅሐፍት ውድና ጠቃሚ ይዘት ያላቸዉ ስለሆኑ በአዲሱ ትዉልድ ስም አመሰግነዋል፡፡” መፅሐፍቶቹ እጅግ በጣም ጠቃሚና ትምህርታዊ ይዘት ያላቸዉም ናቸዉ፡፡ በስብስቡ የተለያዩ የምህንድስና እና የመንገድ ምርምር ላይ የተፃፉ የምርምር ይዘት ያላቸዉም መጽሐፍት ተካተዉበታል፡፡

የቡሬ - ጎመር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+7
የቡሬ - ጎመር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የቡሬ - ጎመር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታን በተገቢው የጥራት ደረጃ በፍጥነት ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን አጠቃላይ ርዝመቱም 43 ኪሎ ሜትር ነው። አካባቢው ከፍተኛ የሆነ የቅይጥ ግብርና እና የእንስሳት እርባታ የሚከናወንበት በመሆኑ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለአካባቢው አርሶና አርብቶ አደር ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ይኖረዋል። መንግስት ይህን እና ተጨማሪ የመንገዱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በመገንዘብ ለመንገዱ የሚያስፈልገውን ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በመመደብ ግንባታው እንዲካሄድ እያደረገ ይገኛል። ለግንባታዉ የሚውለው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን አንድ ቢሊዮን ሶስት መቶ ስልሳ አምስት ሚሊዮን ብር ነው። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ትከሻን ጨምሮ በከተማ 21.5 ሜትር እና በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው። አጠቃላይ ስራውን በሶስት ዓመታት ዉስጥ ለማጠናቀቅ ከአስተዳደር መስሪያ ቤቱ ጋር ተዋውሎ ወደ ግንባታ ስራ የገባው ሜድሮክ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግል/ካምፓኒ የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ እያከናወነ ይገኛል። የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ሰምረዲን አዳነ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት አጋማሽ የተጀመረ መሆኑን በመግለፅ ፣ በአሁኑ ወቅት የካምፕ ግንባታ ስራው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝና የአፈር ቆረጣ ፣ ሙሌት እና የስትራክቸር ስራዎችንም በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የአማካሪ ድርጅቱ የፕሮጀክት ተጠሪ መሀንዲስ ኢንጅነር ዘገየ ጠና በበኩላቸው መንገዱን ከተያዘለት የጊዜ ገደብ ቀድሞ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ ጥራት የማንደራደርበት ጉዳይ በመሆኑ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጥራት መስፈርት መሰረት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ስራችንን በተደራጀ ላቭራቶሪ አስደግፈን ነው እየተንቀሳቀስን ያለው ብለዋል። ፕሮጀክቱ ከ300 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድልን ስለመፍጠሩና እነዚህ ሰራተኞች ከስራ ዕድል ተጠቃሚነታቸው ባሻገር ከፍተኛ የሆነ ሙያዊ ልምድ እየቀሰሙ ስለመሆኑ አክለው ገልፀዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን የወንበርማ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አስማረ መኮንን በበኩላቸው መንገዱ የሚያልፍበትን ቦታ ከ3ኛ ወገን ነፃ በማድረግ ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በአካባቢው ከቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክን በተጨማሪ ሌሎች ግዙፍ የግል ኢንዱስትሪዎችም ይገኛሉ። መንገዱ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ በቆሎ ፣ ስንዴ፣ በርበሬ፣ ሰሊጥና መሰል የአዝርዕት ውጤቶችን እና ማንጎ፣ ሙዝ እና ሌሎች የፍራፍሬ ምርቶች ሳይበላሹ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እና በአካባቢው ወደሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ዞኖች በጥራትና በፍጥነት ለማድረስ ያስችላል። 43 ኪሎሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው ይህ መንገድ በአሁኑ ወቅት ከሁለት ሰዓት ያላነሰ የትራንስፖርት ጉዞን ይጠይቃል። ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ይህን የጉዞ ጊዜ መጠን ወደ 45 ደቂቃ ዝቅ ያደርጋል ተብሎ ይታመናል።

የሳንሱሲ -ታጠቅ-ኬላ
+7
የሳንሱሲ -ታጠቅ-ኬላ

የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የመንገድ ግንባታ ስራ ተጠናቀቀ፡ በፕሮጀከቱ ስፍራ በተካሄደው የመስክ ምልከታ የመንገዱ የግንባታ ክፍል ተጠናቆ ሙሉ መስመሩ ለትራንስፖርት ክፍት ተደርጓል። ይህን ተከትሎም በስፍራው ያነጋገርናቸው የመንገዱ ተጠቃሚዎች፥ አሽከርካሪዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ፥ለፕሮጀክቱ በተደረገው ክፍተኛ የግንባታ ትኩረት መንገዱ ተጠናቆ ክፍት በመደረጉ ፤ አመቺ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ማሳለጥ መቻሉን ተናግረዋል ። የግንባታው አካል የሆነው የእግረኛ መንገድ፣ የትራፊክ ምልክት ተከላ ፥የመንገድ አካፋይ አረንጓዴ ልማት ስራን ጨምሮ ጥቃቅን ስራዎችም እየተጠናቀቁ ነው። 16 ሜትር ርዝመት ያለው የገፈርሳ ወንዝ ድልድይ የዚሁ ፕሮጀክት አካል ሲሆን የውሃ ፍሰቱን ታሳቢ ተደረጎ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ተገንብቷል ። የሳንሱሲ- ታጠቅ - ኬላ 13.54 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የተገነባው። የግንባታው መዋለ-ንዋይ 825,067,522.68 ሚሊዮን ብር ሲሆን ሙሉ ወጪው የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ ግንባታውን ያከናወነው ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ አሰር ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው። ፎርተረስ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልቲንግ ከ አሶሼትስ ጋራ በጣምራ የግንባታ ስራውን በአማካሪነት ከውነውታል ፡፡ የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የቀድሞ የመንገድ ገፅታ ከ7 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋትና በአገልግሎት ብዛት ሳብያ ለከፍተኛ ጉዳት ተዳርጎ የነበረ ነው። መስመሩ ከሚያሰተናግደው የተሸከርካሪ ብዛትና የትራፊክ መጨናነቅ አኳያ ፤እንዲሁም የሚያስተሳስራቸውን ከተማዎች ቀጣይ እድገት ታሳቢ በማድረግ መነሻ ስፋቱ በከፍተኛ ደረጃ እንዲሻሻል ተደርጎ ነው የተገነባው፡፡ በዚህም በአማካይ ከ20 እስከ 32 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደረጓል ፡፡ መንገዱ በዚህ ደረጃ መስፋቱ በግራና ቀኝ 6 ተሸከርካሪዎችን ማስተናገድ ያስችለዋል፡፡ በተጨማሪም በውስጡ የመንገድ አካፋይ ፣ የእግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ነው ፡፡ የመንገዱ ዕውን መሆን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ይከሰት የነበረውን መጉላላት በማስቀረት የተሳለጠ እንዲሆን አስችሏል። የቡራዩ ከተማን ከአዲስ አበባ ጋር በማስተሳሰር እንደ ሳንሱሲ፣ታጠቅና ኬላ አካባቢ ያሉ ብዛት ያላቸው ነዋሪዎች እና የማምረቻ ተቋማት አመቺ እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተጠቃሚ አድርጓቸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የምዕራብ የሀገራችን ክፍል የወጪ ገቢ ንግድ ኮሪደር የሆነውን፤ ከአዲስ አበባ - አምቦ - ነቀምት - አሶሳ ያለው ዋና መንገድ በአሸዋ ሜዳ ታጠቅ በኩል ይጠቀሙ የነበሩትን ብዛት ያላቸው ተሸከርካሪዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን መጨናናቅ ፤ አማራጭ በመፍጠር እና የነበረውን ችግር በመቅረፍ የሳንሱሲ - ታጠቅ - ኬላ መንገድ የጎላ ፍይዳን አበርክቷል፡፡

የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ
+7
የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ

የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የመንገድ ግንባታ ስራ ተጠናቀቀ፡ በፕሮጀከቱ ስፍራ በተካሄደው የመስክ ምልከታ የመንገዱ የግንባታ ክፍል ተጠናቆ ሙሉ መስመሩ ለትራንስፖርት ክፍት ተደርጓል። በስፍራው ያነጋገርናቸው የመንገዱ ተጠቃሚዎች ፤ አሽከርካሪዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም የክርምቱን መምጣት ተከትሎ በተደረገው ክፍተኛ የግንባታ ትኩረት መንገዱ ተጠናቆ ክፍት በመደረጉ መቹ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን ማሳለጥ መቻሉን ተናግረዋል ። የመንገዱ አሁናዊ የግንባታ አፈፃፀሙ 97 ነጥብ 3 በመቶ የደረሰ ሲሆን አስፋልት ንጣፍ ስራውም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለትራፊኮ ክፍት ሆኖል። የግንባታው አካል የሆነው የእግረኛ መንገድ፣ የትራፉክ ምልክት ተከላ የመንገድ አካፋይ አርንጓዴ ልማት ስራን ጨምሮ ጥቃቅን ስራዎችም እየተጠናቀቁ ነው። 16 ሜትር ርዝመት ያለው የገፈርሳ ወንዝ ድልድይ የዚህው ፕሮጀክት አካል ሲሆን የውሃ ፍሰቱን ታሳቢ ተደረጎ ደረጃውን በጠበቀ መለኩ ተገንብቷል ። የሳንሱሲ- ታጠቅ - ኬላ 13.54 ኪ.ሜ ሲሆን መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የተገነባው። የግንባታው መዋለ-ንዋይ 825,067,522.68 ሚሊዮን ብር ሲሆን ሙሊ ወጪው የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ ግንባታውን ያከናወነው ሀገር በቀሉ ተቋራጩ አሰር ኮንስትራክሽን ድርጅት ነው። ፎርተረስ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልቲንግ ከ አሶሼትስ ጋራ በጣምራ የግንባታ ስራውን በአማካሪነት ከውነውታል ፡፡ የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የቀድሞ መንገድ ገፅታ ከ7 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋትና በአገልግሎት ብዛት ሳብያ ለከፍተኛ ጉዳት ተዳርጎ የነበረ ነው። መስመሩ ከሚያሰተናገደው የተሸከርካሪ ብዛትና የትራፊክ መጨናነቅ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ አድገት መነሻ ስፋቱ እንዲጨመር ተደርጎ ነው የተገነባው፡፡ በአማካይ ከ20እስከ 32 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደረጓል ፡፡ መንገዱ በዚህ ደረጃ መስፋቱ በግራና ቀኝ 6 ተሸከርካሪዎችን ማስተናገድ ያስችለዋል፡፡ በተጨማሪም በውስጡ የመንገድ አካፋይ ፣ የእግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ነው ፡፡ የመንገዱ ዕውን መሆን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ይከሰት የነበረውን መጉላላት በማስቀረት የተሳለጠ እንዲሆን አስችሏል። የቡራዩ ከተማን ከአዲስ አበባ ጋር በማስተሳሰር እንደ ሳንሱሲ፣ታጠቅና ኬላ አካባቢ ያሉ ብዛት ያላቸው ነዋሪዎችም አመቺ እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተጠቃሚ አድርጓቸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የምዕራብ የሀገራችን ክፍል የወጪ ገቢ ንግድ ኮሪደር የሆነውን ከአዲስ አበባ - አምቦ - ነቀምት - አሶሳ ያለው ዋና መንገድ በአሸዋ ሜዳ ታጠቅ በኩል ይጠቀሙ የነበሩትን ብዛት ያላቸው ተሸከርካሪዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን መጨናናቅ ፤ አማራጭ በመፍጠር እና የነበረውን ችግር በመቅረፍ የሳንሱሲ - ታጠቅ - ኬላ መንገድ ሁነኛ አማራጭ ሆኖም እያገለገለ ነው ፡፡

#FANA_TV የመንገድ መሰረተ ልማት ሥራዎች በጋምቤላ ክልል

በጋምቤላ ክልል እየተከናወኑ ከሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል የጋምቤላ- አቦቦ -ፑኚዶ መንገድ ግንባታ በአካባቢው የሚገኙ ሰፋፊ እርሻ ልማትና የአሳ ሃብትን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያበረክተው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑ ተነግሯል። ከዚህ ባሻገር የመንገድ ግንባታው ህብረተሰቡ የነበረበትን የትራንስፖርት እጥረት ከመቅረፍ በተጨማሪ ለተለያዩ መሰረተ ልማት ዝርጋታዎች በር የሚከፍት መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሙሉ ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት እየተገነባ የሚገኘው የመንገድ ፕሮጀክትአሁን ላይ የግንባታ ሂደቱ ከ50 በመቶ በላይ መድረሱን ግንባታውን የሚያከናውነው የቻይናው ሬልዌይ ቲዌኒ ፈርስት ግሩፕ አስታውቋል። በስፍራው ቅኝት ያደረገው ባልደረባችን ዓለምሰገድ አሳዬ ተጨማሪ አለው። https://www.youtube.com/watch?v=vXsI-Tsg3ko

የሶዶ-ዲንኬ-ሳውላ የመንገድ ፕሮጀክት
+8
የሶዶ-ዲንኬ-ሳውላ የመንገድ ፕሮጀክት

የማዜ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ የሆነውና በሁለት ኮንትራት ተከፍሎ በመገንባት ላይ የሚገኘው የሶዶ-ዲንኬ-ሳውላ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመስክ ስራ ቅኝት ተጎብኝቷል፡፡ የዚህ መንገድ የመጀመሪያ ሎት የሶዶ-ዲንኬ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 86.22 ኪሎሜትር ርዝመትን ይሸፍናል። የዚህ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የእስካሁን አፈፃፀም 72 በመቶ ስለመድረሱ በመስክ ቅኝታችን ወቅት ተመልክተናል፡፡ የመንገድ ግንባታው ቻይና ሬልዌይ ሰቭንዝ ግሩፕ በተባለ የቻይና ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ፣ የሱዳኑ ኒውቴክ ኮንሰልቲንግ ከሀገር በቀሉ ኔት ኮንሰልቲንግ ጋር በጋራ በመሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለመንግዱ ግንባታ ወጪ የሚሆነው 1,054,003,610.30 ብር ሲሆን ፣ የዚህ ግንባታ ሙሉ ወጪም በአፍሪካ ልማት ባንክ የተሸፈነ ነው፡፡ የዚህ መንገድ ቀጣይ ክፍል የሆነው ኮንትራት ሁለት የዲንኬ-ሳውላ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አጠቃላይ ርዝመቱ76 ኪሎሜትር ነው። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የወሰን ማስከበር ችግር ከሚታይባቸው የአካባቢው አንዳንድ ከተሞች ውጪ በመልካም እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ ይህን ችግር ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በጋራ በመቅረፍ ፕሮጀክቱን በሚጠበቀው ደረጃ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የሚጠበቅብንን ሃላፊነት እንወጣለን ሲሉ የሜላና ከተማ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ዳዊት አስፋው ገልፀዋል፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ ቤጂንግ አርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ ካምፓኒ በተባለ ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራው ደግሞ ሶሱንግ ኢንጅነሪንግ ኃላ/የተ/የግ/ማ ፣ ኮሪያ ኮንሰልታንትስ ኢንተርናሽናልኃላ/የተ/የግ/ማ ፣ ዳሳን ኮንሰልታንትስ ኃላ/የተ/የግ/ማ እና ኔት ኮንሰልትስ ኃላ/የተ/የግ/ማ በተባሉ አማካሪ ድርጅቶች አማካኝነት በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ወጪ የሚሆነው 1,020,177,271.11 ብር ሲሆን ፣ የዚህ ግንባታ ሙሉ ወጪም በአፍሪካ ልማት ባንክ የተሸፈነ ነው፡፡ የሁለቱ ፕሮጀክት የስራ ተቋራጮች በአሁኑ ወቅት የስትራክቸር ፣ የአፈር ሙሊት ፣ የማፋሰሻ እና የቤዝ ኮርስ ስራዎችን ከማከናወን አልፈው የአስፋልት ንጣፍ ስራ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። የትራንስፓርት አገልግሎቱ እንዳይስተጓጎል ነባር ድልድዮችን የማጠናከር እንዲሁም የፕሮጀክቱ አካል የሆኑ አዳዲስ ድልድዮች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑንም በመስክ ቅኝታችን ወቅት ተመልክተናል። ግንባታው የቦታውን እምቅ የተፈጥሮ ፀጋዎች ለመጠበቅ በሚያስችል እንዲሁም የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ መርሆችን በተከተለ መልኩ በጥንቃቄ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ እነዚህ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ወደ ኦሞ ኩራዝ የስኳር ፋብሪካ ለሚደረጉ ጉዞዎች አማራጭ መንገድ በመሆን ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ አካባቢው የቅይጥ ግብርና እና የእንስሳት እርባታ የሚከናወንበት በመሆኑ መንገዶቹ ተገንብተው ሲጠናቀቁ እነዚህን የግብርና ውጤቶች ሳይበላሹ በጥራትና በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላሉ። በተጨማሪም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎንኝዎች ወደ ማዜ ብሔራዊ ፓርክ የሚያደርጉትን ጉዞ በማቀላጠፍ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት ይጨምራል፡፡ ከዚህም ባሻገር መንገዱ ከዚህ ቀደም ለትራንስፖርት እጅግ አስቸጋሪ የነበረ በመሆኑ በሰው እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ይደርስ የነበረ ስለመሆኑ በመስክ ቅኝታችን ወቅት ያነጋገርናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች የገለፁልን ሲሆን ፣ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለነዋሪዎቹ ትልቅ እፎይታን ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል።

የወይጦ-ቱርሚ 120 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት
+4
የወይጦ-ቱርሚ 120 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት

በደቡብ ክልል ኦሞ ዞን ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የወይጦ-ቱርሚ 120 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ በእስካሁኑ የሥራ እንቅስቃሴ የጠረጋ ሥራ፣ የቆረጣ ሥራ፣ የሰቤዝ እና የቤዝኮርስ ሥራ፣ የአፈር ሙሌት፣ ሥራ እና የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ የሰባት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ የተካተተ ሲሆን÷ አሁን ላይ የዲዛይን ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ግንባታውን ራማ ኮንስትራክሽን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ፕሮሜ ኮንሰልቲንግ እና ኦሜጋ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ በጥምረት እየሰሩ ነው፡፡ ለግንባታው የሚያስፈልገው 2,843,185,710 ብር ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል፡፡ የወይጦ-ቱርሚ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን ሶስት ሰዓት ተኩል የጉዞ ጊዜ በአንድ ሰዓት ተኩል የሚያሳጥር ሲሆን÷ በዋናነት የወይጦ፣ አልቦሬ እና ቱርሚ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ያገናኛል፡፡ በፕሮጀክቱ ክልል ስር የሚገኙ አነስተኛ የገጠር ቀበሌዎች ወደ ከተማነት የሚያድጉበትን ምቹ እድል ይፈጥራል፡፡ በተጨማሪም ሥፍራው የኩራዝ ስኳር ፋብሪካ፣ የኦሞ ሸለቆ አርኪኦሎጂካል ሳይት እንዲሁም በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ብሔረሰቦች ባህላዊ እና ቁሳዊ የቱሪስት መስህቦች (በተለይም የሐመር ብሔረሰብ) መዳረሻ እንደመሆኑ ፋይዳው ከፍተኛ ነው፡፡ የኦሞ ወንዝን ተከትለው በሚገኙ ሰፋፊ የእርሻ ቦታዎች የሚመረቱ የተለያዩ የፍራፍሬ ምርቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በጥራትና ፍጥነት በማድረስ በኩል ጉልህ አስተዋፅኦ አለው፡፡ ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ ያለ እና በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተጎዳ ነው፡፡ እሁን ላይ መንገዱ ካለው ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ሲሆን÷ በገጠር 10 ሜትር እንዲሁም በከተማ 21.5 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል፡፡

56.5 ኪ.ሜ የሚረዝምው የአሊ ከተማ-ዋቤ ድልድይ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በጥሩ የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ በቅርቡ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ የጀመረ ሲሆን አሁን ላይ የ8 ኪ.ሜ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪ ከመንገዱ የግንባታ ሥራ መካከልም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦዎች ሥራ፣እንዲሁም የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል፡፡ የሶስት ድልድዮች ግንባታ ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን የአንድ ድልድይ ግንባታ በቅርቡ ይጠናቀቃል፡፡ በተደረገው የመስክ ቅኝትም ፕሮጀክቱ አሁናዊ አፈፃፀሙ ከ79 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን ይህም ከእቅዱ ጋር በሚጣጣም መልኩ እየተከናወነ መሆኑ ተገምግሟል፡፡ ቀሪ የግንባታ ሥራውን አከናውኖ በሚቀጥለው በጀት ዓመት አጋማሽ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም-አቀፉ የሥራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ነው፡፡ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ሆንግ አይኬ ከልደት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በጥምረት እየሰሩ ይገኛል፡፡ ለግንባታው የሚውለው 2,153, 060, 671 (ሁለት ቢሊዮን አንድ መቶ ሃምሳ ሶስት ሚሊዮን ስልሳ ሺህ ስድስት መቶ ሰባ አንድ ብር) ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 427 ኪ.ሜ ርቀት አሊ ከተማ ላይ ጀምሮ ዋቤ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ በዋናነት ሮቤ፣ አሊ እና ዋቤ ከተሞችን በቅርበት ያገናኛል፡፡ ቀደም ሲል ከፊሉ መስመር በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ ሲሆን ቀሪው ክፍል ምንም አይነት መንገድ አልነበረውም፡፡ መንገዱ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የማሕበራዊ አገልግሎቶችን የጤና የትምህርት እና የባህል ልውውጡን በእጅጉ ያሳድጋል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረተውን ስንዴ፣ ገብስ እና የፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ምርቶችን በስፋት እና በጥራት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የአርሶ-አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ይጨምራል፡፡ የቱሪዝም መዳረሻ የሆኑትን የሶፍ ዑመር ዋሻ የሳነቴ ተራራ እና የዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ለጎብኝዎች ምቹ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ የፕሮጀክቱ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የዋቤ ድልድይ-አርሲ ሮቤ ክፍል-2 አስፋልት ኮንክሪት መንገድ፥ ግንባታውን ለማስጀመር የሚረዱ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በቅርቡም ወደ ግንባታ ሥራ ይሸጋገራል።

የሙከጡሪ - ኮከብ መስክ እና ኮከብ መስክ - አለም ከተማ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች
+8
የሙከጡሪ - ኮከብ መስክ እና ኮከብ መስክ - አለም ከተማ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች

የኦሮሚያ ክልልን ከአማራ ክልል ጋር በመንገድ መሰረተ ልማት የሚያስተሳስሩት የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ እና ኮከብ መስክ-አለም ከተማ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች በመስክ የስራ ቅኝት ተጎበኙ ። ለመንገዶቹ የግንባታ ስራ አመቺነት ሲባል በሁለት ኮንትራት ተከፍሎ እየተሰራ ሲሆን ኮንትራት አንድ የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ እና ኮንትራንት ሁለት ኮከብ መስክ-አለም ከተማን ያካልላል ፡፡ ሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በያዝነው በጅት አመት መጨረሻ ድርስ ዋና ዋና ስራዎቹን ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ በመስክ ቅኝቱ ተመላክቷል። አሁን ላይ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም 80 በመቶ ላይ ደርሷል። 59 ኪ.ሜ የሚረዝመው ይህ ፕሮጀክት 40 ኪ.ሜ የሚሆን የአስፓልት ንጣፍ ስራው ተጠናቋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ቀሪ ዋና ዋና ስራዎችን ጨምሮ የማጠቃለያ ስራዎችን ለመፈጸም በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። ለመንገድ ደህንነትን የሚጠቁሙ የተለያዩ የትራፊክ ምልክቶችም እየተመረቱ ነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም-አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ሪልዌይ ቁጥር ሶስት ኢንጅነሪንግ ግሩፕ ነው፡፡ መንገዱን ለመገንባት የሚስፈልገውን ሰባት መቶ ስልሳ ስምንት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሃያ ሁለት ሺ ብር ሲሆን ወጪዉም በኢትዮጵያ መንግስት እየተሸፈነ ነው፡፡ የማማከሩን እና የቁጥጥሩን ስራ ኤልዳ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ጋር በጥምረት እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር በወረዳ ደግሞ 21 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡ በተመሳሳይ የዚህ መንገድ አካል የሆነዉ ኮከብ መስክ-አለም ከተማ የመንገድ ፕሮጀክት ስራ በመስክ ምልከታ ተቃኝቷል፡፡ የመንገድ ግንባታ 47 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለዉ ሲሆን በአስፓልት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ መንገዱን እየገነባ የሚገኘዉ ቻይና እስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ሲሆን የማማከርና ቁጥጥር ስራዉን ደግሞ ቫሊዩ ኢንጅነሪንግ እያከናወነ ይገኛል፡፡ በእሰካሁኑ የሥራ እንቅስቃሴ የዲዛይን ስራ፤ቅየሳ ስራ፣ የአፈር ቆረጣ፤ሙሌት ፤ጠረጋና ድልዳሎ ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 3.5 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የአፈር ቆረጣ ያለዉ ሲሆን ወደ አንድ ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የአፈር ቆረጣ ስራው ተጠናቋል ቀጣዩም እየተከናወነ ነው 105 ሜትር ርዝማኔ ያለዉ የጀማ ወንዝ ድልድይ የዚህ ፕሮጀክት የግንባታ አካል ነው ፡፡ በተጨማሪም ፕሮጀክቱ አራት ድልድዮችን 126 የከልቨርቶች ስራንም ያካተተ ሲሆን መከናወን ጀምሯል። የግንባታ ወጪዉም አንድ ቢሊየን ስድስት መቶ ዘጠና እምስት ሚሊይን ስድስት መቶ ሰማኒያ ስምንት , ብር ሲሆን የግንባታዉ መዋለ ነዋይ በኢትዮጵያ መንግስት ሙሉ ለሙሉ ይሸፈናል፡፡ የመንገዱ መነሻ ኮከብ መስክ ቀበሌ ሲሆን መረሃ-ቤተ ወረዳ አለም-ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ ፕሮጀክቱ የመንገዱ ትከሻን ጨምሮ በወረዳ 21 ሜትር ፣ በከተማ 15 ሜትር በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ አጠቃላይ ፕሮጀክቶቹ ተገንብተው ሲጠናቀቁ ሙከጡሪን ከእንሳሮ ወረዳና ከመርሃቤት ወረዳ ጋራ በቅርበት ያስተሳስራሉ፡፡ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን አሟጧ ለመጠቀም ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል፡፡ አካባቢዎቹ የጤፍ ምርትን ጨምሮ በርካታ የአዝዕርት እህሎችን በማምረት የሚታወቅ በመሆኑ አምራችን ከሸማች ጋር በማቀራረብ ግብይት ይበልጥ ያቀላጥፋል ፡፡ ከመንገድ ግንባታዉ በቅርብ ርቀት ቡርቃ ወንዝ ላይ ከበልበሊት የመስኖ ግድብ ጋር በማስተሳሰር የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቱን ወደ መሃል ገቢያ ለማድረስ ሁነኛ አበርክቶት ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢዉ የሚገኙትን በርካታ የቁም እንስሳት እና የእንስሳት ተዋፅዖ ምርቶችን በፍጥነት ወደገበያ ለማድረስ ያግዛል፡፡