uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 605 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 731-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 488-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 605 obunachiga ega bo‘ldi.

12 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 310 ga, so‘nggi 24 soatda esa -2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 32.38% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.05% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 405 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 048 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 13 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 605
Obunachilar
-224 soatlar
+607 kunlar
+31030 kunlar
Postlar arxiv
የጅግጅጋ-ገላልሼ-ደገሕመደው-ሰገግ አስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ። ጅግጅጋ፣ መስከረም 24/2015 ዓም (ኢመአ) ፡ በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ-ገላልሼ-ደገሕመደው-ሰገግ ሎት 2እና3 110 ኪ.ሜ አስፋልት መንገድ ግንባታ አስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ፡፡ በአሁኑ ወቅት 2 ኪሎ ሜትር ያህሉን አስፋልት ማልበስ የተቻለ ሲሆን፥ ከመንገዱ አጠቃላይ ግንባታም 41 በመቶው ተጠናቅቋል፡፡ ይህም በእቅዱ መሠረት እየተካሄደ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ፥ የፕሮጀክቱን ሎት ሁለት፥ በሚቀጥሉት አራት ወራት ውስጥ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግም በትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ በእሰከአሁኑ የግንባታ ሥራ፤ የአፈር ቆረጣ፣ ድልድይ ግንባታ፣ የግንባታ ግብአቶች ማምረትና ዝግጅት የውኃ መፋሰሻ ቱቦዎች ማምረት ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታውን፥ የፌደራል መንግስት በመደበው 1,828,264,182 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊዮን ኹለት መቶ ስልሳ አራት ሺህ) ብር ወጪ፣ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ሲ-ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እየሠራ ነው፡፡ በክልሉ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ የተፈጠረው የውኃ እጥረት በግንባታው ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ ለመቅረፍ በሥራ ተቋራጩ በኩል አስራ አንድ የውኃ ማጠራቀሚያ ኩሬዎች አጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ፡፡ ኩሬው ከግንባታው አልፎም የአካባቢውን ማኅበረሰብ እየጠቀመ ይገኛል፡፡ መንገዱ ሲጠናቀቅ፥ ቀድሞ ወደ ደገሕመደው ከተማ ለመሄድ፣ በደገሐቡር በኩል ይወስድ የነበረውን የ240 ኪ.ሜ ርቀት ወደ 195 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡ የፋፈን እና ደገሐቡር ዞኖችን በቅርበት በማገናኝት፥ በአካባቢው የሚገኙ አርብቶ-አደሮች እና በእንስሳት ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችንም ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ ፕሮጀክቱ ለአንድ ሺህ ያህል ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ የዚሁ ፕሮጀክት አካል የሆነው ሎት-1 ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ሎት-4 ደግሞ በግንባታ ላይ ይገኛል፡፡

አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ
+6
አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ

በባህርዳር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ በቀጣይ 3 ወራት ውስጥ የድልድዩ ዋነኛ አካል የሆነው (Grider) ሙሉ ለሙሉ ለመግጠም በትኩረት እየተሰራ ነው። የድልድዩን ዋና ዋና ስራዎች በእቅዱ መሰረት ለማከናወን አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ በመፍጠን ላይ ይገኛል። አጠቃላይ የግንባታ አፈፃፀሙ 76 በመቶ ደርሷል። በእስካሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ ከ760 ሜትር (Girder) ርዝማኔ ውስጥ (በሁለትም መስመር) 511 ሚትር የድልድይ (Grider) ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። በግንባታው ፕሮጀክት ላይ በዋነኛነት የድልድይ ተሸካሚ ምሰሶዎች (piers and Abutments) እንዲሁም ከመሬት በታች የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች (Piers piles, Abutment piles and ramp piles) ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል ። ለድልድዩ የሚያስፈልጉ 8 ቋሚ ተሸካሚ መሶሶዎች ( pylons/towers) ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል: ድልዲዩን ወጥሮ ለመያዝ ከሚያግዙ 72 (Stay cables) አምሳው የተጠናቀቀ ሲሆን የተቀሩትን በቅርብ ለመጨረስ እየተሰር ነው። በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 1.4 ቢሊዮን ብር ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ የተባለው ተቋራጭ ነው። የማማከር እና ቁጥጥር ስራውን ደግሞ ቦቴክ ቦስፈረስ ኮንሰልቲንግ ከስታዲያ ኢንጅነሪንግ ጋራ በጣምራ እየሰሩት ይገኛሉ። አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልዲይ በባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው እየተገነባ ያለው። ይህ ዘመናዊ ድልድይ ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ከሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ ጎን ለጎን ምቹ የሆነ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር ያደርጋል። በተጨማሪም ባህር-ዳር ከተማ ተጨማሪ ውበት እንድትላበስ ይረዳታል። ድልድዩ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በግራና በቀኝ በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ ይችላል፣ በተጨማሪም 5 ሜትር የእግረኛ መንገድ እንዲሁም የብስክሌት ተጠቃሚዎችን መስመር ባካተተ መልኩ ነው እየተገነባ የሚገኘው ፡፡

Call for Project Managers and Resident Engineers Training
Call for Project Managers and Resident Engineers Training

[Forwarded from Abrham Era] የጎዴ - ቀላፎ - ፌርፌር ሎት1 ጎዴ -ቀላፎ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመካሄድ ይገኛል፡፡ መስከረም 3 ቀን 2015 (ኢመአ)- በሶማሌ ክልል ሸበሌ ዞን ውስጥ የሚገኘው ይህ መንገድ በጠጠር ደረጃ ተገንብቶ ላለፉት በርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ግን ከአገልግሎት ብዛት አኳያ በመጎዳቱ እና ለትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ ባለመሆኑ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ በመንግስት ተወስኖ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ግንባታው በይፋ ሊጀመር ችሏል፡፡ 94.8 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን ፕሮጀክት ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው 1,530,000,000.00(አንድ ቢልዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን ብር)ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ(China Railway Seventh Group Co. Ltd) የተባለ የቻይና አለም አቀፍ ድርጅት ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ ስታድያ የምህንድስና ሥራዎች አማካሪ ኃላ/የተ/ የግል ማህበር ከንዑስ አማካሪ ጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ኃላ/የተ/ የግል ማህበር ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የጠጠር መፍጫ ማሽን በመትከል ለግንባታ ግብዓትነት የሚውል ምርት የማምረት ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የአነስተኛ የውሃ መተላለፊያ ቱቦዎችና የድልድይ ግንባታዎች ስራዎች በመካሔድ ላይ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ ከተማ 19 ሜትር እና በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጥራት ደረጃ እና የጊዜ ገደብ መስከረም 5 ቀን 2016 ዓ.ም ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በግንባታ ሂደቱ ወቅት የታዩ ውስንነቶችን በመለየት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ ይገኛል፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የጎዴ እና ቀላፎ ከተሞችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ የሚያስተሳስር ከመሆኑም ባሻገር በአካባቢው ለሚገኙ ትንንሽ ከተሞች እድገትም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከዚህም ባሻገር በዚህ አካባቢ ፍየል ፣ ግመል ፣ ሽንኩርት እንዲሁም ሌሎች አትክልት እና ፍራፍሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ የሚገኙ በመሆናቸው አርሶ እና አርብቶ አደሮች ምርቶቻቸውን እና የቁም እንስሶቻቸውን ካለምንም ውጣ ውረድ በአፋጣኝ ወደ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ በተጨማሪም የጤና ፣ የትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል።

አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ----------------------------------------------------------------------------------- ጋምቤላ፣ ነሐሴ 30፣ 2014 (ኢመአ) በጋምቤላ ክልል ግንባታው እየተከናወነ ያለውና የጋምቤላ ክልልን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ከኦሮሚያ ክልሎች ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው (የጋምቤላ አቦቦ-ጎግ ዲማ) አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ፡፡ ሰማኒያ ሁለት ኪሜ ( 82ኪሜ) የሚረዝመው ይህ መንገድ በአሁኑ ወቅት የዲዛይን ስራን ጨምሮ የምንጣሮ ስራ፣የአፈር ጠረጋ፣ ድልዳሎ እና ሙሌት፣ ተጨማሪ የጠጠር መፍጫ ማሽነሪ ተከላ ስራዎች እየተከናወኑለት ይገኛል። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ NKH Construction Plc ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ በለስ ኮንሰልት Plc እየከወነ ይገኛል:: አጠቃላይ የግንባታ መዋለንዋይ ብር 1,574,746,965.24 ሲሆን የግንባታ ውጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረና ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ በመሆኑ ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት፣ አሽከርካሪዎችን ለጊዜ ወጪ እና ብክነት የዳረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ካለው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አንፃር መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ወደ ደቡብ ሱዳን ከሚወስደው ዋና አውራ ጎዳና (Trunk Road) ጋራ ያገናኘዋል፡፡ በተጨማሪም ዲማ ወረዳን ከጎግ ወረዳ ጋራ በማገናኘት ወደ ጋምቤላ የሚደረገውን ጉዞ የግዜና ገንዘብ ብክነት በእጥፍ ይቀንሰዋል። የመንገዱ መግንባት የኢሉአባቦር እና የሸካ ዞኖችን ከአኙዎክ ዞን ጋራ በቅርበት ያስተሳስራል። አካባቢው በርካታ ማዕድናት (ወርቅ) እና ሰፋፊ የእርሻ መሬት የሚገኝበት በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው። በመንገዱ ኮሪደርና በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የማር፥ ቡና፥ ቅመማቅመም እንዲሁም የሻይ ተክል ምርቶች በተገቢው ፍጥነት ወደ መሃል ገበያ ለማድረስ ያስችላል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ከማሳለጡም ባሻገር፣ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማሕበራዊ አገልግሎት ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል። ነባሩ መንገድ የጎን ስፋት ከ (3) ሶስት ሜትር የማይበልጥ ሲሆን አሁን እየተገነባ የሚገኘው በከተማ 17 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ያለው።

አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ----------------------------------------------------------------------------------- ጋምቤላ፣ ነሐሴ 30፣ 2014 (ኢመአ) በጋምቤላ ክልል ግንባታው እየተከናወነ ያለውና የጋምቤላ ክልልን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ከኦሮሚያ ክልሎች ጋር በአቋራጭ የሚያስተሳስረው (የጋምቤላ አቦቦ-ጎግ ዲማ) አኩይላ-አቻኛ ዲማ/ራድ መንገድ ግንባታ በታቀደለት የግንባታ ጊዜ እየተከወነ ይገኛል ፡፡ ሰማኒያ ሁለት ኪሜ ( 82ኪሜ) የሚረዝመው ይህ መንገድ በአሁኑ ወቅት የዲዛይን ስራን ጨምሮ የምንጣሮ ስራ፣የአፈር ጠረጋ፣ ድልዳሎ እና ሙሌት፣ ተጨማሪ የጠጠር መፍጫ ማሽነሪ ተከላ ስራዎች እየተከናወኑለት ይገኛል። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ NKH Construction Plc ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ በለስ ኮንሰልት Plc እየከወነ ይገኛል:: አጠቃላይ የግንባታ መዋለንዋይ ብር 1,574,746,965.24 ሲሆን የግንባታ ውጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረና ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ በመሆኑ ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት፣ አሽከርካሪዎችን ለጊዜ ወጪ እና ብክነት የዳረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ካለው ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ አንፃር መንገዱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ወደ ደቡብ ሱዳን ከሚወስደው ዋና አውራ ጎዳና (Trunk Road) ጋራ ያገናኘዋል፡፡ በተጨማሪም ዲማ ወረዳን ከጎግ ወረዳ ጋራ በማገናኘት ወደ ጋምቤላ የሚደረገውን ጉዞ የግዜና ገንዘብ ብክነት በእጥፍ ይቀንሰዋል። የመንገዱ መግንባት የኢሉአባቦር እና የሸካ ዞኖችን ከአኙዎክ ዞን ጋራ በቅርበት ያስተሳስራል። አካባቢው በርካታ ማዕድናት (ወርቅ) እና ሰፋፊ የእርሻ መሬት የሚገኝበት በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው። በመንገዱ ኮሪደርና በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የማር፥ ቡና፥ ቅመማቅመም እንዲሁም የሻይ ተክል ምርቶች በተገቢው ፍጥነት ወደ መሃል ገበያ ለማድረስ ያስችላል። የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ከማሳለጡም ባሻገር፣ የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች ማሕበራዊ አገልግሎት ተቋማት ተደራሽነትን ያሰፋል። ነባሩ መንገድ የጎን ስፋት ከ (3) ሶስት ሜትር የማይበልጥ ሲሆን አሁን እየተገነባ የሚገኘው በከተማ 17 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር ተጨማሪ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ያለው።

የጅግጅጋ ከተማ ባይፓስ(Bypass) መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ ነው። ጅግጅጋ ፣ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም. ፦ የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅ የሚያስቀረው የጅግጅጋ ባይፓስ (Bypass) መ
+4
የጅግጅጋ ከተማ ባይፓስ(Bypass) መንገድ ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ ነው። ጅግጅጋ ፣ ነሐሴ 23/2014 ዓ.ም. ፦ የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅ የሚያስቀረው የጅግጅጋ ባይፓስ (Bypass) መንገድ ግንባታ ሥራ እየተካሄደ ነው። ሰባት (7) ኪ.ሜ የሚረዝመው የመንገድ ፕሮጀክቱ የፌደራል መንግስት በመደበው 672 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው። 'ባይፓስ' መንገድ አንድ ዋና ማሳለጫ ባላቸው ከተሞች በውጭ የሚገነባና ተሽከርካሪዎች ከተማ ውስጥ መግባት ሳያስፈልጋቸው አልፈው እንዲሄዱ የሚያገለግል ነው። መንገዱ የከተማዋን የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ ለመቅረፍ ታልሞ ነው የሚገነባው። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ይርጋለም ኮንስትራክሽን ሲሆን በእስካሁኑ የግንባታ ሂደት የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የሰብቤዝ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራና የ94 ሜትር ድልድይ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። አስፋልት ለማንጠፍ የሚረዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችም እየተሠሩ ነው። የመንገድ ግንባታው ዋነኛ ግብዓት የሆነው የሲሚንቶ ዕጥረት ለስራው ፈተና እንደሆነበትም ታውቋል። ችግሩን ለመቅረፍ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ። የማማከሩን ስራ እያከናወነ የሚገኘው ደግሞ ኤልዳ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንትሲ ሲሆን የድጋፍና ክትትል ሥራውን እያከናወነ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው በትላልቅ ከተሞች የመንገድ ደረጃ በኮንክሪት አስፋልት እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፥ የእግረኛ እና የብስክሌት መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ በፕሮጅክቱ ተካትተውበታል። የጅግጅጋ ባይባስ ግንባታ ሲጠናቀቅ የንግድ እንቅስቃሴዎችን በማሳለጥ፤ ለከተማዋ ዕድገት ምቹ ዕድል ይፈጥራል። በክልሉ ለሚደረጉ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችም የጎላ ሚና አለው። መንገዱ 30 ሜትር የጎን ስፋት አለው።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለሰራተኞቹና አመራሮቹ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየሰጠ ነው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሰራተኞች እና አመራሮች የአቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሰልጠና ዛሬ በቢሾፍቱ ከተማ ተጀመረ። ስለጠናው በአራት የተለያዩ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሲሆን እነሱም Project management፣ Project planning and implementation፣ Good governance in public sector administration እና 4.Human resource management ናቸው፡፡ ስልጠናው እየተሰጠ የሚገኘው አሀጉር አቀፈ እውቅና ባለው East and South Africa Training Management Institute (ESAMI) እና ሌሎች የስለጠና እና ምርምር ተቋማት በጣምራ ነው። በዘርፉ የረጅም አመታት ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች በመሰጠቱ ስለጠናው የበለጠ ውጤት ተኮር ይሆናል። የስለጠናው በቨርቿል እና በአካል እየተሰጠ ይገኛል። በዛሬ እለት በቢሾፍቱ ከተማ የተጀመረው ይህ ስልጠና ተቋሙ መንግስትና ህዝብ የጣለውን አገራዊ ሀላፊነት ይበልጥ በብቃት እንዲወጣ ይረዳዋል። በስልጠናው ከ110 በላይ የተቋሙ ሰራተኞች እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን የቀሰሙትን ዕውቀት ለሌሎችም በማካፈል ስራን ለማቀላጠፍ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ኢመአ በክረምት ወራት አቅዶ እያከናወናቸው ከሚገኘው በርካታ ስራዎች አንዱ የሰራተኞቹን አቅም በተለያዩ ስልጠናዎች በማዳበር በአዲሱ የስራ አመት ውጤታማ ስራ ማከናወን ነው። ስለጠናውም እንደየ ኮርሱ ይዘትና ስፉት ከአንድ እስከ ሶስት ሳምንት የሚቆይ ይሆናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

Supply, installation, training, commissioning, integration, and maintenance support of the ITS & Toll Collection systems, and their Power supply and Communication infrastructures of the Modjo-Hawassa Highway በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST Individual Consultancy Service for the Implementation of the Livelihood Restoration Plans for the Modjo-Hawassa Expressway Project በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

REQUEST FOR EXPRESSIONS OF INTEREST Individual Consultancy Service for the Implementation of the Livelihood Restoration Plans for the Modjo-Hawassa Expressway Project

ውድ የገጻችን ተከታዮች፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከነባሩ ሚዲያ በተጨማሪ በተለያዩ የበይነ መረብ ሚዲያ አውታሮች የመንገድ አስተዳደርና ልማት መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ በያዘው ዕቅድ መሰረት
ውድ የገጻችን ተከታዮች፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከነባሩ ሚዲያ በተጨማሪ በተለያዩ የበይነ መረብ ሚዲያ አውታሮች የመንገድ አስተዳደርና ልማት መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ በያዘው ዕቅድ መሰረት እስካሁን በዌብ ፖርታልና ፌስ ቡክ መረጃዎችን ተደራሽ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡ አሁን ደግሞ ይፋዊ የቲዊተር አካውን በመክፈት ለደንበኞቻችን መረጃዎችን ተደራሽ የማድረግ ሥራ እየራን ስለሆነ የቲዊተር ገጻችን ተከታይ በመሆን ቤተሰብ እንዲሆኑ ስንጋብዛችሁ በታላቅ ደስታ ነው፡፡ ለተቀናጀ የመንገድ ልማት እና ሁለንተናዊ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ተግተን እንሰራለን!! ዘላቂና አስተማማኝ የመንገድ መሠረተ ልማት ለበለጸገች ኢትዮጵያ!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መላው ሰራተኞች እና አመራሮች ሁለተኛ ዙር የችግኘ ተከላ መርሃ-ግብር ዛሬ አከናወኑ ። የዋናው መስሪያ ቤት፤ የአለም ገና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞች እና አመራሮች ናቸው በእንጦጦ ፖርክ አካባቢ 3ሺህ ችግኞችን ዛሬ በስፍራው የተከሉት ። የበጀት አመቱን ሁለተኛ ዙር የችግኘ ተከላ መርሃ-ግብር ሁሉም በተቋሙ ስር የሚገኘው ምርምር ማዕከልን ጨምሮ ዲስትሪክቶች ፥ ሴክሽኖች እና ማሰልጠኛ ማዕከላትም ሶስት መቶ ሺህ ችግኞችን በዛሬው ዕለት በየአካባቢያቸው ተክለዋል ። ኢመአ ባለፋት ዓመታት ሀገራዊ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ሀላፊነቱን ይበልጥ እየተወጣ ነው ። በኢመአ የጊንጪ ማሰልጠኛ ጣቢያም የራሱን የችግኘ ማፍያ ፕሮጀክትን እውን በማድረግ ለአካባቢው ህብረተሰብ ፣ለተቋማት፣ የተለያዩ የችግኘ አይነቶችን በማበርከት ላይ ይገኛል። የተቋሙ ሰራተኞችም አረንጓዴ አሻራን ማሰረፉ ያለው ጥቅም የጎላ በመሆኑና ሀገራዊ ባህል እየሆነ በመምጣቱ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የተከሉትን ችግኞች በቀጣይ መንከባከብ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። ባለፉት ዓመታት በኢመአ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከ3ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። ዘንድሮም አንድ ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብ የተያዘ ሲሆን ከወዲሁ በስኬት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው ኢመአ የችግኝ ተከላ-መርሃ ግብሩ ተገቢውን ሳይንሳዊ ሂደት ጠብቆ እንዲተከል፤ ከአካባቢው ስን- ምህዳር ጋር የሚጣጣሙ ሀገር በቀል ችግኞች እውን እንዲሆኑ፤ ከተተከሉም ብኋሏ የመጸደቅ ምጣኔው እንዲረጋገጥ፤ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ ነው።