fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 307 مشترک است و جایگاه 1 759 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 546 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 307 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 15 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 88 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 40.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.41% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 352 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 050 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 17 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 16 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 307
مشترکین
+224 ساعت
+297 روز
+8830 روز
آرشیو پست ها
የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ ጅግጅጋ፣ የካቲት 22/2018 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ የትራፊክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አጠቃላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ 6 ነጥብ 93 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፣ 30 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ተገንብቷል። መነሻውን ጅግጅጋ ከተማ መግቢያ አድርጎ ቶጎ-ጫሌ አደባባይ ላይ ያበቃው ይህ ፕሮጀክት ዋና ዋና ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን፣ የትራፊክ ምልክቶች ተከላ  እና ሌሎች ጥቃቅን ስራዎች እየተከናወኑ ነው። በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ  ግንባታ ተካቷል። ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ግንባታውን ያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤልዳ አማካሪ ድርጅት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር  በጋራ ሰርተውታል። ለግንባታው ማስፈጸሚያ የዋለውን 672,098,730.28 (ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊየን ዘጠና ስምንት ሺህ ብር ሰባት መቶ ሰላሳ ብር ከሃያ ስምንት) ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ተሸፍኗል። የተለዋጭ መንገድ ግንባታው መጠናቀቅ በጅግጅጋ ከተማ ውስጥ እንዲሁም መግቢያ እና መውጫ  ላይ የሚታየውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያቃልላል። ከቶጎ ጫሌ  እንዲሁም ከደገሀቡር የሚመጡ የከባድም ሆነ ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች ጅግጅጋ ከተማን ሳያቋርጡ ለማለፍ አማራጭ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት እና ውበት በማሳለጥ በኩል ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአጣጥ ማዞሪያ - ጉንችሬ - ቆሴ - ሌራ - ጌጃ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 56 በመቶ ተጠናቀቀ ጉንችሬ፣ የካቲት 20/2018 (ኢ መ አ):- የጉራጌ፣ ስልጤ እና ሃዲያ ዞኖችን እንዲሁም 6 ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው የአጣጥ ማዞሪያ - ጉንችሬ - ቆሴ - ሌራ - ጌጃ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 56 በመቶው ተጠናቅቋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 5 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግሥት በጀት ተይዞለት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 47 ኪሎሜትሩን በአስፋልት የማልበስ ሥራ ተከናውኗል። ከዚህ ጎን ለጎንም የመሬት ጠረጋ፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ፣ የአስፋልት ንጣፍ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። የግንባታውን አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ለማስቀጠል በተቋማችን በኩል የቅርብ ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ወደ አጣጥ ሆስፒታል፣ ጉንችሬ፣ ዲንቁላ እና ጌጃ ከተሞች የሚወስዱትን አገናኝ መንገዶች ጨምሮ አጠቃላይ 97 ኪሎሜትር ይሸፍናል። ሀገር - በቀሉ ዓለማየሁ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ የመንገድ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ኤስጂ የምህንድስና አማካሪዎች የፕሮጀክቱን ጥራት እና ቁጥጥር ሥራ በመሥራት ላይ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በሦስቱ ዞኖች ውስጥ የሚገኙትን የቸሃ፣ እኖር፣ ኤነርና መገር፣ እንደጋኝ፣ አመካ እንዲሁም ምዕራብ አዘርነትን ጨምሮ የ6 ወረዳዎች ሁለንተናዊ ትስስር ያጠናክራል። በአካባቢው የሚገኙትን የተለያዩ የግብርና ምርት ውጤቶች በስፋት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የጎላ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቆሼ - ሚቶ - ወራቤ አስፋልት መንገድ ግንባታ በቀጣይ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ወራቤ፣ የካቲት 18/2018 (ኢ መ አ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 5 ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው የቆሼ - ሚቶ - ወራቤ አስፋልት መንገድ ግንባታ 79 ነጥብ 5 በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የፕሮጀክቱን ዋና ዋና ሥራዎች በቀጣይ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ይገኛል። በመንገድ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ47 ኪሎሜትር አስፋልት ንጣፍ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የሰብቤዝ እንዲሁም የቤዝኮርስ ሥራዎች ተከናውነዋል። የሁለት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ ተካትቷል። ከፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሥራ አሁን ላይ 58 ኪሎሜትሩ ወይንም 79 ነጥብ 5 በመቶው ተጠናቅቋል። የግንባታውን ዋና ዋና ሥራዎች በቀጣይ ዓመት ታኅሣሥ ወር ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 73 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፣ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው። የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሉ የንኮማድ ኮንስትራክሽን የሚያከናውን ሲኾን፥ የጥራት እና ቁጥጥር ሥራውን ፕሮሚነንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽንስ ያከናውናል። ለግንባታ የተመደበው 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በፌደራሉ መንግሥት ይሸፈናል። የመንገዱ ነባር ገጽታ 63 ኪሎሜትሩ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲኾን፥ ቀሪው ምንም ዓይነት የመንገድ መሠረተ ልማት አልነበረውም። አሁን ላይ መንገዱ በወረዳ የእግረኛ መንገድን ሳይጨምር 14 ሜትር፣ በገጠር ቀበሌ የመንገድ ትከሻን ሳይጨምር 7ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በመገንባት ላይ ነው የሚገኘው። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የማረቆ እና የስልጤ ሕዝብ ማኅበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ትስስር ያጠናክራል። ከዚህ ቀደም ከቆሼ ከተማ ተነስቶ የስልጤ ዞን መናገሻ ወራቤ ከተማ ለመድረስ የሚፈጀውን 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ በ2 ሰዓት በማሳጠር፣ በአካባቢው በስፋት የሚታወቁትን የበርበሬ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ እና መሰል የጥራጥሬ እና የአዝርዕት ምርት ውጤቶች በፍጥነት እና በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኮልፌ 18 ማዞሪያ (ኮልፌ ሃይስኩል)- አሸዋ ሜዳ - ኬላ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል አዲስ አበባ ፣ የካቲት 17/ 2018 ዓ.ም ( ኢመአ ) ፡ የአዲስ አበባ ከተማን ከተለያዩ የክልል ከተሞች ጋር ከሚያገናኙ ዋና ዋና መግቢያና መውጫ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የኮልፌ ሃይስኩል - አሸዋ ሜዳ - ኬላ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ፡፡ በአሁኑ ወቅት ከአጠቃላይ የመንገድ ይዞታ 14 .73 ኪሎ ሜትር ውስጥ 8 ኪሎ ሜትር መንገድ የአስፋልት ንጣፍ ተደርጎለታል ፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ በኢመአ የራስ ሃይል ( ዓለም ገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ) እና በሀገር-በቀሉ የሥራ ተቋራጭ ብሪጅ ኮንስትራክሽን በጋራ እየተገነባ የሚገኝ ሲሆን፣ የማማከሩን ሥራ ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን እየተወጣው ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚሆነው ወጪ ዘጠኝ ቢሊዮን ሁለት መቶ ሃምሳ አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ብር ( 9, 254 586 980 ) የሚሸፈነው በፌደራል መንግሥት ሲሆን፣ መንገዱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ( ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ) እና ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ( ሸገር ከተማ አስተዳደርን ) አቋርጦ በማለፍ ከምዕራቡ የሀገራችን ክፍል ጋር የነበረውን ቁርኝት ያጠናክራል ፡፡ መንገዱ የአዲስ አበባ መግቢያና መውጫ እንደመሆኑ መጠን በቦታው የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ እና የመንገዱን ደረጃ ለመጠበቅ ሲባል ማስፋፊያ በማድረግ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶች በዲዛይኑ በማካተት በአዲስ መልክ እየተገነባ ይገኛል፡፡ መንገዱ አጠቃላይ 50 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል። የመንገድ ግንባታው ከአስፋልት ንጣፍ ጎን ለጎን የአቃፊ ግንብ ፣ የውኃ መፋሰሻ ፣ የመንገድ አካፋይ ፣ የከልቨርት እንዲሁም ቀሪ የአፈር ቆረጣ ፣ የሰብ ቤዝና የቤዝ ኮርስ ስራዎች እየተከናወኑለት ይገኛል ፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ የአካባቢውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ከማድረጉም ባሻገር የጉዞ ጊዜን ፣ ወጪና እንግልትን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል ፡፡ በተጨማሪም የግብርና ምርቶችን በፍጥነት ለገበያ እንዲቀርቡና በአካባቢው ብዛት ያላቸውን የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለማእከላዊ ገበያ ተደራሽ የማድረግ ጠቀሜታ ይኖረዋል ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የመረዋ - ሰሞዶ - ሰቃ እና ሰሞዶ ሊሙ መገንጠያ መንገድ ግንባታ 64 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ) ፦ 93.95 ኪ.ሜ የሚረዝመው የመረዋ - ሰሞዶ - ሰቃ እና ሰሞዶ ሊሙ መገንጠያ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃጸም 64 በመቶ ደርሷል፡፡ እስካሁን ባለው የግንባታ ሂደት 42.65 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራ የተከናወነ ሲሆን የአፈርጠረጋ 88.49% እና የአፈር ሙሌት ስራው ደግሞ 80.32% ደርሷል። በተጨማሪም የአንድ ድልድይ እና 49 የውሃ መፋሰሻዎች ግንባታ ለማጠናቀቅ ተችሏል። የመንገዱ ግንባታ በቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በተባለ የሥራ ተቋራጭ እየተከናወነ ሲሆን፤የማማከርና የቁጥጥር ሥራው በተባበሩት የምሕንድስና አማካሪዎች አማካኝነት ነው እየተሰራ የሚገኘው። መንገዱ በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ ከተሞች 12 ሜትር እንዲሁም በወረዳ ከተሞች 19 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው 2 ነጥብ 58 ቢሊዮን ብር ወጪም በኢትዮጵያ መንግሥት የተሸፈነ ነው። በግንባታው ወቅት ባጋጠመ የተራዘመ ዝናብና በወሰን ማስከበር ምክንያት ያጋጠሙ መዘግየቶችን ለማካካስ፤ በበጋ ወቅትም የሥራ ሰዓትን በማራዘም፣ ተጨማሪ ማሽነሪዎችን በማሰማራትና የወሰን ማስከበር ሂደቱን ለማጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት የግንባታ ሥራው ተጠናክሮ እየተሰራ ይገኛል። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በጅማ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሊሙ ገነት፣ የሊሙ ኮሳ እና የማና ወረዳዎችን እንዲሁም በስራቸው የሚገኙ ቀበሌዎችን በማስተሳሰር እና የጉዞ ጊዜን በከፍተኛ ሁኔታ በማሳጠር የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋግጣል። ከዚህም ባሻገር በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ቡና፣ በቆሎ እና አቮካዶ ያሉ የግብርና ምርቶችን በፍጥነት ወደ ገበያ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን ከመፍጠሩም ባለፈ፤ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማነቃቃትና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በበለጠ ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የድሬዳዋ - ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ ድሬዳዋ ፣ የካቲት 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ): የድሬዳዋ ከተማን ከሽንሌ ከተማ ጋር የሚያገናኘው የድሬዳዋ - ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ስራዎች ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን፣ የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ፤ የቀልም ቅብ ስራዎች እና ሌሎች ጥቃቅን ስራዎች ተገባደዋል። አጠቃላይ ፕሮጀክቱ 29 ነጥብ 29 ኪሎ ሜትርን የሚሸፍን ሲሆን በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የተገነባው። ዓለም - አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የመንገዱን ግንባታ ያካሄደው ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራው በቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬንያ ሊሚትድ ተከናውኗል። ፕሮጀክቱን ለማስፈፀም የዋለው 1,146,143,392 ( አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ አርባ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ አርባ ሶስት ሺህ ሶስት መቶ ዘጠና ሁለት ብር ሲሆን ሙሉ ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል፡፡ የመንገዱ መገንባት የድሬዳዋ እና የሽንሌ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ያገናኛል። ከዚህም ባሻገር ከጂቡቲ በድሬዳዋ ደወሌ መንገድ በኩል የሚመጡ የጭነት ተሸከርካሪዎች ድሬዳዋ ከተማ ውስጥ ሳይገቡ የሚያልፉ ሲሆን ይህም ቀደም ሲል ይፈጠር የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ አስቀርቶታል፡፡ በተጨማሪም አሽከርካሪዎች ይወስድባቸው የነበረውን የጉዞ ጊዜ አሳጥሯል። በአካባቢው በስፋት የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ ገበያ በማውጣት የገበያ ትስስርን ለመፍጠር ያስችላል፡፡ መንገዱ በወረዳ 21.5 ሜት ር ፣ በከተማ 25 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሰቀላ-አዴት የመንገድ ግንባታ ሂደትን ለማቀላጠፍ በትኩረት እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2018 (ኢመአ) :- የደምበጫ ፈረስ ቤት አዴት ኮንትራት ሁለት ሰቀላ-አዴት 61.76 ኪሎሜትር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሂደትን ለማቀላጠፍ በትኩረት እየተሰራ ነው ፡፡ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ባለው በዚህ የመንገድ ግንባታ ሂደት አሁን ላይ የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የውሃ ማፋሰሻ፣ የድልድይ እና የድንጋይ ድጋፍ እንዲሁም የጠጠር መፍጨት ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው። ግንባታውን ዲ. ኤም.ሲ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፤ ኢንጅነር ዘውዴ እስክንድር ኃ/የተ/የግ/ማህበር ደግሞ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ እየሰራው ይገኛል። ለግንባታው የሚውለው 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። በእስካሁኑ የግንባታው ሂደት በአካባቢውአልፎ አልፎ የሚስተዋለው የፀጥታ ፣ የወሰን ማስከበር እና የግብዓት እጥረት ችግሮች ፕሮጀክቱ በሚፈለገው ፍጥነት እንዳይሄድ እንቅፋት ሆኖው ቆይተዋል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ባደረገው ከፍተኛ ጥረት አሁን ላይ ፕሮጀክቱን ለማፍጠን በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የይልማና ዴንሳ ፣ ደጋ ዳሞት እና ቋሪት ወረዳዎች እና የሰቀላ ፣ የሀሙስ ገበያ ፣ አይባር ፣ ጎሽየ ፣ አዴት ዙሪያ እና ብር አዳማ ያሉ ቀበሌዎች በማገናኘት ሁለንተናዊ ትስስርን በዘላቂነት ይፈጥራል። በተጨማሪም በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን እንደ ጤፍ ፣ በቆሎ ፣ ሽንኩርት ፣ ገብስ ፣ ስንዴና ድንች ያሉ ሰብሎችን እንዲሁም የማርና የእንስሳት ተዋፅኦዎችን ያለምንም እንግልት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማውጣት ሰፊ እድል በመፍጠር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል። ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት በሚሆንበት ጊዜ ቀድሞ ለጉዞ ይባክን የነበረውን ሰዓትና ድካም በግማሽ በመቀነስ የአካባቢውን የንግድ ልውውጥና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው ይጠበቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads