fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 688 مشترک است و جایگاه 8 024 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 156 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 688 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 137 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 35.24% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 17.40% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 528 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 730 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 688
مشترکین
-524 ساعت
-17 روز
+13730 روز
آرشیو پست ها
የሥራ አመራር ቦርዱ የተቋሙን ዓመታዊ አፈፃፀም እየገመገመ ነው .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በስካይ ላይት ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ግምገማው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ  በኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣  በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፍ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና የጥገና ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም ያቀረቀቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት በአስራ ሁለት ወራት ውስጥ ተቋሙ ካመነጨው አጠቃላይ ኃይል ውስጥ 93 በመቶውን ለሀገር ውስጥ እና  ቀሪ  7 በመቶውን ደግሞ ለጎረቤት ሀገራት አቅርቧል። በበጀት ዓመቱ በኃይል ማመንጨት፣ ማከፋፈል፣ ማስተላለፍ እና ሽያጭ እንዲሁም በዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ አበረታች ለውጦች መታየታቸውን ጠቁመዋል። ተቋሙ ለዘመናት ከተከማቸበት ዕዳ ወጥቶ ወደ ትርፍ የተሸጋገረበት ዓመት እንደነበርም ነው በሪፖርታቸው ያመለከቱት። በበጀት ዓመቱ ተቋሙ ከነበረበት 168 በመቶ ኪሳራ ወደ ያልተጣራ 39 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ትርፍ መሸጋገር መቻሉን ገልፀዋል። ለዚህ ስኬት መገኘትም የመንግስት፣ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድና የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ድርሻ የጎላ መሆኑን በመጥቀስ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዳሴ፣ የአይሻ እና የአሰላ ፕሮጀክቶችን በስኬት አጠናቆ ወደ ኦፕሬሽን ማስገባት መቻሉ የኢነርጂ ምርት ዕድገት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ የፕሮጀክቶች ማኔጅመንት አቅም ማነስ፣ የጸጥታ ችግርና ሥርቆት፣ የወሰን ማስከበር መዘገየት፣ የግዥ ሂደት መጓተት፣ የሎጂስቲክስ እንዲሁም የነዳጅ እጥረት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቁ ዋና ዋና ተግዳሮቶች የነበሩ መሆናቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ከ940 ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2018 በጀት ዓመት 94
+7
ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ከ940 ጌጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል  .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 1 የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2018 በጀት ዓመት 943 ጌጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ተናገሩ፡፡   ሥራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደተናገሩት ጣቢያው በ2018 በጀት ዓመት ለማመንጨት ካቀደው 986 ጌጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ 943 ጌጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማመንጨት የዕቅዱን 95 ነጥብ 63 በመቶ አሳክቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ የመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ከዕቅዱ የ43 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም የ4 ነጥብ 37 በመቶ እንዲሁም ከባለፈው የ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ34 ጌጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 6 በመቶ ቅናሽ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማመንጫ-ጣቢያው-በበጀት-ዓመቱ-ከ940-ጌጋ-ዋት-ሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

🌱 "#ተስፋን_እንትከል!" 🌱 👉 በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል ታሪካዊ ዘመቻ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚህ
+9
🌱 "#ተስፋን_እንትከል!" 🌱 👉 በዛሬው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል ታሪካዊ ዘመቻ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚህም መሰረት በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች፣ የአሉቶ ጂኦተርማል ቁፋሮ ፕሮጀክት ሰራተኞችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም የሰሜን ምሰራቅ -2 ሪጅን ሰራተኞች ባሉበት አካባቢ የችግኝ ተከላ ላይ ተሳትፈዋል፡፡   የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞች በፕሮጀክቱ መገኛ ስፍራ ከአይሻ ወረዳ አመራሮች ጋር ችግኝ ሲተክሉ የአሉቶ ጂኦተርማል ቁፋሮ ፕሮጀክት ሠራተኞች ደግሞ ከፌዴራል ፖሊስ እና ከኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት አባላት ጋር ችግኝ ተክለዋል፡፡   በተመሳሳይ የሰሜን ምሰራቅ 2 ሪጅን ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች በአፋር ክልል ዱብቲ ወረዳ አይሮልአፍ ቀበሌ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የችግኝ ተከላው ተቋሙ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=🌱-ተስፋን_እንትከል-🌱&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27

ተቋሙ ከዋና ተልዕኮው ጎን ለጎን የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተሰጠው የኃይል ማመንጨትና ማስተላለፍ ሀገራ
ተቋሙ ከዋና ተልዕኮው ጎን ለጎን የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተሰጠው የኃይል ማመንጨትና ማስተላለፍ ሀገራዊ ተልዕኮ ባሻገር የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የማህበራዊ ኃላፊነት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት ኃይል ማመንጫት አስከ ማከፋፈያ ጣቢያ ማድረስ፣ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ከ132 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮችን መገንባት እንዲሁም ኃይልን በጅምላ ለደንበኞች ማቅረብ በአዋጅ የተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት ናቸው። ተቋሙ እነዚህን አገራዊ ኃላፊነቶች በብቃት ከመወጣት ጎን ለጎንም የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት የሚያስችሉ ተጨባጭ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ከዋና-ተልዕኮው-ጎን-ለጎን-የማህበረ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

photo content

ከኤሌክትሪክ ሽያጭ ባለፉት አምስት ዓመታት 1 ነጥብ 15 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት አምስት ዓመታት ከኤሌክትሪክ ሽያጭ  1 ነጥብ 15 ቢሊየን ዶላር የሚሆን የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ አለማየሁ መንግስቱ እንደገለፁት በአምስት ዓመታት ውስጥ ከተገኘው የውጭ ምንዛሪ ውስጥ 611 ሚሊየን ዶላሩ ወይም 53 በመቶ የሚሆነው ባለፉት ሦስት ዓመታት ከዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች የተገኘ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የውጭ ምንዛሪ ግኝቱ በ2014 በጀት ዓመት ከነበረበት 68 ነጥብ 4 ሚሊየን ዶላር በ2018 በጀት ዓመት 475 ሚሊየን ዶላር መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ከአስር ዓመታት በላይ ተከታታይ ኪሳራ ውስጥ ቢቆይም መንግስት እና ተቋሙ በተለያዩ ጊዜያት ባከናወኗቸው የሪፎርም ሥራዎች ጤነኛ የፋይናንስ ቁመና ላይ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ መንግስት አምስት መቶ ቢሊየን ብር የሚደርስ የተቋሙን ዕዳ በመውሰዱ፣ የታሪፍ ማሻሻያ በመፈቀዱ፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ስማርት ቆጣሪዎች በመተከላቸውና ኦፕሬሽናል ልህቀት በመጨመሩ የተቋሙ የፋይናንስ ቁመና መስተካከሉን ዘርዝረዋል፡፡ ከሀገራዊ ለውጥ በኋላ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁ እንዲሁም የኃይል ማምረት አቅም፣ የኢነርጂ ምርት መጠን እና ሽያጭ እያደገ መምጣቱ ተጨማሪ አስተዋጽዖ አበርክተዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 119 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡንና ከዚህ ውስጥ ያልተጣራ 39 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ማግኘቱን መግለፃችን ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ በውጭ ምንዛሪ የ475 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ አከናውኗል ………///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በውጭ ምንዛሪ የ475 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ ማከናወኑን የተ
ተቋሙ በውጭ ምንዛሪ የ475 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ አከናውኗል ………///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በውጭ ምንዛሪ የ475 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ ማከናወኑን የተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት በውጭ ምንዛሪ የ455 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ ለማከናወን ታቅዶ የ475 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ በማከናወን ከዕቅዱ የ5 በመቶ ብልጫ ያለው አፈፃፀም ተመዝግቧል፡፡ ለጎረቤት ሀገራት የ140 ነጥብ 19 ሚሊየን ዶላር ኃይል ሲቀርብ ለቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ደግሞ የ335 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡ በውጭ ምንዛሪ የተከናወነው ሽያጭ ከአምናው ተመሳሳይ ሽያጭ የ41 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

"የፕሮጀክት አፈጻጸም ላይ ለሚታዩ ችግሮች ሁሉም ኃላፊነት ወስዶ መስራት አለበት!" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ .......///….... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የሚታዩ  ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ሁሉም ሠራተኛ እና የሥራ መሪ ኃላፊነት ወስዶ መስራት እንዳለበት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀሙን ከሠራተኞችና ሥራ መረዎች ጋር በመሆን ገምግሟል። በበጀት ዓመቱ በኦፕሬሽንና በፕሮጀክት ግንባታ አፈፃጸም እንዲሁም በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኮርፖሬት ገቨርናንስ፣ በዲጂታላይዜሽንና በንብረት አስተዳደር የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ተወካይ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ ቀርቧል፡፡ በሪፖርቱ በገቢ አሰባሰብ፣ የኃይል ማንጫ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ኦፕሬሽን ማስገባት፣ በራስ አቅም ፕሮጀክቶችን የማከናወን አቅም እያደገ መምጣት፣ በኃይል ማመንጨትና ሽያጭ እንዲሁም የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነትን በማስጠበቅ በኩል በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡ ከኃይል መሰረት ልማት ግንባታ አንጻር በኃይል ማመንጫ ዘርፍ አምስት ፕሮጀክቶች እና በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ዘርፉ 31 ፕሮጀክቶች በተለያዩ ደረጃ ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ የተመረተ የኤሌክትሪክ ኃይልን ከማሳደግ አንጻር በ2017 በጀት ዓመት 29 ሺህ 480 ጊጋ ዋት ሰዓት ምርት እንደነበረ ያስታወሱት አቶ ያለውአይቀር በ2018 በጀት ዓመት 35 ሺህ 734 ጊጋ ዋት ሰዓት ማመንጨት መቻሉንና ይህም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ21 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ገልፀዋል። በ2018 በጀት ዓመት 477 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ መገኘቱን የጠቆሙት ተወካይ ሥራ አስፈፃሚው በ2017 በጀት ዓመት ከተገኘው 337 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ የ41 ነጥብ 5 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በነዳጅ እጥረትና በጸጥታ ችግር ውስጥ ሆኖ የተመዘገቡ ዓመታዊ አፈጻጸሞች ተቋሙን ከነበረበት ኪሳራ በማውጣት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ትርፍ እንዲያስመዘግብ ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ይሁን እንጂ አዲሱን የካሳ አዋጅ ሙሉ በሙሉ ለመተግበር፣ የግንባታ ሥራቸው የሚጠናቀቁ ፕሮጀክቶች በወቅቱ የካፒታላይዜሽን ሥራ ለመስራት እና ከተቋሙ አቅምና ከሀገራዊ ፍላጎት ጋር በተጣጣመ መንገድ ፕሮጀክቶችን በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት ለማከናወን እንዲሁም የባለሙያዎችን አቅም ለማጠናከር ቀጣይ ሥራ እንደሚፈልግም ተናግረዋል፡፡ በቀረበው ሪፖርት ላይ በተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በሚመለከታቸው የዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በግምገማው ላይ የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ ተግባራት እንደ ሀገር የነበረውን 15 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ያልበለጠ የኢነርጂ ምርት ወደ 35 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ማሳደግ ተችሏል፡፡ ሆኖም ከፕሮጀክት አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያልተሻገርናቸውን ችግሮች ለመፍታትና ብክነትን ለማስወገድ ኦዲት በማድረግ እንዲሁም የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም መረባረብ አለበት ብለዋል። ሁሉም ሠራተኛና የሥራ መሪ የእኔንት ስሜትን በመላበስና ሌት ተቀን በመስራት የተቋሙን መልካም ስምና ዝና በመጠበቅ በኩል ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ጠቅሰዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ሀገሪቱ ቀጣይነት ባለው ዕድገት ውስጥ የምትገኝ በመሆኑና በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እየገቡ በመሆናቸው ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደርና አሰራሩን በማዘመን በኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል። በቀጣይ በጀት ዓመት እያንዳንዷ ኪሎ ዋት ስዓት ሳትባክን ወደ ገንዘብ ለመለወጥና የፕሮጀክት አፈጻጸም ላይ አፋጣኝ ውሳኔዎችን ለመስጠት መረባረብም ይገባል ብለዋል። በበጀት ዓመቱ በብዙ ችግሮች ውስጥ በማለፍ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል። አሰራርን በማዘመንና ብክነትን በማስወገድ ኢትዮጵያን ብርሃን ለማድረግ በሚደረገው ጉዞ ሁሉም ሠራተኛ ድርሻውን በመወጣት አሻራ ማሳረፍ እንዳለበት አቅጣጫ ሰጥተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

"የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ትላልቅ ተቋማዊ ውጤቶች የተመዘገቡበት የማንሰራራት ዓመት ነበር"  ኢንጂነር አሸብር ባልቻ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኃይል መሰረተ ልማት ዘርፍ ትላልቅ ተቋማዊ ውጤቶች ማስመዝገቡን አስታወቀ። የተቋሙ የሥራ አመራሮችና ሠራተኞች የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀምን በዛሬው ዕለት መገምገም ጀምረዋል። በዚሁ ወቅት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ ግዙፍ የኃይል መሰረተ ልማቶች ተጠናቀው ወደ ኦፕሬሽን የገቡበትና ከኪሳራ ወደ ትርፍ ሽግግር የተደረገበት የማንሰራራት ዓመት ነው። በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው ስኬት ወደ ኋላ እንዳይመለስ ለማድረግ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ላይ የጋራ መግባባት በመያዝ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛ እና የሥራ አመራር በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። የ2019 በጀት ዓመት ፋይናንስ የተገኘላቸው አዳዲስ ፕሮጀክቶች የሚጀመሩበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው የኮፕ-32 ዝግጅት የሚከናወንበት ወቅት መሆኑንም ጠቅሰዋል። በመሆኑም በመንግሥትና በህዝብ የተጣለብንን ተቋማዊና ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ለኮፕ-32 ስኬት መረባረብ እንደሚገባም  አሳስበዋል። በቀጣይ የተቋም ቀን በሚል በሚከበረው ክብረ-በዓል ላይ በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የተቋሙ የሥራ ክፍሎችና ሠራተኞች የዕውቅናና ሽልማት መርሃ-ግብር እንደሚካሄድም ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 119 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ …..//….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 119 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የ
+6
ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 119 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ …..//….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 119 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና የሰው ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት ገቢው የተሰበሰበው ከኃይል ሽያጭ፣ ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ፣ ከባለፈው ዓመት ከዞረ የኃይል ሽያጭ እና ከልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች እንዲሁም ካለፈው በጀት ዓመት የዞረ ተሰብሳቢ ሂሳብ ነው፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 129 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 119 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 92 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት የሰበሰበው ገቢ ካለፈው ተመሳሳይ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 57 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በተጠናቀቀው-በጀት-ዓመት-119-ቢሊዮን-ብ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በጊዜው በማጠናቀቅ ውጤት ማስመዝገብ ይገባል ....///.... በኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የታቀዱ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት በማጠናቀቅ ውጤት
+9
በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በጊዜው በማጠናቀቅ ውጤት ማስመዝገብ ይገባል ....///.... በኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የታቀዱ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት በማጠናቀቅ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። በዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም በተሳታፊዎች ከፕሮጀክት አስተዳደር፣ ከግብዓት አቅርቦት፣ ከግዥ ሰንሰለት እና ከሰው ሀብት አስተዳደር ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል። ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እንደገለፁት የአፈፃፀም መዘግየት በሚታይባቸው ፕሮጀክቶች ላይ አስቸኳይ ውሳኔ በመስጠት፣ በፍጥነትና በጥራት ለማጠናቀቅ በትኩረት ይሰራል። የኢንጂነሪንግ ቢሮው የአማካሪነት ሚናውን እየተወጣ በመሆኑ ለውጭ አማካሪ ሊከፈል የሚችለውን ወጪ በማስቀረት ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን መቻሉን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በዕቅድ-የተያዙ-ፕሮጀክቶችን-በጊዜው-በማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ በራስ አቅም የሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች እያደጉ መጥተዋል …......///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ በራስ አቅም የሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ል
+4
ተቋሙ በራስ አቅም የሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች እያደጉ መጥተዋል …......///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ በራስ አቅም የሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደጉ መምጣታቸውን በተቋሙ የኢንጂነሪንግ እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ውድነህ የማነ የዘርፉን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት ተቋሙ የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚያሳድጉ በርካታ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን እያከናወነ ይገኛል። ዘርፉ በእነዚህ ፕሮጀክቶች ተቋማዊ አቅምና ሀገራዊ ጥሪት እንዲፈጠር በአማካሪነት እና በሥራ ተቋራጭነት በመሳተፍ  በርካታ የኃይል መሰረተ ልማቶችን አጠናቆ ወደ ኦፕሬሽን ማስገባቱን አስታውቀዋል። ​እንደ ኢንጂነር ውድነህ ገለፃ ለመጀመሪያ ጊዜ በአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሙሉ አማካሪነት እንዲሁም በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በተባባሪ አማካሪነት  መሳተፍ ተችሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-በራስ-አቅም-የሚያከናውናቸው-ፕሮጀ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎችን መሰረት በማድረግ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸው ተገለፀ ...//... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ያስቀመጣቸውን ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎ
+7
ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎችን መሰረት በማድረግ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸው ተገለፀ ...//... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ያስቀመጣቸውን ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎችን መሰረት በማድረግ የኃይል ማከፋፈያና ማስተላለፊያ ግንባታ እንዲሁም የኦፕሬሽን ሥራዎች ማከናወኑን አስታወቀ። በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ደስታለም ኃይሉ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ የብሔራዊ ግሪድ አስተማማኝነትን ለማረጋገጥ፣ የኃይል ብክነትን ለመቀነስ እና የኦፕሬሽን ልህቀትን ለማስፈን ሰፊ ተግባራት ተከናውነዋል። በበጀት ዓመቱ 31 ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ታቅዶ 18ቱ በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 5 ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ተጠናቀው ወደ ኦፕሬሽን መግባቸውን ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ስትራቴጂካዊ-የትኩረት-አቅጣጫዎችን-መሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

"ዓለም አቀፍ ልምዶችን በመቅሰም በዘርፉ የበለጠ ውጤት ማስመዝገብ ይገባል" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ .....///..... ​በዓለም ላይ ያሉ ውጤታማ የኃይል ማመንጫ አሰራሮችን በመቅሰም በጀነሬሽን ቢ
+9
"ዓለም አቀፍ ልምዶችን በመቅሰም በዘርፉ የበለጠ ውጤት ማስመዝገብ ይገባል" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ .....///..... ​በዓለም ላይ ያሉ ውጤታማ የኃይል ማመንጫ አሰራሮችን በመቅሰም በጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ። ​ዋና ሥራ አስፈጻሚው ይሄን የተናገሩት ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍን ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት መድረክ ላይ ነው። ​በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ በቀረበው ሪፖርት ላይ ከፕሮጀክት አስተዳደር፣ ከኃይል ማመንጨት አቅም፣ ከግድብ ደህንነት፣ ከፋይናንስ አጠቃቀም እና ከመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ጋር ተያይዞ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ምላሽ ተሰጥቶባዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ዓለም-አቀፍ-ልምዶችን-በመቅሰም-በዘርፉ-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም

በበጀት ዓመቱ ከ35 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መንጭቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ከ35 ሺህ 670 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨቱን
+3
በበጀት ዓመቱ ከ35 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መንጭቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ከ35 ሺህ 670 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨቱን የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። ‎ ‎የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ 38 ሺህ 124 ነጥብ 78 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 35 ሺህ 670 ነጥብ 99 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም የዕቅዱን 93 ነጥብ 6 በመቶ መሆኑንና ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል ጋር ሲነፃፀር የ21 በመቶ ዕድገት ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ኃይል ውስጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 51 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስት እና የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የ17 ነጥብ 8 እና የ7 በመቶ ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው አንስተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀምሯል ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ከተ
+7
‎ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀምሯል ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ከተቋሙ የሥራ መሪዎች ጋር በስካይ ላይት ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎በግምገማው ማስጀመሪያ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ያለ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት የሀገር ዕድገትና ብልፅግና የሚታሰብ ባለመሆኑ ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት የአመራሩ ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አንስተዋል። ‎ኢትዮጵያ ካሏት ግዙፍ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ግንባር ቀደሙ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በዚህ ተቋም ማገልገልና ለተሻለ ውጤት መትጋት እንደ ክብር ሊታይ የሚገባው ነው ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የ2018-በጀት-ዓመት-ዕቅድ-አፈጻጸም-መገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገጽ ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም