ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 553 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 406 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 161 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 553 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -3، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.69‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.00‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 150 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 332 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 553
المشتركون
-524 ساعات
+97 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
በማከፋፈያ ጣቢያዎች በተከናወኑ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ከ400 ሜጋ ዋት በላይ ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል ...…///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 5 ዓመታት በ10 የኃይል ማ
+3
በማከፋፈያ ጣቢያዎች በተከናወኑ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ከ400 ሜጋ ዋት በላይ ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል ...…///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 5 ዓመታት በ10 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ባከናወናቸው የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ ሥራዎች 439 ሜጋ ዋት ወይም 487 ነጥብ 3 ሜጋ ቮልት አምፒር ተጨማሪ ኃይል ማግኘቱን አስታወቀ። በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወልደማርያም እንደገለፁት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማረጋገጥና እያደገ የመጣውን የደንበኞች የኃይል ፍላጎት በዘላቂነት ለመመለስ በትኩረት እየሰራ ነው። ባለፉት 5 ዓመታት በለገጣፎ፣ ቦሌ ለሚ 2፣ አዳማ 2፣ ወልቂጤ፣ ሚዛን፣ ባህር ዳር፣ ኮምቦልቻ 2፣ ገፈርሳ፣ ባሌ ሮቤ እና አዲስ ዌስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ እና የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተከላ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያዎች-በተከናወኑ-የአቅም&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የማስተላለፊያ መስመሮችን ዲዛይን በሶፍትዌር በመታገዝ ለማከናወን እየተሰራ ነው .......///........ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉበትን ቦታ በዘመናዊ ሶፍትዌር ታግዞ ለመምረጥ የሚያ
+7
የማስተላለፊያ መስመሮችን ዲዛይን በሶፍትዌር በመታገዝ ለማከናወን እየተሰራ ነው .......///........ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉበትን ቦታ በዘመናዊ ሶፍትዌር ታግዞ ለመምረጥ የሚያስችል ስልጠና መሰጠቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ዲዛይን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳኛቸው ፀጋ እንዳስታወቁት ስልጠናው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አርክ ጂአይ ኤስ በተሰኘ ሶፍርዌር በመታገዝ የተሰጠው ለ30 የዲዛይንና የቅየሳ ባለሙያዎች ነው፡፡ በሁለት ዙር የተሰጠው ስልጠና መስመሮቹ ከመገንባታቸው በፊት የሚያልፍበትን አካባቢ በሶፍትዌር በመታገዝ ለመምረጥ እና ሥራውን በቀላሉ ለማከናወን የሚያስችል ብቃት ያለው ባለሙያ ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቁመዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማስተላለፊያ-መስመሮችን-ዲዛይን-በሶፍ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስና የሲስተሙን ደህንነት ለመጠበቅ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እያከናወነ ያለው የቴክኖሎጂ
አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስና የሲስተሙን ደህንነት ለመጠበቅ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እያከናወነ ያለው የቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤት እያሳየ ይገኛል።   ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች፦   ·  የብሬከር ማዘመን ሥራ፦ ከ2016 - 2018 ዓ.ም በነበሩት 3 ዓመታት  በ 60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የነባር መቆጣጠሪያ ብሬከሮችን በዘመናዊ ብሬከሮች የመተካት ሥራ ተከናውኗል።   ·   የአቅም እድገት፦ ቀደም ሲል የነበሩ ብሬከሮች ይሸከሙት የነበረው እስከ 5 ሜጋ ዋት የነበረ አቅም አሁን ባለው ማሻሻያ ከ10 እስከ 20 ሜጋ ዋት እንዲያድግ ተደርጓል። ይህም ለደንበኞች የሚቀርበውን የኃይል መጠን በእጥፍ አሳድጎታል።   ·  የቴክኖሎጂ ሽግግር፦ በዘይት ከሚሰሩና ለብልሽት ተጋላጭ ከነበሩ ነባር ብሬከሮች ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ቁጥጥር ሥርዓት በመሸጋገሩ የኃይል መቆራረጥ ርዝማኔ በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=አስተማማኝ-የኃይል-አቅርቦት-እንዲኖር-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የብሬከር ማዘመን ሥራ ተከናውኗል ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት
+3
ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የብሬከር ማዘመን ሥራ ተከናውኗል ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት ወይም የብሬከር ማዘመን ሥራ ማከናወኑን በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወልደማርያም እንደገለፁት ከ2016 እስከ 2018 በጀት ዓመት ድረስ በ75 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የመቆጣጠሪያ ብሬከር ለማዘመን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ገጠማ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በ13 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚከናወኑ የማዘመን ሥራዎችን በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝም ነው ዳይሬክተሩ ጠቆሙት። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ባለፉት-3-ዓመታት-በ60-የኃይል-ማከፋፈያ-ጣቢያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የ38 አዳዲስ ትራንስፎር
+4
የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የ38 አዳዲስ ትራንስፎርመሮችን ግዥ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወልደማርያም እንዳስታወቁት ተቋሙ ከ50 እስከ 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮችን በሦስት ዙር ለመግዛት በሂደት ላይ ነው፡፡ ትራንስፎርመሮቹ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ጭነት በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያግዙ ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያዎችን-የኃይል-ጭነት-ለማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ወዳጅነት በኃይል ዘርፍ ደመቀ! 🇪🇹🤝🇫🇷 የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ እና ለዲጂታላይዜሽን ፕሮግ
+1
የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ወዳጅነት በኃይል ዘርፍ ደመቀ! 🇪🇹🤝🇫🇷 የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ እና ለዲጂታላይዜሽን ፕሮግራም የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት መስማማቷን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡   ይህ ስምምነት ለሀገራችን ምን ይዞ ይመጣል?   🔹 ዘመናዊ አሠራር፦ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የአውቶሜሽን ሥርዓት ለማዘመን እና አዲስ የብሔራዊ ግሪድ መቆጣጠሪያ ማዕከልን ለመገንባት ይውላል።   🔹 ጂኦተርማል ኃይል፦ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል (የከርሰ ምድር እንፋሎት) ኃይል ለማመንጨት አዲስ የማዕቀፍ ስምምነት ተደርጓል።   🔹 የተሻሻለ አገልግሎት፦ የኤሌክትሪክ መቆራረጥን በ 50 በመቶ በመቀነስ ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተሻለ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር ያደርጋል።   🔹 አረንጓዴ ልማት፦ የካርቦን ልቀትን በ150 ሺህ ቶን በመቀነስ የአካባቢ ጥበቃ ጥረታችንን ያግዛል። 🌱🌍   ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ በአውሮፓ ህብረት እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲዎች (AFD) በትብብር የሚተገበር ሲሆን የሀገራችንን የኢነርጂ ዘርፍ ወደ ተሻለ ዲጂታል ከፍታ የሚያሸጋግር ነው። ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል እያበራች ትቀጥላለች! 💡🇪🇹 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የግዥ ሥርዓቱን ለማዘመን ዲጂታይዜሽን እንደ መፍትሔ! 💻📜   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዥ ሂደቶቹን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽ እና ወረቀት አልባ ለማድረግ "ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ" ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር በጋራ ያለማው አዲስ የግዥ ሲስተም ወደ ሥራ ሊገባ ነው።   ይህ ዘመናዊ ሲስተም ምን ፋይዳ አለው? 🤔   ወረቀት አልባ አሠራር፦ የተቋሙን ሥራዎች በዲጂታል ሥርዓት በመምራት የአሠራር ችግሮችን በላቀ ፍጥነት ለመፍታት ያስችላል። 📄🚫   ግልጽነትና ተጠያቂነት፦ የግዥ ሂደቱ በግልጽነትና በተጠያቂነት እንዲመራ ከማድረጉም ባለፈ ለሦስተኛ ወገን የሚፈለጉ መረጃዎችን በወቅቱ ለማቅረብ ይረዳል። 🔍✅   የሳይበር ደህንነት፦ ሲስተሙ የሳይበር ደህንነት ፍተሻ ተደርጎበትና ከነባር የግዥ ሕጎችና ደንቦች ጋር ተናቦ የሚተገበር ነው። 🛡🔒   የፕሮጀክቱ ሂደት ⏳   የ21 ወራት የቆይታ ጊዜ ያለው ይህ ፕሮጀክት የሥልጠናና የድጋፍ ሥራዎችን ጨምሮ ሲስተሙን ከሌሎች የተቋሙ አሠራሮች ጋር የማናበብ ሥራዎችን ያጠቃልላል።   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዚህ በጀት ዓመት የተለያዩ አሠራሮቹን ከማኑዋል ወደ ዲጂታል ሥርዓት የመቀየር ተግባርን በልዩ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል። 🚀✨ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን እየተሰራ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዢ ሂደቶቹን ለማዘመን ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር ያለማው ሲስተም ወ
+9
የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን እየተሰራ ነው   ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዢ ሂደቶቹን ለማዘመን ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር ያለማው ሲስተም ወደሥራ ሊገባ ነው፡፡  የለማውን የግዢ ሥርዓት ለማስጀመር በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተቋሙ እና የኩባንያው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡    በፕሮጀክቱ የማስጀመሪያ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት በተቋሙ የሚከናወኑ የተለያዩ ሥራዎች በወረቀት አልባ መንገድ እንዲመሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። ተቋሙ ግዢዎቹን ጨምሮ ሌሎች ሥራዎቹን በዲጂታል ሥርዓት ታግዞ ማከናወኑ በአሰራር ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በቀላሉ መፍትሔ ለመስጠት እና ሥራዎቹን ለማቀላጠፍ እንደሚያስችል አንስተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-የግዥ-ሥርዓት-ለማዘመን-እየተሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ብክነትን በቴክኖሎጂ መታገል - ለጠንካራ ኢኮኖሚና አስተማማኝ ብርሃን! የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትን መቀነስ የሀገርን ኢኮኖሚ መገንባት ነው! የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት (Power Loss) ከ
+1
የኃይል ብክነትን በቴክኖሎጂ መታገል - ለጠንካራ ኢኮኖሚና አስተማማኝ ብርሃን!   የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትን መቀነስ የሀገርን ኢኮኖሚ መገንባት ነው!   የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት (Power Loss) ከኢኮኖሚ ጥቅሙ ባለፈ የተቋሙን የፋይናንስ አቅምና የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚፈትን ትልቅ ጉዳይ ነው። ይህ ብክነት በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይከሰታል፡፡     ቴክኒካዊ ብክነት (Technical Loss)፦ ይህ ብክነት የሚከሰተው ኤሌክትሪክ ከማመንጫ ጣቢያው ተነስቶ ለተጠቃሚዎች በሚደርስበት ረጅም መንገድ ላይ በተለያዩ ምክንያቶች የሚባክን ኃይል ሲሆን በኢንጂነሪንግ ሥራዎች የሚፈታ  ነው። ምንጮቹ፦ በዋናነት ያረጁ የማስተላለፊያ እና የሥርጭት መስመሮች እና የትራንስፎርመሮች መጨናነቅ ናቸው።   መፍትሔው፦ መሠረተ-ልማትን ማዘመን! ስማርት ግሪድ (Smart Grid) በመጠቀም ብክነት ያለበትን መስመር ለይቶ ማወቅና ኃይልን በከፍተኛ ቮልቴጅ በማስተላለፍ በመንገድ ላይ የሚጠፋውን ኃይል መቀነስ ይቻላል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ብክነትን-በቴክኖሎጂ-መታገል-ለጠ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት ለህዳሴው ግድብ ደህንነት! 🌱💧 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ9 ወራት ውስጥ 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለኃይል ማመንጨት ተግባር ጥቅም ላይ አውሏል! 🌊⚡️ የ
+2
የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት ለህዳሴው ግድብ ደህንነት! 🌱💧 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ9 ወራት ውስጥ 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለኃይል ማመንጨት ተግባር ጥቅም ላይ አውሏል! 🌊⚡️ የግድቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ከማል አሕመድ እንዳስታወቁት ግድቡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ በመጠቀም 13 ሺህ 778 ነጥብ 37 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ችሏል። ይህም ለኃይል ማመንጨት የታቀደውን የውሃ አጠቃቀም 84.9 በመቶ አፈጻጸም ላይ አድርሶታል። ታሪካዊው የውሃ ፍሰት እና የወደፊት ተስፋ   • ከታቀደው በላይ የነበረ የውሃ መጠን፦ ወደ ግድቡ ይገባል ተብሎ የታቀደው 46 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ቢሆንም በዓመቱ 57.7 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ገብቷል (የ24.4% ብልጫ)። • የክረምት በረከት፦ ከጠቅላላ የውሃ ገቢ ውስጥ 50.5 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የሚሆነው በሐምሌ፣ ነሐሴ፣ መስከረም እና ጥቅምት ወራት የገባ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአረንጓዴአሻራትሩፋትለህዳሴውግድብደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የሀገር ሀብትን በመቆጠብ ለቀጣይ ትውልድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረብን ነው! 🇪🇹 ......///...... የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለሙያዎች ባለፉት 9 ወራት በራስ አቅም ባከናወኗ
የሀገር ሀብትን በመቆጠብ ለቀጣይ ትውልድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረብን ነው! 🇪🇹  ......///...... የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለሙያዎች ባለፉት 9 ወራት በራስ አቅም ባከናወኗቸው የጥገና ሥራዎች በከ7.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪን አድነዋል!   የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ  ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አይናለም ወ/ሚካኤል አእንዳስታወቁት ይህ ስኬት የተመዘገበው ጣቢያው የቴክኖሎጂ ሽግግርንና የባለሙያዎችን ክህሎት መሠረት በማድረግ በወሰደው እርምጃ ነው።   የተመዘገቡት ዋና ዋና ስኬቶች፦   ✅  ራስን መቻል፦ የስዊችጊር፣ የስዊችያርድ፣ የኮሙዩኒኬሽን መቆጣጠሪያዎች እና የስርጭት መስመሮችን በራስ ባለሙያዎች በመጠገን ከፍተኛ ወጪ ተቆጥቧል።   ✅  የቴክኖሎጂ ሽግግር፦ በካርዶች፣ በስሊፕሪንግ እና በአይ.ጂ.ቢ.ቲ (IGBT) የጥገና ሥራዎች ወቅት የክህሎት ሽግግር በማድረግ አዳዲስ ባለሙያዎችን ማፍራት ተችሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የሀገር-ሀብትን-በመቆጠብ-ለቀጣይ-ትውልድ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የገነባው የዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን አሸነፈ ------///------- የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ
+1
ታላቁ  የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የገነባው የዊቢልድ  ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን አሸነፈ ------///------- የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን  (Samoter 2026 Innovation Award) አስገኝቷል።   በጣሊያን በተካሄደው የሳሞተር ዓለም አቀፍ የግንባታ ማሽነሪዎች ኤግዚቢሽን ላይ የተሰጠው ይህ ሽልማት  የፕሮጀክቱን ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ፋይዳ እንዲሁም የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የኃይል ዘርፍ ገጽታ በመለወጥ ረገድ ያለውን ጠቀሜታ የሚያሳይ ነው። በ1965 የተመሰረተው የሳሞተር የፈጠራ ሽልማት በአውሮፓ የግንባታ ምህንድስና ዘርፍ ውስጥ ረጅም ዕድሜ ካላቸውና ታዋቂ ከሆኑ የክብር ሽልማቶች አንዱ ሲሆን  ሽልማቱ በኃይል መሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ልማት ውስጥ አነስተኛ የቴክኒክ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ አዲስና አብዮታዊ ለውጥን ያመጡ ፕሮጀክቶችን እውቅና ለመስጠት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብን-የገነባው&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥ ስምምነት ተፈራረመ …..///…… የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ዘላቂ አገልግሎትና የኃይል ምርት አስተማማኝ ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ስም
+3
ተቋሙ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥ ስምምነት ተፈራረመ …..///…… የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ዘላቂ አገልግሎትና የኃይል ምርት አስተማማኝ ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱት የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ግሩፕ የሃይድሮ ሰርቪስ ዳይሬክተር ዋን ጂይ ናቸው፡፡ በቻይና ሻንጋይ በሚገኘው የቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ዋና መሥሪያ ቤት የተከናወነው የመግባቢያ ስምምነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዓለም አቀፍ የውሃ ኃይል መፍትሔዎች አቅራቢ ከሆነው ቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ኩባንያ የረጅም ጊዜ የጥገና እና የቴክኒክ ድጋፍ አገልግሎት ለማግኘት ያስችለዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለታላቁ-ህዳሴ-ግድብ-የቴክኒክ-ድጋፍ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

"የተቋሙን መሠረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነት እንወጣለን" የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች …......///…….... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን
+9
"የተቋሙን መሠረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነት እንወጣለን" የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች …......///…….... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል እና ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰጣቸውን አደራ በኃላፊነት እንደሚወጡ በሪጅኖች የተመደቡ የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች አረጋገጡ። ከፍተኛ መኮንኖች በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚፈጸሙ ጉዳቶችን በመከላከል ረገድ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያከናወኗቸውን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተቋሙን ንብረቶች በመጠበቅ እና የሚፈጸሙ ስርቆቶችን በመከላከል እንዲሁም ስርቆት የሚበዛባቸውን የስጋት ቀጣናዎች በመከታተልና በሙከራ ደረጃ በማህበረሰቡ እንዲጠበቁ በማድረግ፣ ከአካባቢ የመስተዳድር አካላትና ከማህበረሰቡ ጋር የቅድመ መከላከል የግንዛቤ ሥራዎችን በማጠናከር የአስተሳሰብ ለውጦች እንዲመጡ ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-መሠረተ-ልማት-ደህንነት-ለማስጠ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ጣቢያው አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ነው ‎….....///…..…. ‎የጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚ
+6
ጣቢያው አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ነው ‎….....///…..…. ‎የጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌዲዮን አበራ እንደገለፁት የጎዴ ማከፋፈያ ጣቢያ ከራይቱ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኝበት አንድ ገቢ መስመር እንዲሁም በ132 እና 33 ኪሎ ቮልት ለተለያዩ አካባቢዎች ኃይል የሚሰጥበት ሰባት ወጪ መስመሮች አሉት። ‎ ‎ጣቢያው በ132 ኪሎ ቮልት ለቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያ፣ በ33 ኪሎ ቮልት ለጎዴ፣ ሀዳዋይ እና አዳዲሌይ ከተሞች እና በዙሪያው ለሚገኙ አካባቢዎች እንዲሁም ለሁለት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጣቢያው-አዲስ-ለሚገነባው-የማዳበሪያ-ፋብ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ ይቀጥላል …......///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በዘላቂነት ለመከ
+9
በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ ይቀጥላል …......///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በዘላቂነት ለመከላከል የሚደረገውን ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋማዊ ደህንነትና አስተዳደራዊ ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው ከሪጅን ኃላፊዎችና ከመሠረተ ልማት ደህንነት የጥበቃ ከፍተኛ መኮንኖች ጋር በኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ደህንነት ዙሪያ የተከናወኑ ሥራዎችን አስመልክቶ ለሦስት ቀናት በሀዋሳ ሲያካሂድ የቆየውን ግምገማ አጠናቋል። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሺፋ በሪፖርቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት መምሪያው ከተደራጀ አጭር ጊዜ ቢሆነውም የተቋቋመበትን ተልዕኮ በሚገባ እየተወጣ ይገኛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-ንብረቶች-ላይ-የሚደርሱ-ጉዳቶችን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል ….....///….... በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ኦዳ በተባለ አካባቢ ከትናንት በስቲያ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝና
+6
ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል ….....///….... በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ኦዳ በተባለ አካባቢ ከትናንት በስቲያ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ስድስት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በመጣሉ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንዳስታወቁት ጉዳቱ የደረሰው ከመልካ ዋከና - ራይቱ - ጎዴ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ነው። መስመሩ ለጎዴ እና ቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚሰጥ ሲሆን ከእነዚህ ጣቢያዎች ኃይል የሚያገኙ የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ኃይል መቋረጡን ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከባድ-ንፋስ-ቀላቅሎ-የጣለ-ዝናብ-ለኃይል-መ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ሥልጠናው የፕሮጀክቶችን አካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ስጋቶችን ለመከላከል ያግዛል ‎…....///.….. በዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚደረጉ የፕራይም - 1 ፕሮጀክቶች ላይ ‎በአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ዙሪያ የተሰጠው ሥልጠና የአካባቢያዊና ማህበራዊ ስጋቶችን ለመከላከል እንደሚያግዝ የስልጠናው ተሳታፊ ባለሙያዎች ገለጹ። ‎ ‎የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ቡድን ጋር በመተባበር በባንኩ ፋይናንስ ተደርገው በሚሰሩ ፕሮጀክት ላይ ለሚሰማሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና እና የደቡብ ሱዳን የአካባቢያዊ፣ የማህበራዊ እና የጤና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ ‎ ‎በተቋሙ የፕራይም - 1 ፕሮጀክቶች የኢንቫሮሜንታል ባለሙያ የሆነችው ወ/ሪት አዝመራ ተስፋዬ እንደገለጸችው ፕሮጀክቶች በሚተገበሩበት ወቅት ከአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ጋር በተያያዘ የተለያዩ ተግዳሮቶች ያጋጥማሉ። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሥልጠናው-የፕሮጀክቶችን-አካባቢያዊና-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4