ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 551 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 406,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 161

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 551 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -3,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.69%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.00% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 150 次浏览,首日通常累积 2 332 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 551
订阅者
-524 小时
+97
-330
帖子存档
በማከፋፈያ ጣቢያዎች በተከናወኑ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ከ400 ሜጋ ዋት በላይ ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል ...…///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 5 ዓመታት በ10 የኃይል ማ
+3
በማከፋፈያ ጣቢያዎች በተከናወኑ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ከ400 ሜጋ ዋት በላይ ተጨማሪ ኃይል ማግኘት ተችሏል ...…///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 5 ዓመታት በ10 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ባከናወናቸው የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ ሥራዎች 439 ሜጋ ዋት ወይም 487 ነጥብ 3 ሜጋ ቮልት አምፒር ተጨማሪ ኃይል ማግኘቱን አስታወቀ። በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወልደማርያም እንደገለፁት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝነትን ለማረጋገጥና እያደገ የመጣውን የደንበኞች የኃይል ፍላጎት በዘላቂነት ለመመለስ በትኩረት እየሰራ ነው። ባለፉት 5 ዓመታት በለገጣፎ፣ ቦሌ ለሚ 2፣ አዳማ 2፣ ወልቂጤ፣ ሚዛን፣ ባህር ዳር፣ ኮምቦልቻ 2፣ ገፈርሳ፣ ባሌ ሮቤ እና አዲስ ዌስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ እና የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተከላ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያዎች-በተከናወኑ-የአቅም&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የማስተላለፊያ መስመሮችን ዲዛይን በሶፍትዌር በመታገዝ ለማከናወን እየተሰራ ነው .......///........ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉበትን ቦታ በዘመናዊ ሶፍትዌር ታግዞ ለመምረጥ የሚያ
+7
የማስተላለፊያ መስመሮችን ዲዛይን በሶፍትዌር በመታገዝ ለማከናወን እየተሰራ ነው .......///........ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉበትን ቦታ በዘመናዊ ሶፍትዌር ታግዞ ለመምረጥ የሚያስችል ስልጠና መሰጠቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ዲዛይን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳኛቸው ፀጋ እንዳስታወቁት ስልጠናው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር አርክ ጂአይ ኤስ በተሰኘ ሶፍርዌር በመታገዝ የተሰጠው ለ30 የዲዛይንና የቅየሳ ባለሙያዎች ነው፡፡ በሁለት ዙር የተሰጠው ስልጠና መስመሮቹ ከመገንባታቸው በፊት የሚያልፍበትን አካባቢ በሶፍትዌር በመታገዝ ለመምረጥ እና ሥራውን በቀላሉ ለማከናወን የሚያስችል ብቃት ያለው ባለሙያ ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቁመዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማስተላለፊያ-መስመሮችን-ዲዛይን-በሶፍ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም

አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስና የሲስተሙን ደህንነት ለመጠበቅ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እያከናወነ ያለው የቴክኖሎጂ
አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የተከናወኑ ሥራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስና የሲስተሙን ደህንነት ለመጠበቅ በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እያከናወነ ያለው የቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤት እያሳየ ይገኛል።   ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች፦   ·  የብሬከር ማዘመን ሥራ፦ ከ2016 - 2018 ዓ.ም በነበሩት 3 ዓመታት  በ 60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የነባር መቆጣጠሪያ ብሬከሮችን በዘመናዊ ብሬከሮች የመተካት ሥራ ተከናውኗል።   ·   የአቅም እድገት፦ ቀደም ሲል የነበሩ ብሬከሮች ይሸከሙት የነበረው እስከ 5 ሜጋ ዋት የነበረ አቅም አሁን ባለው ማሻሻያ ከ10 እስከ 20 ሜጋ ዋት እንዲያድግ ተደርጓል። ይህም ለደንበኞች የሚቀርበውን የኃይል መጠን በእጥፍ አሳድጎታል።   ·  የቴክኖሎጂ ሽግግር፦ በዘይት ከሚሰሩና ለብልሽት ተጋላጭ ከነበሩ ነባር ብሬከሮች ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ቁጥጥር ሥርዓት በመሸጋገሩ የኃይል መቆራረጥ ርዝማኔ በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።   ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=አስተማማኝ-የኃይል-አቅርቦት-እንዲኖር-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የብሬከር ማዘመን ሥራ ተከናውኗል ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት
+3
ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የብሬከር ማዘመን ሥራ ተከናውኗል ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የመቆጣጠሪያ ሥርዓት ወይም የብሬከር ማዘመን ሥራ ማከናወኑን በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወልደማርያም እንደገለፁት ከ2016 እስከ 2018 በጀት ዓመት ድረስ በ75 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የመቆጣጠሪያ ብሬከር ለማዘመን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ባለፉት 3 ዓመታት በ60 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ገጠማ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በ13 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚከናወኑ የማዘመን ሥራዎችን በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝም ነው ዳይሬክተሩ ጠቆሙት። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ባለፉት-3-ዓመታት-በ60-የኃይል-ማከፋፈያ-ጣቢያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የ38 አዳዲስ ትራንስፎር
+4
የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል ጭነት ለማቃለል የ38 አዳዲስ ትራንስፎርመሮችን ግዥ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ወልደማርያም እንዳስታወቁት ተቋሙ ከ50 እስከ 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮችን በሦስት ዙር ለመግዛት በሂደት ላይ ነው፡፡ ትራንስፎርመሮቹ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ጭነት በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያግዙ ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያዎችን-የኃይል-ጭነት-ለማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ወዳጅነት በኃይል ዘርፍ ደመቀ! 🇪🇹🤝🇫🇷 የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ እና ለዲጂታላይዜሽን ፕሮግ
+1
የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ ወዳጅነት በኃይል ዘርፍ ደመቀ! 🇪🇹🤝🇫🇷 የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ እና ለዲጂታላይዜሽን ፕሮግራም የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት መስማማቷን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡   ይህ ስምምነት ለሀገራችን ምን ይዞ ይመጣል?   🔹 ዘመናዊ አሠራር፦ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የአውቶሜሽን ሥርዓት ለማዘመን እና አዲስ የብሔራዊ ግሪድ መቆጣጠሪያ ማዕከልን ለመገንባት ይውላል።   🔹 ጂኦተርማል ኃይል፦ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል (የከርሰ ምድር እንፋሎት) ኃይል ለማመንጨት አዲስ የማዕቀፍ ስምምነት ተደርጓል።   🔹 የተሻሻለ አገልግሎት፦ የኤሌክትሪክ መቆራረጥን በ 50 በመቶ በመቀነስ ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተሻለ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር ያደርጋል።   🔹 አረንጓዴ ልማት፦ የካርቦን ልቀትን በ150 ሺህ ቶን በመቀነስ የአካባቢ ጥበቃ ጥረታችንን ያግዛል። 🌱🌍   ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ በአውሮፓ ህብረት እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲዎች (AFD) በትብብር የሚተገበር ሲሆን የሀገራችንን የኢነርጂ ዘርፍ ወደ ተሻለ ዲጂታል ከፍታ የሚያሸጋግር ነው። ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል እያበራች ትቀጥላለች! 💡🇪🇹 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም

የግዥ ሥርዓቱን ለማዘመን ዲጂታይዜሽን እንደ መፍትሔ! 💻📜   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዥ ሂደቶቹን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽ እና ወረቀት አልባ ለማድረግ "ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ" ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር በጋራ ያለማው አዲስ የግዥ ሲስተም ወደ ሥራ ሊገባ ነው።   ይህ ዘመናዊ ሲስተም ምን ፋይዳ አለው? 🤔   ወረቀት አልባ አሠራር፦ የተቋሙን ሥራዎች በዲጂታል ሥርዓት በመምራት የአሠራር ችግሮችን በላቀ ፍጥነት ለመፍታት ያስችላል። 📄🚫   ግልጽነትና ተጠያቂነት፦ የግዥ ሂደቱ በግልጽነትና በተጠያቂነት እንዲመራ ከማድረጉም ባለፈ ለሦስተኛ ወገን የሚፈለጉ መረጃዎችን በወቅቱ ለማቅረብ ይረዳል። 🔍✅   የሳይበር ደህንነት፦ ሲስተሙ የሳይበር ደህንነት ፍተሻ ተደርጎበትና ከነባር የግዥ ሕጎችና ደንቦች ጋር ተናቦ የሚተገበር ነው። 🛡🔒   የፕሮጀክቱ ሂደት ⏳   የ21 ወራት የቆይታ ጊዜ ያለው ይህ ፕሮጀክት የሥልጠናና የድጋፍ ሥራዎችን ጨምሮ ሲስተሙን ከሌሎች የተቋሙ አሠራሮች ጋር የማናበብ ሥራዎችን ያጠቃልላል።   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዚህ በጀት ዓመት የተለያዩ አሠራሮቹን ከማኑዋል ወደ ዲጂታል ሥርዓት የመቀየር ተግባርን በልዩ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል። 🚀✨ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን እየተሰራ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዢ ሂደቶቹን ለማዘመን ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር ያለማው ሲስተም ወ
+9
የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን እየተሰራ ነው   ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዢ ሂደቶቹን ለማዘመን ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር ያለማው ሲስተም ወደሥራ ሊገባ ነው፡፡  የለማውን የግዢ ሥርዓት ለማስጀመር በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተቋሙ እና የኩባንያው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡    በፕሮጀክቱ የማስጀመሪያ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት በተቋሙ የሚከናወኑ የተለያዩ ሥራዎች በወረቀት አልባ መንገድ እንዲመሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። ተቋሙ ግዢዎቹን ጨምሮ ሌሎች ሥራዎቹን በዲጂታል ሥርዓት ታግዞ ማከናወኑ በአሰራር ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በቀላሉ መፍትሔ ለመስጠት እና ሥራዎቹን ለማቀላጠፍ እንደሚያስችል አንስተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-የግዥ-ሥርዓት-ለማዘመን-እየተሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ብክነትን በቴክኖሎጂ መታገል - ለጠንካራ ኢኮኖሚና አስተማማኝ ብርሃን! የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትን መቀነስ የሀገርን ኢኮኖሚ መገንባት ነው! የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት (Power Loss) ከ
+1
የኃይል ብክነትን በቴክኖሎጂ መታገል - ለጠንካራ ኢኮኖሚና አስተማማኝ ብርሃን!   የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትን መቀነስ የሀገርን ኢኮኖሚ መገንባት ነው!   የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት (Power Loss) ከኢኮኖሚ ጥቅሙ ባለፈ የተቋሙን የፋይናንስ አቅምና የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚፈትን ትልቅ ጉዳይ ነው። ይህ ብክነት በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይከሰታል፡፡     ቴክኒካዊ ብክነት (Technical Loss)፦ ይህ ብክነት የሚከሰተው ኤሌክትሪክ ከማመንጫ ጣቢያው ተነስቶ ለተጠቃሚዎች በሚደርስበት ረጅም መንገድ ላይ በተለያዩ ምክንያቶች የሚባክን ኃይል ሲሆን በኢንጂነሪንግ ሥራዎች የሚፈታ  ነው። ምንጮቹ፦ በዋናነት ያረጁ የማስተላለፊያ እና የሥርጭት መስመሮች እና የትራንስፎርመሮች መጨናነቅ ናቸው።   መፍትሔው፦ መሠረተ-ልማትን ማዘመን! ስማርት ግሪድ (Smart Grid) በመጠቀም ብክነት ያለበትን መስመር ለይቶ ማወቅና ኃይልን በከፍተኛ ቮልቴጅ በማስተላለፍ በመንገድ ላይ የሚጠፋውን ኃይል መቀነስ ይቻላል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ብክነትን-በቴክኖሎጂ-መታገል-ለጠ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት ለህዳሴው ግድብ ደህንነት! 🌱💧 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ9 ወራት ውስጥ 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለኃይል ማመንጨት ተግባር ጥቅም ላይ አውሏል! 🌊⚡️ የ
+2
የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት ለህዳሴው ግድብ ደህንነት! 🌱💧 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ9 ወራት ውስጥ 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለኃይል ማመንጨት ተግባር ጥቅም ላይ አውሏል! 🌊⚡️ የግድቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ከማል አሕመድ እንዳስታወቁት ግድቡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ በመጠቀም 13 ሺህ 778 ነጥብ 37 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ችሏል። ይህም ለኃይል ማመንጨት የታቀደውን የውሃ አጠቃቀም 84.9 በመቶ አፈጻጸም ላይ አድርሶታል። ታሪካዊው የውሃ ፍሰት እና የወደፊት ተስፋ   • ከታቀደው በላይ የነበረ የውሃ መጠን፦ ወደ ግድቡ ይገባል ተብሎ የታቀደው 46 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ቢሆንም በዓመቱ 57.7 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ገብቷል (የ24.4% ብልጫ)። • የክረምት በረከት፦ ከጠቅላላ የውሃ ገቢ ውስጥ 50.5 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የሚሆነው በሐምሌ፣ ነሐሴ፣ መስከረም እና ጥቅምት ወራት የገባ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአረንጓዴአሻራትሩፋትለህዳሴውግድብደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የሀገር ሀብትን በመቆጠብ ለቀጣይ ትውልድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረብን ነው! 🇪🇹 ......///...... የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለሙያዎች ባለፉት 9 ወራት በራስ አቅም ባከናወኗ
የሀገር ሀብትን በመቆጠብ ለቀጣይ ትውልድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረብን ነው! 🇪🇹  ......///...... የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለሙያዎች ባለፉት 9 ወራት በራስ አቅም ባከናወኗቸው የጥገና ሥራዎች በከ7.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪን አድነዋል!   የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ  ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አይናለም ወ/ሚካኤል አእንዳስታወቁት ይህ ስኬት የተመዘገበው ጣቢያው የቴክኖሎጂ ሽግግርንና የባለሙያዎችን ክህሎት መሠረት በማድረግ በወሰደው እርምጃ ነው።   የተመዘገቡት ዋና ዋና ስኬቶች፦   ✅  ራስን መቻል፦ የስዊችጊር፣ የስዊችያርድ፣ የኮሙዩኒኬሽን መቆጣጠሪያዎች እና የስርጭት መስመሮችን በራስ ባለሙያዎች በመጠገን ከፍተኛ ወጪ ተቆጥቧል።   ✅  የቴክኖሎጂ ሽግግር፦ በካርዶች፣ በስሊፕሪንግ እና በአይ.ጂ.ቢ.ቲ (IGBT) የጥገና ሥራዎች ወቅት የክህሎት ሽግግር በማድረግ አዳዲስ ባለሙያዎችን ማፍራት ተችሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የሀገር-ሀብትን-በመቆጠብ-ለቀጣይ-ትውልድ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የገነባው የዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን አሸነፈ ------///------- የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ
+1
ታላቁ  የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የገነባው የዊቢልድ  ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን አሸነፈ ------///------- የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን  (Samoter 2026 Innovation Award) አስገኝቷል።   በጣሊያን በተካሄደው የሳሞተር ዓለም አቀፍ የግንባታ ማሽነሪዎች ኤግዚቢሽን ላይ የተሰጠው ይህ ሽልማት  የፕሮጀክቱን ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ፋይዳ እንዲሁም የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የኃይል ዘርፍ ገጽታ በመለወጥ ረገድ ያለውን ጠቀሜታ የሚያሳይ ነው። በ1965 የተመሰረተው የሳሞተር የፈጠራ ሽልማት በአውሮፓ የግንባታ ምህንድስና ዘርፍ ውስጥ ረጅም ዕድሜ ካላቸውና ታዋቂ ከሆኑ የክብር ሽልማቶች አንዱ ሲሆን  ሽልማቱ በኃይል መሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ልማት ውስጥ አነስተኛ የቴክኒክ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ አዲስና አብዮታዊ ለውጥን ያመጡ ፕሮጀክቶችን እውቅና ለመስጠት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብን-የገነባው&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥ ስምምነት ተፈራረመ …..///…… የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ዘላቂ አገልግሎትና የኃይል ምርት አስተማማኝ ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ስም
+3
ተቋሙ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥ ስምምነት ተፈራረመ …..///…… የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ዘላቂ አገልግሎትና የኃይል ምርት አስተማማኝ ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱት የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ግሩፕ የሃይድሮ ሰርቪስ ዳይሬክተር ዋን ጂይ ናቸው፡፡ በቻይና ሻንጋይ በሚገኘው የቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ዋና መሥሪያ ቤት የተከናወነው የመግባቢያ ስምምነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዓለም አቀፍ የውሃ ኃይል መፍትሔዎች አቅራቢ ከሆነው ቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ኩባንያ የረጅም ጊዜ የጥገና እና የቴክኒክ ድጋፍ አገልግሎት ለማግኘት ያስችለዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለታላቁ-ህዳሴ-ግድብ-የቴክኒክ-ድጋፍ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

"የተቋሙን መሠረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነት እንወጣለን" የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች …......///…….... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን
+9
"የተቋሙን መሠረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነት እንወጣለን" የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች …......///…….... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል እና ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰጣቸውን አደራ በኃላፊነት እንደሚወጡ በሪጅኖች የተመደቡ የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች አረጋገጡ። ከፍተኛ መኮንኖች በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚፈጸሙ ጉዳቶችን በመከላከል ረገድ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያከናወኗቸውን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተቋሙን ንብረቶች በመጠበቅ እና የሚፈጸሙ ስርቆቶችን በመከላከል እንዲሁም ስርቆት የሚበዛባቸውን የስጋት ቀጣናዎች በመከታተልና በሙከራ ደረጃ በማህበረሰቡ እንዲጠበቁ በማድረግ፣ ከአካባቢ የመስተዳድር አካላትና ከማህበረሰቡ ጋር የቅድመ መከላከል የግንዛቤ ሥራዎችን በማጠናከር የአስተሳሰብ ለውጦች እንዲመጡ ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-መሠረተ-ልማት-ደህንነት-ለማስጠ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ጣቢያው አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ነው ‎….....///…..…. ‎የጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚ
+6
ጣቢያው አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ነው ‎….....///…..…. ‎የጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌዲዮን አበራ እንደገለፁት የጎዴ ማከፋፈያ ጣቢያ ከራይቱ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኝበት አንድ ገቢ መስመር እንዲሁም በ132 እና 33 ኪሎ ቮልት ለተለያዩ አካባቢዎች ኃይል የሚሰጥበት ሰባት ወጪ መስመሮች አሉት። ‎ ‎ጣቢያው በ132 ኪሎ ቮልት ለቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያ፣ በ33 ኪሎ ቮልት ለጎዴ፣ ሀዳዋይ እና አዳዲሌይ ከተሞች እና በዙሪያው ለሚገኙ አካባቢዎች እንዲሁም ለሁለት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጣቢያው-አዲስ-ለሚገነባው-የማዳበሪያ-ፋብ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ ይቀጥላል …......///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በዘላቂነት ለመከ
+9
በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ ይቀጥላል …......///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በዘላቂነት ለመከላከል የሚደረገውን ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋማዊ ደህንነትና አስተዳደራዊ ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው ከሪጅን ኃላፊዎችና ከመሠረተ ልማት ደህንነት የጥበቃ ከፍተኛ መኮንኖች ጋር በኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ደህንነት ዙሪያ የተከናወኑ ሥራዎችን አስመልክቶ ለሦስት ቀናት በሀዋሳ ሲያካሂድ የቆየውን ግምገማ አጠናቋል። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሺፋ በሪፖርቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት መምሪያው ከተደራጀ አጭር ጊዜ ቢሆነውም የተቋቋመበትን ተልዕኮ በሚገባ እየተወጣ ይገኛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-ንብረቶች-ላይ-የሚደርሱ-ጉዳቶችን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል ….....///….... በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ኦዳ በተባለ አካባቢ ከትናንት በስቲያ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝና
+6
ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል ….....///….... በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ኦዳ በተባለ አካባቢ ከትናንት በስቲያ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ስድስት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በመጣሉ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንዳስታወቁት ጉዳቱ የደረሰው ከመልካ ዋከና - ራይቱ - ጎዴ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ነው። መስመሩ ለጎዴ እና ቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚሰጥ ሲሆን ከእነዚህ ጣቢያዎች ኃይል የሚያገኙ የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ኃይል መቋረጡን ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከባድ-ንፋስ-ቀላቅሎ-የጣለ-ዝናብ-ለኃይል-መ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ሥልጠናው የፕሮጀክቶችን አካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ስጋቶችን ለመከላከል ያግዛል ‎…....///.….. በዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚደረጉ የፕራይም - 1 ፕሮጀክቶች ላይ ‎በአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ዙሪያ የተሰጠው ሥልጠና የአካባቢያዊና ማህበራዊ ስጋቶችን ለመከላከል እንደሚያግዝ የስልጠናው ተሳታፊ ባለሙያዎች ገለጹ። ‎ ‎የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ቡድን ጋር በመተባበር በባንኩ ፋይናንስ ተደርገው በሚሰሩ ፕሮጀክት ላይ ለሚሰማሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና እና የደቡብ ሱዳን የአካባቢያዊ፣ የማህበራዊ እና የጤና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ ‎ ‎በተቋሙ የፕራይም - 1 ፕሮጀክቶች የኢንቫሮሜንታል ባለሙያ የሆነችው ወ/ሪት አዝመራ ተስፋዬ እንደገለጸችው ፕሮጀክቶች በሚተገበሩበት ወቅት ከአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ጋር በተያያዘ የተለያዩ ተግዳሮቶች ያጋጥማሉ። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሥልጠናው-የፕሮጀክቶችን-አካባቢያዊና-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4