fa
Feedback
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

رفتن به کانال در Telegram

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

کانال Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 24 930 مشترک است و جایگاه 9 722 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 1 343 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 24 930 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -198 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 6 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید شده (به صورت رسمی توسط تلگرام)
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.52% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.24% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 372 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 307 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

24 930
مشترکین
+624 ساعت
-357 روز
-19830 روز
آرشیو پست ها
ከ80 በመቶ በላይ የሀገር ውስጥ ግብዓትን የሚጠቀመው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመረቀ +++++++++++++++ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካልና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትል
+6
ከ80 በመቶ በላይ የሀገር ውስጥ ግብዓትን የሚጠቀመው የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ ተመረቀ +++++++++++++++ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ጉዟችን አካልና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ እመርታ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞጆ የተገነባውን የግራንዴር ሴራሚክ ፋብሪካ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል። በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን መሰል ፋብሪካዎች ግንባታ፣ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ በመላ ሀገሪቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በተግባር ያረጋገጠ ነው ብለዋል። ‎ ‎​ፋብሪካው የዓለም ዓቀፍ ጥራትና ተወዳዳሪነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሴራሚክ ምርቶችን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ለምርቱ የሚያስፈልጉትን ጥሬ ዕቃዎች ከ80 በመቶ በላይ ከሀገር ውስጥ ዐቅም ያገኛል። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብትና እምቅ ጸጋ የመጠቀም ብቃቷን ከመገንባቱ ባሻገር፣ ከውጭ ገቢ ምርቶች ላይ ያለንን ጥገኝነት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል ሲሉም ገልጸዋል። #ሴራሚክስ #ግራንዴርሴራሚክፋብሪካ #ተኪምርት #ceramics #የኢትዮጵያአየርመንገድ #MadeInEthiopia #EthiopiaDelivers

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ኢትዮጵያን በመረጃ ላይ የተመሠረተ የልማት መጻኢ ዕድል የሚያሳየው ''በመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት'' ብሔራዊ ጉባኤ ላይ
+9
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ኢትዮጵያን በመረጃ ላይ የተመሠረተ የልማት መጻኢ ዕድል የሚያሳየው ''በመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት'' ብሔራዊ ጉባኤ ላይ የቀረቡ የብሔራዊ ዕቅድና ስታቲስቲክስ ዳሽቦርዶች (የመረጃ መከታተያ ሰሌዳዎች) እና ኤግዚቢሽን ያደረጉት ጉብኝት። #PMOEthiopia

#አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ https://press.et/e-paper
#አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ https://press.et/e-paper

''የማዳበሪያ ፋብሪካው በሚጠናቀቅበት ወቅት የሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ያጎለብታል፤ ጥገኝነት ይቀንሳል፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮቻችንን ይደግፋል። ለኢንቨስትመንትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ አ
''የማዳበሪያ ፋብሪካው በሚጠናቀቅበት ወቅት የሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ያጎለብታል፤ ጥገኝነት ይቀንሳል፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮቻችንን ይደግፋል። ለኢንቨስትመንትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ አዳዲስ ዕድሎችን ይከፍታል'' - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #ጋዜጣፕላስ #fertilizerindustry #productivity #ተኪምርት #gazetteplus #dangoterefinery #Dangote

በምግብ ራስን መቻል ዋነኛ አጀንዳችን ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) #dangotecement #fertilizerindustry #EthiopiaDelivers #productivity #ጋዜጣፕላስ

የማዳበሪያ ፋብሪካው የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ እድገትና በኢኮኖሚ ራስ የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ እድገትና በኢኮኖሚ ራስ የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት እንዳሰታወቁት፤ ባለፈው አመት ነሐሴ ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመሆን በአመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ ማዳበሪያ የማምረት አቅም ያለው ፋብሪካ ለማቋቋም ትልቅ የባለድርሻ ስምምነት አድርገን ነበር። በያዝነው አመት ጥቅምት ወር ደግሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ በይፋ ጀምረናል። ይኽ ሥራ ከመሠረተ ልማት ግንባታም በላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንደስትሪ እድገት እና በኢኮኖሚ ራስ የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቬስትመንት መሆኑን ገልጸዋል። የማዳበሪያ ፋብሪካው በሚጠናቀቅበት ወቅት የሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ያጎለብታል፣ ከውጭ በሚገባ ማዳበሪያ ላይ ያለውን ጥገኝነት ይቀንሳል፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አርሶአደሮቻችንን ይደግፋል። ለኢንቨስትመንትና የሥራ ዕድል ፈጠራም አዳዲስ እድሎችን ይከፍታል። ዛሬ ማለዳ ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በጎዴ ተገኝቼ ሥራው የደረሰበትን ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክት ስፍራውን ጎብኝቻለሁ። በመላው የፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደቱ ፍጥነት አበረታች ነው። ይኽን ግዙፍ እና እጅግ ጠቃሚ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለመፈፀም ያለውን ቁርጠኝነት እና ትብብር በሚያንፀባርቅ ሁኔታ በተለያዩ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ያሉት ግንባታዎች በእቅዳችን መሠረት እየተጓዙ ይገኛሉም ብለዋል። #ግብዓትአቅርቦት #PMOEthiopia #DigitalTransformation #FinancialFreedom #fertilizerindustry

🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ። 🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከ
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ። 🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ። ✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል። 📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ:: 👇🏾👇🏾👇🏾 https://t.me/+G7KxcdEwTKBjYzg6

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጂቡቲ የነበራቸውን ቆይታ በማጠናቀቅ ዛሬ ከሰአት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። #PMOEthiopia #Djibouti #ethiodjibouti #diplomac
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጂቡቲ የነበራቸውን ቆይታ በማጠናቀቅ ዛሬ ከሰአት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። #PMOEthiopia #Djibouti #ethiodjibouti #diplomacy #gazetteplus

photo content
+1

🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ። 🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከ
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ። 🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ። እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ። ✅ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል። 📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ:: 👇🏾👇🏾👇🏾 https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi

ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ጄተን ጋር ውጤታማ የሥልክ ውይይት አድርገናል። በውይይታችን የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ የመከርን ሲሆን፣ በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚያስች
ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ጄተን ጋር ውጤታማ የሥልክ ውይይት አድርገናል። በውይይታችን የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ የመከርን ሲሆን፣ በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ መንገዶች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠናል። - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ከ80 ሺህ በላይ ወጣቶች በ“ሪሞት ጆብስ” ወይም ፍሪላንሲንግ ሥራ ተሰማርተዋል +++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | በኢትዮጵያ ከ80 ሺህ በላይ ወጣቶች በ“ሪሞት ጆብስ” ወይም ፍሪላንሲንግ ሥራ
ከ80 ሺህ በላይ ወጣቶች በ“ሪሞት ጆብስ” ወይም ፍሪላንሲንግ ሥራ ተሰማርተዋል +++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | በኢትዮጵያ ከ80 ሺህ በላይ ወጣቶች በ“ሪሞት ጆብስ” ወይም ፍሪላንሲንግ ሥራ ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ አንድ ባለሙያ ባለበት ቦታ ሆኖ ስማርት ስልክ ወይም ላፕቶፕ በመጠቀም በተለያዩ የዓለም ሀገራት ተቀጥሮ መሥራት የሚያስችለው ሥርዓት ነው። በዘርፉ ከ80 ሽህ በላይ ወጣቶች ቴክኖሎጅን በመጠቀም እዚሁ ሁነው ሌላ ዓለም ላይ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡ ገቢያቸውም እያደገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በዘርፉ በሥራ ፈጠራና ክህሎት ልማት የሰው ኃይል ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የዲጂታል ግንዛቤን ማሳደግና የክህሎት ክፍተቶችን መሙላት ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል። የሪሞት ጆብስ (ፍሪላንስ) ስራ የዲጂታል ክህሎትና እውቀት ያለው ሰው የሚፈልግ በመሆኑ ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ኃይል ለመፍጠር ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ የሥራ ፈጠራ ሐሳቦች እንዲስፋፉ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ በእየሩስ ተስፋዬ #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #ዲጂታል_ኢትዮጵያ #ሪሞት_ጆብስ #ፍሪላንሲንግ #የሥራ_ፈጠራ #ቴክኖሎጂ *#ኢትዮጵያ

"አርበኝነት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት፤ ሀገርንና ሕዝብን ብቻ ማዕከል ያደረገ፤ ለግል ወይም ለቡድን በተለየ የሚገኝ ነገር የለውም። ለሀገር ከሚገኘው ነጻነት፣ ሉዓ
"አርበኝነት ለሀገር ያለ ዋጋ የሚከፈል ከራስ ወዳድነት የነጻ መሥዋዕትነት፤ ሀገርንና ሕዝብን ብቻ ማዕከል ያደረገ፤ ለግል ወይም ለቡድን በተለየ የሚገኝ ነገር የለውም። ለሀገር ከሚገኘው ነጻነት፣ ሉዓላዊነትና ክብር ከሚደርስ የዜጋ ድርሻ በቀር" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) #VictoryOverFascism #ሚያዝያ27 #የአርበኞችቀን #VictoryDay #Ethiopia #PatriotsDayEthiopia

ጥበብ ሀገር ትሠራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታከብራለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ-በዛሬው ዕለት ለሃገር ባለውለታ ለሆኑና በጥበብ ሞያቸው ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅዖ የመታሰቢያና የክብር ሃውልት በአዲስ አበባ በተለያዩ አከባቢዎች ቆሞላቸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ሀገር ለጠቢባን የሕያው ሥራዎቻቸው ምስክር ሐውልት ታቆማለች። ጥበብ ሀገር ትሠራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታከብራለች ብለዋል። ዛሬ በአርበኞች ቀን በተለያዩ መስኮች የጀግንነት ሚና የተወጡ አርበኞቻችንን በማስታወስ እየዘከርናቸው ነው ያሉት ከንቲባዋ የሀገር ባለውለታ ለሆኑና በጥበብ ሞያቸው ለኢትዮጵያ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽዖ የመታሰቢያ ሐውልት ቆሞላቸዋልም ብለዋል። ሀገር በልማት ስራዎች፣ ድንበርን በመከላከል፣ በሰንደቅ ዓላማና በሕግ ብቻ አትገነባም። ሀገር የምትገነባው በሕዝብ የጋራ ትውስታ፣ በጋራ ስሜትና በታላላቅ የጥበብ ውጤቶችም ጭምር ነው። ይህ እውነት ዛሬ በቆሙት የሀገር ባለውለታ ታላላቅ ጠቢባን ሐውልቶች በአዲስ አበባ እውን አድርገናል ሲሉም ገልጸዋል። ከተማ አስተዳደራችን በኮሪደር ልማትና በታላላቅ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ ጥበብን ማዕከል አድርጓል ብለዋል። ዛሬ ሃውልት የቆመላቸው ለሃገራቸው ሰላም፣ ለኢትዮጵያዊነት ግንባታ፣ ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ ለወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ ለፍትሃዊነት፣ ለነፃነትና እኩልነት ላቀነቀኑት አንጋፋዎቹ የሀገር ባለውለታዎች ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድኅን፣ የክብር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ፣ ማሕሙድ አሕመድ፣ ዓሊ ቢራ፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔርና ሐጫሉ ሑንዴሣ ናቸው። ከእነዚህ በተጨማሪም ልናከብራቸው የሚገባን የሀገር ባለውለታዎች የሆኑ የጥበብ ሰዎች መኖራቸው ስለሚታወቅ ይህ ስራ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይደለም። ጥበብ ሀገርን ትስራለች፤ ሀገርም ጠቢብን ታስታውሳለች ብለዋል። እነዚህ የመታሰቢያና የክብር ሃውልቶች በጥበብ ሞያቸው ለሀገር ያበረከቷቸው አስተዋጽኦ የሚዘከርበት ነው ተብሏል። #ሀጫሉሁንዴሳ #የጥበብኮከብ #አዲስአበባ #አፍሪካፓርክ #የኢትዮጵያአሻራ #EthiopianArt #MusicLegend

እንኳን ለ85ኛው የዐርበኞች ድል በዓል አደረሳችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ85ኛው የዐርበኞች ድል
+1
እንኳን ለ85ኛው የዐርበኞች ድል በዓል አደረሳችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ85ኛው የዐርበኞች ድል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 'ኢትዮጵያ ታምርት' ኤክስፖ 2018 በይፋ መርቀው ከፈቱ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የአምራ
+9
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 'ኢትዮጵያ ታምርት' ኤክስፖ 2018 በይፋ መርቀው ከፈቱ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የአምራች ዘርፍ ለማስፋፋት የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክረውን አራተኛውን 'ኢትዮጵያ ታምርት' ኤክስፖ 2018 ዛሬ በይፋ መርቀው ከፍተዋል። ‎ ‎ኤክስፖው እስካሁን ያሳያቸውና የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች ✍️ የአምራች ዘርፉ ግብዓት አቅርቦት በዓመት ከ9 ሚሊዮን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል፤ ‎✍️ ለአዳዲስ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች ከ3.4 ጊጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ቀርቧል፤ ‎✍️ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው የፋይናንስ አቅርቦት ከ8.1 ቢሊዮን ወደ 50 ቢሊዮን ብርአድጓል፣ ✍️ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ከ262 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍ ብሏል፤ ‎✍️ ለዘርፉ ከ2.28 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ተመድቧል፤ ‎✍️ የፋብሪካዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ አድጓል፤ ‎✍️ የማምረት አቅምና ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ ዕድገት ይጠበቃል፤ ‎✍️ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት እስከ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን የተቻለ ሲሆን የወጪ ንግድም አድጓል፣ ‎✍️ ከ2,800 በላይ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ የተቻለ ሲሆን፣ ለ1.4 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል። ‎ ‎ኤክስፖው ኢንዱስትሪዎችን የሚያስተሳስር፣ ኢንቨስትመንትን የሚስብ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ አምራቾችንና ጎብኚዎችን የሚያገናኝ ቁልፍ ሀገራዊ መድረክ ሆኗል። ‎የኤክስፖው ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያለውን ፋይዳ በማጉላት የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ሽግግር እያፋጠነ መሆኑን ያሳያል። #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers

የአራት ዓመታት ተከታታይ ጥረትና የሚጨበጥ ውጤት- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ‎በዘንድሮው “ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ ላይ የሀገራዊ ርዕያችንን ተጨባጭ ስኬት መመልከት ትልቅ ክብር ነው።
+7
የአራት ዓመታት ተከታታይ ጥረትና የሚጨበጥ ውጤት- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ‎በዘንድሮው “ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ ላይ የሀገራዊ ርዕያችንን ተጨባጭ ስኬት መመልከት ትልቅ ክብር ነው። ውጤት ተኮር አመራራችን ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ የኢንዱስትሪ መስፋፋት ተንጸባርቋል። ይኸውም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ በማድረግ፣ ባለፉት አራት አመታት ከ2,800 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ የተቻለ ሲሆን፤ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በሀገር ውስጥ ተኪ ምርት ከ4.85 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ በማዳን ተረጋግጧል። ኤክስፖው ከመላው የሀገሪቱ የተወጣጡ ንቁ አምራቾችን እና ስታርትአፖችን በጨመረ ዐቅም በአንድነት አሰባስቧል። ‎ ‎በጋራ በመሆን ይህንን ጠንካራ መነቃቃት በማስቀጠል፣ ለሚመጣው ትውልድ ጸኑ፣ በኢንዱስትሪ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች ኢትዮጵያን እንገነባለን። ‎ ‎ታላቅ የነበርን ይበልጥም ታላቅ እንሆናለን! #EthiopiaDelivers #MadeInEthiopia