fa
Feedback
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

رفتن به کانال در Telegram

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

کانال Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 24 767 مشترک است و جایگاه 9 682 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 1 405 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 24 767 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 01 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -20 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -14 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید شده (به صورت رسمی توسط تلگرام)
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 10.62% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 4.78% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 632 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 185 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 02 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

24 767
مشترکین
-1424 ساعت
-247 روز
-2030 روز
آرشیو پست ها
“ትግራይ ወጣቶች በየቀኑ የሚታፈሱባት ፍትሕ አልባ ክልል ሆናለች” -ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ │ ትግራይ ወጣቶች የሚሰደዱባት፣ በየቀኑ የሚታፈሱባትና በግዳጅ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የሚገቡባት ፍትሕ አልባ ክልል ሆናለች ሲሉ የስምረት ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ አባል ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ገለጹ፡፡ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ለጋዜጣ ፕላስ እንደተናገሩት፤ የሕወሓት ቡድን በቅርቡ የትግራይን ሕዝብ መብት የሚጥስ አፋኝና ሕገ-ወጥ ሕግ አውጥቷል፡፡ በዚህም ምክንያት ወጣቶች የሚሰደዱበት፣ በየቀኑ የሚታፈሱበትና ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የሚገቡበት አሰጋጭና ፍትሕ አልባ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡ በሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ምክንያት የትግራይ ሕዝብ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛል ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፤ ወጣቶች በተለያየ መንገድ ወደ አዲስ አበባ፣ ወደ ሌሎች ክልሎችና ወደ ጎረቤት ሀገራት በስደት በመውጣታቸው የክልሉ ከተሞች ወጣት አልባ እየሆኑ መጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ ቡድኑ ትግራይንና የትግራይን ሕዝብ እንደ መያዣ (ጋሻ) አድርጎ እየተጠቀመ መሆኑን በመጠቆም፤ መሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች በመጣሳቸው ምክንያት ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ እየተሰቃየ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በትግራይ ክልል አመርቂና አስቻይ ሁኔታ ባለመኖሩ ምክንያት መሠረታዊ የሸቀጦች፣ የነዳጅና የሌሎች አቅርቦቶች እጥረት መከሰቱን የገለጹት ፕሮፌሰሩ፤ ይሁን እንጂ በፌዴራል መንግሥት የሚሰጡ መሠረታዊ የስልክ፣ የትራንስፖርትና ሌሎች አገልግሎቶች ቀጣይነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ሕገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ፣ ሕገ-ወጥ የሰውና የመሣሪያ ዝውውር በየከተማው እንደሚፈጸም አብራርተው፤ በአሁኑ ወቅት ክልሉ በከፍተኛ አጠቃላይ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ የሕወሓት ቡድን የጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ በኃይል ሥልጣን መቆጣጠሩንና ክልሉን ጨምድዶ በመያዝ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ምርጫ ሲካሄድ በትግራይ እንዳይካሄድ ማድረጉንም አብራርተዋል። በማርቆስ በላይ #ጋዜጣ_ፕላስ #ትግራይ #ስምረትፓርቲ #ሕወሓት #ሰብዓዊመብት #ኢትዮጵያ #GazettePlus #Tigray #Ethiopia

እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper
+1
እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper

ሕወሓት አንደ አልሸባብ... ነገ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በጋዜጣ ፕላስ የዩቲዩብ ቻናላችን ይጠብቁ

የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ቡድን ላይ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን መወሰን ይጠበቅበታል - ጋዜጠኛ ዳሞራ ያህያ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ቡድን ላይ ጠንካራ ውሳ
የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ቡድን ላይ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን መወሰን ይጠበቅበታል - ጋዜጠኛ ዳሞራ ያህያ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ቡድን ላይ ጠንካራ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ክልሉን ወደ ነበረበት ሰላማዊ ሁኔታ ለመመለስ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል ሲል ጋዜጠኛ ዳሞራ ያህያ ተናገረ። የሕወሓት አመራሮችና የትግራይን የወርቅ ማዕድን በኮንትሮባንድ መንገድ በመዝረፍ ላይ ናቸውም ብለዋል።የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ቡድን ላይ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን መወሰን ይጠበቅበታል። ጋዜጠኛ ዳሞራ ያህያ ለጋዜጣ ፕላስ በሰጡት አስተያየት፤ የትግራይ ሕዝብ በሕወሓት ቡድን ላይ ጠንካራ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ክልሉን ወደ ነበረበት ሰላማዊ ሁኔታ ለመመለስ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል ብለዋል። የሕወሓት ቡድን የዓለም አቀፍ አሸባሪነትን መመዘኛዎች እያሟላ እንደሚገኝ ያነሱት ጋዜጠኛው፤ ቡድኑ ወጣቶችን ለሌላ ሀገር አሳልፎ በመሸጥ፣ ማዕድንን በመዝረፍና በኮንትሮባንድ ወደ ውጭ በመላክ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በተለይም ቡድኑ በትግራይ አካባቢ ያለውን የወርቅ ማዕድን በስፋት በመዝረፍና በኮንትሮባንድ መንገድ ወደ ሌላ ሀገር በመሸጥ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ይህንኑ የሀብት ዘረፋ እያካሄዱ የሚገኙት የፖለቲካ ኃይሎችና በተለይም የሕወሓት ቡድን ከፍተኛ የበላይ አመራሮች መሆናቸውንም አስረድተዋል። በክልሉ ባለው የሰላም እጦት ምክንያት ወጣቶች ወደ አዲስ አበባና ወደ ሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች በመሸሽ ላይ መሆናቸውን የጠቀሱት ጋዜጠኛ ዳሞራ፤ በአሁኑ ሰዓት የትግራይ ወጣቶች እስከ ሩዋንዳና ኡጋንዳ ድረስ ለመሰደድ መገደዳቸውን ገልጸዋል። መላው ኢትዮጵያውያን ክልሉ ከንቱ በሆኑ የራሱ ልጆች ሲጠፋ በዝምታ ማየት እንደሌለባቸውም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ስላሴ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ጉዳዮች ✍️ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በታቀደውና በሚጠበቀው መሰረት ስራዎቹን በጥሩ ሁኔታ በማከናወን
+3
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ስላሴ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ጉዳዮች ✍️ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በታቀደውና በሚጠበቀው መሰረት ስራዎቹን በጥሩ ሁኔታ በማከናወን ላይ ይገኛል ✍️ በአምስት መቶ ተሳታፊዎች የተቋቋሙት 8 የምክክር ቡድኖች ውይይት ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ተሳታፊዎች በምክረ-ሀሳቦቻቸው ላይ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ፊርማቸውን በማስፈር ስራቸውን በማጠናቀቅ ላይ ናቸው ✍️ በሂደቱ ልዩነቶችና አለመግባባቶች ቢኖሩም ተሳታፊዎች በመወያየት ወደ አማካኝና የጋራ ሀሳብ መድረስ ችለዋል ✍️ ተሳታፊዎች በመደማመጥና በመወያየት ወደ አማካይና የጋራ ሀሳብ መድረስ የምክክሩን አስፈላጊነት አረጋግጧል ✍️ ከየስምንቱ ቡድኖች በተወጣጡ አባላት የተዋቀረ አዲስ ቡድን ተቋቁሟል፤ ✍️ የቡድኑ ዋና ተግባር የምክረ-ሀሳቦቹን ወጥነት መጠበቅ፣ ድግግሞሾችን ማስቀረትና ሀሳቦች እንዳይቃረኑ ያደርጋል፣ ✍️ በሂደቱ የሚቀርቡ ቅሬታዎችና አቤቱታ በተዘረጋው የቅሬታ መፍቻ ስርዓት መሰረት የመመርመርና ውሳኔ የመስጠት ስራ እየተከናወነ ነው ✍️ አጠቃላይ ስራው ሶስት አራተኛ ያህሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የምክክሩ ውጤት በቅርቡ ለኢትዮጵያ ህዝብ ይፋ ይደረጋል ✍️ ለረጅም ጊዜ ሲደከምበት የቆየው የሀገራዊ ምክክር ሂደት ውጤታማና ታሪካዊ ምዕራፍ ነው #Ethiopia #NationalDialogue #PeaceBuilding #NationalConsensus #EthiopianPolitics

የአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ... #EthiopianPolitics #NuclearEnergyEthiopia #SelfReliance #HornOfAfrica

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቀረበውን የኢትዮጵያ ወጣቶች የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭን እንዲቀላቀሉ የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተደረገውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት በኢኒሼቲቩ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መርሐግብር ተካሂዷል። ‎ይህ ዝግጅት የዘርፉን መሪዎችና ፖሊሲ አውጭዎች፣ የምስክር ወረቀት ያላቸውን የኢኒሼቲቩን ተመራቂዎች እና ወጣት ባለሙያዎችን በአንድነት ያገናኘ ነው። ተሳታፊዎች ተሞክሯቸውንና እይታቸውን በመድረኩ እንዲያካፍሉ መደላድልን በመፍጠርም፣ መርሃ ግብሩ በተግባራዊ ዲጂታል ክህሎት ልማት አማካኝነት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 አጀንዳ ዕድገት የራሱን አስተዋፅኦ አበርክቷል። ‎ ‎መርሃ ግብሩ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ባተኮረ የኤግዚቢሽን ጉብኝት የተጀመረ ሲሆን በመቀጠልም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ሥዩም የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸው የወጣቶች የቴክኒክና የዲጂታል ክህሎት ብቃት ወሳኝ ሀገራዊ ሀብት መሆኑን ገልጸው በዚህ ክረምት የኮደሮችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበውን ጥሪ ተግባራዊነት አረጋግጠዋል። ‎ ‎በመቀጠል በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ልምዳቸውንና እይታቸውን ያካፈሉ አራት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። ፓናሊስቶቹም፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ የጊሮ (gheero) ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቤተልሔም ደሴ፣ እንዲሁም የኢኒሼቲቩ ምሩቃን የሆኑት አዝመራው ታደሰ እና የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ማኅሌት ሥዩም ነበሩ። ተሳታፊዎችና ወጣቶች ክህሎታቸውን ያለማቋረጥ እንዲያሳድጉ፣ በተግባር ላይ ያተኮሩ መፍትሔዎችን እንዲያበለጽጉና በኢትዮጵያ የዲጂታል ሥነ-ምህዳር ዕድገትና ፈጠራ ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ የውይይቱ ተሳታፊዎች አበረታተዋል። ወጣት ተሳታፊዎች የዲጂታል ክህሎትን የተመለከቱ ጥያቄዎችን ለፓናሊስቶች አቅርበው ምላሽ ያገኙበት ሲሆን አጠቃላይ መርሃ ግብሩ ግልጽ ውይይትና የልምድ ልውውጥ የተስተናገደበት ነው። ይህ የልምድ ልውውጥ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ የዲጂታል ክህሎትን ለማሳደግና ሀገራዊ ለውጥን ለማፋጠን ያለውን ከፍተኛ ሚና በድጋሚ አረጋግጧል። #PMOEthiopia #DigitalEthiopia2030 #5MillionEthiopianCoders

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ✅ የአሮሞ ህዝብ የኢኮኖሚ ፣የማንነትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን በግልጽ አስቀምጦ በህግ ማዕቀ
+2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ✅ የአሮሞ ህዝብ የኢኮኖሚ ፣የማንነትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን በግልጽ አስቀምጦ በህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሊተዳደሩ የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር በዚህች ሀገር ውስጥ መረጋገጥ የሚችልበትን መንገድ ለመቀየስ መስዋዕትነትን ከፍሏል፣ '✅ የኦሮሞ ህዝብ ትግል ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የቆዬ ነው። ይህ ትግል በአንድ ቦታ፣ በአንድ አካባቢ የተጀመረና እዚያው የቆመ አይደለም፣ ✅ የአሮሞ ትግል ድል የራቀው የአመራር ትግል ነው፤ ትልቅ ሃሳብ አሸናፊ ሃሳብ ይዞ የሚነሳ አመራር አለመኖር ነው፣ ✅ የአሮሞ ህዝብ በዘመናት ታሪኩ በማንኛውም ጊዜ ከሥርዓቱ መበላሸት ውጭ በኢትዮጵያ ላይ ተቃውሞ አያውቅም፤ ጥያቄው ሁልጊዜ ከሥርዓቱ እንጅ ከሀገሪቱ አይደለም፣

ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ተቋም የሆነው 'ፈርስት ፖስት' ስለኢትዮጵያ ባሰራጨው ዘገባ ያነሳቸው ዐቢይት ሃሳቦች +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ| ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት የመጪው ዘመን የአፍሪካ ኃያል ሀገር ወደመሆን እየተሸጋገረች ነው ሲል ታዋቂው የህንድ ሚዲያ ፈርስት ፖስት ዘግቧል። ፈርስት ፖስት ሚዲያ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሠራው ወደ ዘጠኝ ደቂቃ በሚጠጋ ትንታኔው ያነሳቸው ዐቢይት ሃሳቦች፤ ✍️ ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር እያደረገች ነው፣ ✍️ በኢነርጂ፣ በአቪዬሽን፣ በማዕድንና በዲጂታል ኢኮኖሚ መስኮች በተግባር እየሰራች ነው፣ ✍️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በግንባታ ላይ ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ፣ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ያሰተናግዳል፣ ✍️ አዲሱ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ አህጉር ለሚካሄደው የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ከፍተኛ መነቃቃትን ለመፍጠር ታስቦ የተነደፈ ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው፣ ✍️ ህዳሴ ግድብ ከየትኛውም የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ብድር ሳይወሰድበት በኢትዮጵያውያን መገንባቱ፣ አፍሪካውያን የራሳቸውን የተፈጥሮ ሃብት መጠቀም እንደሚችሉ ያረጋገጠ ትልቅ ማሳያ ነው፣ ✍️ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለጎረቤት ሀገራት በማቅረብ የቀጣናው የትስስር ማዕከል እየሆነች መምጣቷን አድንቋል ✍️ የወጪ ንግዱን በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገ ያለው የማዕድን ዘርፍና በሶማሌ ክልል እየተገነባ ያለው ግዙፉ የማዳበሪያ ፋብሪካ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን እንድትችል በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና አለው፣ ✍️ የዲጂታል ትስስር በማስፋፋት የ4ጂ እና 5ጂ አገልግሎቶች በበርካታ ከተሞች ተደራሽ ሆኗል ✍️ ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት፣ ከምዕራባውያን አጋሮችና ከአፍሪካ ኢንቨስትመንትን እየሳበች ትገኛለች፣ ✍️ ኢትዮጵያ ጎራ ሳትለይ ከሁሉም የዓለም ሀገራት ጋር ትብብሯን እያጠናከረች ነው፣ ✍️ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በኢንቨስትመንት ማሻሻያዎች ረገድ አስደማሚ ለውጦችን እያሳየች ነው ✍️ የባንክ ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍትና የካፒታል ገበያ መጀመር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በእጅጉ እንደሚያሳድገው ✍️ ኢትዮጵያ ካላት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ አኳያ እድልና ፈተናዎች ከፊቷ መሆናቸውን በማንሳት፥ አዲሱን የዓለም አቀፍ የትብብር ጥምረት ብሪክስ አባል መሆኗ ጠቅሷል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሪነት በቀጣናውና የአፍሪካ ኃያል ሀገር መሆን የሚያስችላትንና የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚበይንና የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እየሠራች መሆኗን በዘገባው አመላክቷል። #Firstpost #Ethiopia #EconomicGrowth #Africa #Ethiopia #EconomicReform #DigitalTransformation #CapitalMarket

“ጊዜ አይለፍብን፣ ዘመን አይለፍብን ዕድል ስናገኝ እንጠቀምበት” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | ጊዜ አይለፍብን ዘመን አይለፍብን እድል ስናገኝ እንጠቀምበት፤ ልማት እንስራበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በባህርዳር ከተማ የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናልን የመረቁ ሲሆን በምረቃው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ጊዜ አይለፍብን፣ ዘመን አይለፍብን ዕድል ስናገኝ እንጠቀምቡት ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። የባህርዳርን ዕድገት ለማስቀጠል ሁለት ቁልፍ ጉዳዮች ያስፈልጋሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በመጀመሪያ መሠረተ ልማት በተገነባ ቁጥር በርካታ ሰዎች እየመጡ የከተማዋ ገቢ እንዲያድግና ሌላ ልማት እንዲሰራ የከተማዋን የገቢ አቅም ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል። ባህርዳር በገቢ አቅም ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ከተሞች 7ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ በመሆኑ ይህንን አቅም ለማሻሻል መሥራት እንደሚገባ ተናግረዋል። ለቱሪስቶች፣ ለባለሀብቶች፣ወጥተው ለሚገቡ ሰዎች ምቹ እንዲትሆን መላው የከተማዋ ነዋሪና የክልሉ መንግሥት በቅንጅት በመሥራት ባህርዳር የሚገባትን የገቢ ልክ ማመንጨት እንድትችል ተጨማሪ ሥራዎች ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ሁለተኛው መሠረታዊ ጉዳይ ሰላም መሆኑን በአፅንኦት ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የተጀመረው ሥራ ልማድ እንዲሆን ተደጋጋሚ ልማት እንዲሰራ ሰላም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ባህር ዳር ከብዙ የአፍሪካ ሀገራት ዋና ከተሞች የሚሻል አቅም ያለት በመሆኑ ይህ አቅሟ በእኛ ትጋት፣ ልፋትና ሥራ ልቆ እንዲታይ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ሰላም ውድ ስጦታ፣ ጊዜ ትልቅ ሀብት፣ ሥራ ትልቅ ፀጋ፣ ትብብር በጋራ መቆምና መልፋት ከምንጊዜውም በላይ የሚያስፈልግበት ዘመን መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል። እንደዛሬው ዘመን የአማራ ክልልም ሆነ ባህርዳር እራሱን በራሱ በተሟላ መንገድ የሚያስተዳድርበት ዘመን አልነበረም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጊዜ እንዳያልፍብን ተባብረን ተግባብተን ሀገራችንን እንለውጥ ሲሉ አስገንዝበዋል። በክብረአብ በላቸው ++++++++++++++ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት #ጋዜጣ-ፕላስ #ኢትዮጵያ #አማራ #ባህርዳር #ኤርፖርት #የአየርትራንስፖርት

76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ በአዲስ አበባ ይካሄዳል ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 201
76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ስብሰባ በአዲስ አበባ ይካሄዳል ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓም ድረስ በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና መረጃ እንዳመለከተው፤ስብሰባው ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የሚዘጋጅ ሲሆን፤ የቀጣናውን የጤና አጀንዳዎች ላይ መምከርና አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከርን ያለመ ነው ተብሏል። የአፍሪካ የኢኮኖሚ፣የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መዲና የሆነቸው አዲስ አበባ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በርካታ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ጉባኤዎችን አስተናግዳለች፤ ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት ጉባኤን ታስተናግዳለች፡፡ ስብስባው የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ፣ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በመጠቀም ለጋራ የጤና ፈተናዎች የተቀናጀ አህጉራዊ ምላሽ ለመስጠት ስትራቴጂያዊ መድረክ እንድትሆን ያደርጋታል። ጉባኤው ኢትዮጵያ በጤናው ዲፕሎማሲ ዘርፍ የምታደርገው አወንታዊ አስተዋዕጾ እንዲሁም በዘርፉ ያላት ልምድ ለማካፈል እድል ያመቻቻል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የአፍሪካ ቀጣና አባል ሀገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ጤና መሪዎች፣ የልማት አጋሮችና የዓለም ጤና ድርጅት ተወካዮችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች እንደሚሳተፋ መረጃው አመልክቷል። #Ethiopia #health #WHO #HealthSecurity #RC76 #AddisAbaba #africaunion

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እንዲሁም ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ጋር በመሆን ባህር ዳር ከተ
+2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እንዲሁም ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ጋር በመሆን ባህር ዳር ከተማ ገብተዋል። Prime Minister Abiy Ahmed and First Lady Zinash Tayachew together with the Deputy Prime Minister Temesgen Tiruneh and Speaker of the House of Federation Agegnehu Teshager arrive in Bahir Dar city. #PMOEthiopia