ar
Feedback
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

الذهاب إلى القناة على Telegram

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

تُعد قناة Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 24 822 مشتركاً، محتلاً المرتبة 9 605 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 340 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 24 822 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -100، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: موثّقة (مؤكدة رسمياً من تيليجرام)
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.34‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.05‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 319 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 253 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 5.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

24 822
المشتركون
+124 ساعات
-387 أيام
-10030 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+2

ቱሪዝም- አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ቱሪዝምን አሰመልክቶ ከNBC ጋር ባደረጉት ቆይታ ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️ 👉 ለቱሪዝም ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት መነሾ ራዕ
ቱሪዝም- አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ቱሪዝምን አሰመልክቶ ከNBC ጋር ባደረጉት ቆይታ ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️ 👉 ለቱሪዝም ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት መነሾ ራዕያችን ነው 👉 ራዕያችን የበለጸገች የተለወጠች የተከበረችና የተወደደች ሀገር ሰርተን ለልጆቻችን ማስረከብ ነው፣ 👉 በዚህ ዓመት ከ1 ነጥብ 4 ሚሊየን ጎብኝ ኢትዮጵያን ጎብኝቷል፤ ከ5 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል 👉 በቀድሞ ጊዜ በነበረው የትርክት ችግር በቱሪዝም ዘርፉ አለን ከማለት ያለፈ ሥራ አልነበረም፣ 👉 ቅርሶቻችን እንደ ዕዳ ከመታየት ወጥተው ታድሰው ተጠግነው ውብ ሆነው ወጥተው ምንዳ ሆነው ሀብት እያስገኙ 👉 ቅርስ የምናስመልስ የምንጠብቅ እንጅ ቅርስ የምናፈርስ አይደለንም 👉 ቱሪዝምን ከአምስቱ ዋና ዋና የትኩረት መስኮች በመመደብ በመደመር ዕሳቤ በትኩረት እየሠራበት ነው፣ 👉 ባለፉት 7 ዓመታት ከዚህ ቀደም የተዘረፉ ከ35 በላይ የኢትዮጵያ ቅርሶች ተመልሰዋል 👉 እንደ ሀገር ቅርስ ከመመለስ በተጨማሪ ቅርስ በማደስ የሚጎሉትን ደግሞ ገንብተን ለአገልግሎት አብቅተናል፣ 👉 ቱሪዝም ከብዘሃ የኢኮኖሚ ሴክተሮች አንዱ ተደርጎ ተወስዶ እየተሰራ ነው 👉 በዓለም ላይ በቱሪዝም ሴክተር የሚንቀሳቀሰው ሀብት መጠን በጣም ከፍተኛ ነው 👉 ለዘመናት ኢትዮጵያ አያሌ ጸጋዎች እንዳሏት እናምናለን እንናገራለን በዚህም እንኮራለን፣ 👉 ቱሪዝም ላይ ኢንቨስት ማድረግ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ያለውን ሃብት ለመቋደስ ያስችላል 👉 ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም መስህቦች አሏት እሱን የሚያውቁ ፣ የሚያዩና የሚያሳውቁ ውስኖች ናቸው #LandOfOrigins #Medemer #ገበታለሀገር #ገበታለትውልድ #TravelEthiopia #EcoTourism

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው የእንጦጦ-ቀበና የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በፎቶ
+9
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው የእንጦጦ-ቀበና የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በፎቶ

እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper
+2
እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper

16 A+ ያስመዝገበው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ የዓመቱ ኮኮብ ዘለቀ መንግስቴ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በዛሬው ዕለት ካሰመረቃቸ
+3
16 A+ ያስመዝገበው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ የዓመቱ ኮኮብ ዘለቀ መንግስቴ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በዛሬው ዕለት ካሰመረቃቸው ከአንድ ሺህ 817 ተማሪዎችን መካከል የሰርቬይ ኢንጂነሪንግ ዲፓርትመንት ተማሪው ዘለቀ መንግስቴ የዓመቱ ኮከብ ተማሪ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን አንድ ሺህ 817 ተማሪዎችን በአደዋ ድል መታሰቢያ አስመርቋል። ተመራቂ ዘለቀ መንግስቴ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ከወሰዳቸው 58 ኮርሶች 16 A+ በማስመዝገብ የዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ ​ዘለቀ ባለትዳና የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፤ ለስኬቱ የቤተሰቦቹ ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሶ፤ በተለይም የባለቤቱ የዕለት ተዕለት ድጋፍ ለውጤቱ መሳካት ትልቅ እገዛ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በየዩኒቨርሲቲ ቆይታው ከአካዳሚክ ትምህርት ባለፈ ብዙ ጥሩ ነገሮችን መማሩን የሚናገረው ዘለቀ፤ በቀጣይም በተማረበት የሞያ ዘርፍ ሀገሩን በታማኝነት ለማገልገል መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ንጉሥ ታደሰ (ዶ/ር) በምረቃው ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ትምህርት የህይወት ዘመን ጉዞ መሆኑን በመገንዘብ ምሩቃን ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም ሀገራቸውን እንዲሁም ህዝባቸውን በታታሪነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል። ዩኒቨርሲቲው በትምህርት፣ በአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች፣ በጥናትና ምርምር በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች የሀገሪቱን የፐብሊክ ሴክተር ተቋማዊ አቅም ግንባታ እያጠናከረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአማን ረሺድ #ጋዜጣ_ፕላስ #ፕብሊክየኒቨርሲቲ #ተማሪምርቃት #ኢትዮጵያ #EthiopiaDelivers #gazetteplus #graduation

አበባየሁ ደሳለኝ ትባላለች፤ የሦስተኛ ዲግሪ ተመራቂ ከልጇ ጋር +++++++++++ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ከሚያስመርቃቸው 6ሺህ 417 ተማሪዎች መካከል 2 ሺህ 646 ሴቶች ናቸው። 37
+3
አበባየሁ ደሳለኝ ትባላለች፤ የሦስተኛ ዲግሪ ተመራቂ ከልጇ ጋር +++++++++++ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ከሚያስመርቃቸው 6ሺህ 417 ተማሪዎች መካከል 2 ሺህ 646 ሴቶች ናቸው። 377 የሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች መሆናቸው በምረቃው ስነስርዓት ላይ ተገልጿል።

ለምክክር የቀረቡ 8ቱ አጀንዳዎች....
ለምክክር የቀረቡ 8ቱ አጀንዳዎች....

photo content
+5

photo content

ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ 8 አጀንዳዎች ይፋ ሆኑ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ 8 አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ
ለዋናው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ 8 አጀንዳዎች ይፋ ሆኑ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው የምክክር ጉባኤ የሚቀርቡ 8 አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ ኮሚሽኑ ግልጽ በሆነ ሥርዓትን በተከተለ መንገድ 8 ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎችን ለይቷል። በኮሚሽኑ የተለዩት 8 አጀንዳዎች እያንዳንዳቸው በስራቸው ዝርዝር ንዑስ ጉዳዮችን አካተዋል ብለዋል። በዚህ መሠረት 1.የሀገር ግንባታ 2.የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ የፖለቲካ ውክልና የምርጫ ሥርአት ጉዳዮች 3.የፌድራል ከተሞች አዲስአበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ 4.የሃይማኖት ጉዳዮች 5.የተቋማት ግንባታ የህግ የበላይነትና የሰብአዊ መብቶች 6.ማህበራዊና ኢኮኖሚ እንዲሁም የአርሶአደር እና አርብቶ አደር ጉዳዮች 7.ሙስና እና መልካም አስተዳደር 8.ሰላም ግንባታ አጀንዳዎቹ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ በሚካሄደው ጉባዔ ላይ የሚመከርባቸው ናቸው፡፡ በማርቆስ በላይ

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም- ከማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እስከ ማዕድን ዘርፍ ዕድገት +++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “ኢትዮጵያ ታከናውና
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም- ከማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እስከ ማዕድን ዘርፍ ዕድገት +++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ ተካሂዷል። በጉባኤው ላይ ባለፉት ስምንት ዓመታት የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችና ያመጧቸው ተፅዕኖዎች ታይተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር እዮብ ተካልኝ በጉባኤው በሰጡት ማብራሪያ ፤ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ የሀገር ውስጥ መረጋጋትንና ተዓማኒነትን መልሶ ማምጣቱን ገልጸዋል። ይህም የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ነፃ በማድረግ፣ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲን በማዘመን፣ ለዘላቂና አካታች ዕድገት ጠንካራ መሠረት ለመጣል የፋይናንስ ዘርፉን በማጠናከር የተገኘ መሆኑን አብራርተዋል። ‎ በተመሳሳይ የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሐና ብርሃኑ፣ የማዕድን ዘርፍ ከነበረበት ደካማ አፈጻጸም በመላቀቅ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አንዱ መሆን የቻለበትን ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አቅርበዋል። ‎ በቁርጠኛ ማሻሻያዎች፣ በገበያ መልሶ ማዋቀርና እሴትን መጨመር በሚያስችሉ ኢንቨስትመንቶች በመታገዝ ዘርፉ ከፍተኛ የወጪ ንግድ ገቢን እያስገኘ፣ የገቢ ምርቶችን ጥገኝነት እየቀነሰ እና ለኢንዱስትሪ ልማት አዳዲስ ዕድሎችን እየፈጠረ እንደሚገኝ ኢንጂነር ሐና አመላክተዋል። ‎ ‎በወርቅ፣ በወሳኝ ማዕድናት፣ በነዳጅና በማዳበሪያ ምርት ላይ እየተስፋፋ በመጣው የኢንቨስትመንት ለውጦች፣ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት አቅም ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ ዕድገት እየቀየረችው ትገኛለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ በገዘፈ ርዕይና አፈጻጸም ድምር ውጤት እንደሚያስገኙ ህያው ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል። #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers

ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበትን ምርጫ አካሂደዋል - ማህሙድ አሊ ዩሱፍ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ የማህበራዊና
ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበትን ምርጫ አካሂደዋል - ማህሙድ አሊ ዩሱፍ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት መሰረት እንዲሆን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳዩበት ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህመድ አሊ ገለፁ። ሊቀመንበሩ ባወጡት መግለጫ ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግሥት ያላቸውን አድናቆት ገለፀው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ ያሳየውን ሙያዊ ብቃት እና ቁርጠኝነትም አድንቀዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን በታማኝነት፣ ሰላማዊ እና ግልጽነት ባለው የምርጫ ሂደቶችን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑንም በመግለጫቸው ገልጸዋል። ሊቀመንበሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ውጤት መሰረት በአብላጫ ድምፅ ላሸነፉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ለብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመጨረሻም የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን በአባል ሀገራት ውስጥ ተአማኒ፣ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ የምርጫ ሂደት ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጠናከር ያለውን ጽኑ አቋም መግለጻቸውን የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመላክታል። #Ethiopia #AfricanUnion #AU #Election2026

ኢትዮጵያ ታከናውናለች #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers

ኢጋድ ለምርጫው ስኬታማነት ቀዳሚውን ሚና ለተወጡ ኢትዮጵያውያን ዕውቅና ሰጠ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ
+3
ኢጋድ ለምርጫው ስኬታማነት ቀዳሚውን ሚና ለተወጡ ኢትዮጵያውያን ዕውቅና ሰጠ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ውጤት መሠረት፣ በአብላጫ ድምፅ ላገኘው ብልጽግና ፓርቲና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል። በመልዕክቱ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሂደቱን በሙያዊ ብቃትና በቁርጠኝነት በመምራቱና የምርጫው በስኬት መጠናቀቅ ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲያዊ አስተዳደርና ለሕገ-መንግስታዊ ሥርዓት ያላትን ቀጣይነት ያለው ቁርጠኝነት የሚያንጸባርቅ መሆኑንም ጠቁሟል። ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁን ለኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን ያስተላለፈው ኢጋድ፣ ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ውይይትን ለማስፋፋት፣ ዘላቂ ልማትን ለማምጣት ለምታደርገው ጥረት ሙሉ ድጋፍ እንዳለው ገልጿል። በምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትብብርን፣ ውህደትን፣ ሰላምን እና ዘላቂ ልማትን ለማስፈን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቅርበት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። በጋዜጣ ፕላስ ሪፖርተር #ጋዜጣፕላስ #ኢጋድ #ምርጫ2018 #IGAD #Ethiopia #EthiopianElection2026 #Democracy #NEBE #GazettePlus

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስጀመሩ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓ
+6
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስጀመሩ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር በይፋ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን። ዜጎች ‎ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያኖሩም ጥሪ አቅርበዋል።

"የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ግንባታ አትችሉም ለሚሉን እንደምንችል የምናሳይበት ፕሮጀክት ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ | እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማሪፊያ ፕሮጀክት አትችሉም ለሚሉን እንደምንችል፣ የአፍሪካን አቅም ለዓለም የምናሳይበት ፕሮጀክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ፕሮጀክቱ ሲታሰብ ጀምሮ በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬ እንደነበርም ጠቅሰዋል። በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ከ8ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ግንባታን በጎበኙበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ የቢሾፍቱ ኤርፖርት ግንባታ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የማሰብ፣ የማቀድና የመስራት አቅም ለአለም የሚያሳይ ግዙፍ ስራ ነው ብለዋል። ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም እንደነበሩትና በተለያዩ ምክንያቶች እንደሚዘገዩት ፕሮጀክቶች ሳይሆን በከፍተኛ ክትትል የሚመራ፤ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ የሚጠናቀቅ እንደሆነም ገልጸዋል። በፕሮጀክቱ ጅማሮ ላይ ብዙዎች አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ስራውን መምራት አይሆንላችሁም፣ ለምን ታስባላችሁ የሚል የተስፋ ማስቆረጥ ምልከታ እንደነበራቸው አስታውሰው፤ እኛ ግን እንችላለን፣ ይገባናል የሚመጥነን ፕሮጀክት ነው ብለን በተግባር እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ የኤርፖርቱ ግንባታ በትልቅነቱ፣ በሚመደብለት ሃብትና በአጠቃላይ በሚያንቀሳቅሰው ማሽነሪ በአፍሪካ ደረጃ ትልቁ ፕሮጀክት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በግንባታው ሂደት የሚገጥሙ በርካታ ፈተናዎችን በመፍታት ፕሮጀክቱን ማሳካት እንደሚቻል በተግባር እየታየ ይገኛል ብለዋል። በልማቱ ምክንያት የተነሱ የአካባቢው አርሶ አደሮች የቤት ግንባታና የቢዝነስ ተቋማት መደራጀታቸውንና በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚጎዳ አርሶ አደር እንደማይኖርና ሙሉ በሙሉ ህይወታቸው እንደሚሻሻል አረጋግጠዋል። በፕሮጀክቱ ከ8 ሺህ በላይ ሠራተኞች እንደሚገኙና እስከ 4 ሺህ የሚጠጉ ማሽነሪዎችና መኪናዎች እንደሚንቀሳቀሱ ጠቅሰው፣ ለማሽኖቹና ለመኪናዎች አገልግሎት በቀን ከ650 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ጥቅም ላይ ይውላል ብለዋል። በብዙ ሀገራት ብሎም በኢትዮጵያ የሥራ ሐሳብና ሀብት ቢኖርም፤ የፕሮጀክት አመራር ችግር ስላለ ፕሮጀክቶች መቼ ተጀምረው መቼ እንደሚጠናቀቁና እንዴት ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው በቂ ግንዛቤ አለመኖሩን ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ በረከት ነው፤ ለልጆቻችንም ትልቅ መሰረት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ በተባበረ ክንድ የኢትዮጵያን ድህነት ለመስበር፣ የበለጸገችና ያደገች ኢትዮጵያን በጋራ ለማየት በጋራ እንዲቆምና እንዲተባባር ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በአማን ረሺድ እና በሀብታሙ በውቀት #ቢሾፍቱ_ኤርፖርት #ሜጋ_ፕሮጀክት #የኢትዮጵያ_አየር_መንገድ #አፍሪካ #BishoftuAirport #AfricanExcellence #Infrastructure #AfricaRising

photo content

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መረሐግብር የችግኝ ተከላ በቢሾፍቱ ሲያስጀምሩ #GreenLegacy #ቢሾፍቱ_ኤርፖርት #AfricaRising #አረንጓዴዐሻራ #water