fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 269
مشترکین
+224 ساعت
+97 روز
+2130 روز
آرشیو پست ها
96 ሰው በናዳው የጠፋ ሲሆን የ36 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል *** ለትላንት መጋቢት 1 አጥቢያ ለሊት ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ የተነሳ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ማዞ ዶይሳ እና ላካ ቀበሊያት ላይ
96 ሰው በናዳው የጠፋ ሲሆን የ36 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል *** ለትላንት መጋቢት 1 አጥቢያ ለሊት ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ የተነሳ በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ ማዞ ዶይሳ እና ላካ ቀበሊያት ላይ በተፈጠረው የመሬት መንሸራተት ምክንያት 96 ሰዎች በናዳው ምክንያት የጠፉ ሲሆን የ36 ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል። ቀሪ የ60 ሰዎችን አስክሬን የማፈላለግ ሥራው እየተሰራ ይገኛል። እግዚአብሔር ይታረቀን! አቤቱ ጌታ ሆይ ማረን ይቅር በለን በእውነት!

=> ቅዱስ ቄርሎስ የክርስቶስን ሥጋና ደም መቀበል ለነፍስና ለሥጋ ያለውን ፋይዳ ሲያስረዳ እንዲህ ይላል፦ "የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ ሕያው የሚያደርግ ነው፤ ምክንያቱም የሕያው ቃል ሥጋ ነውና። መለኮት በባሕርዩ ሕይወት እንደሆነ ሁሉ፣ እርሱ የተዋሐደው ሥጋም ሕይወትን የሚሰጥ ሆነ። ስለዚህ ሥጋውን በበላችሁና ደሙን በጠጣችሁ ጊዜ በእናንተና በክርስቶስ መካከል ያለውን አንድነት አስቡ። ይህ ሰማያዊ ምግብ የኃጢአት መርዝን የሚያጠፋ፣ ሞትን የሚገድልና የማይሞት ሕይወትን የሚሰጥ እውነተኛ መድኃኒት ነው።" => ቅዱስ ቄርሎስ በጉባኤ ኤፌሶን ላይ ድንግል ማርያምን "ወላዲተ አምላክ" (የአምላክ እናት) ብሎ መጥራት የሃይማኖት መሠረት መሆኑን ሲያበስር እንዲህ ብሏል፦ "በአንቺ (በድንግል ማርያም) አማካኝነት መላእክት ደስ ይላቸዋል፤ ሰይጣን ከሰማይ ወደቀ፤ ፍጥረት ሁሉ ወደ እውነት መጣ። በአንቺ አማካኝነት አሕዛብ ወደ ንስሐ ተመለሱ። ድንግል ሆይ! አንቺ የአምላክ እናት ነሽ፤ በአንቺ ማኅፀን ያደረውና የተወለደው እርሱ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው ነውና። በአንቺ አማካኝነት የጨለመው ዓለም በብርሃን ተሞላ።" => ቅዱስ ቄርሎስ መለኮትና ትስብእት (ሰው መሆን) እንዴት አንድ እንደሆኑ ሲያስተምር እንዲህ ይላል፦ "ክርስቶስን ለሁለት አትክፈሉት፤ እርሱ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው። መለኮት ከሥጋ ጋር ሲዋሐድ እንደ እሳትና ብረት ነው። ብረቱ በእሳቱ ውስጥ ሲገባ ብረትነቱ ሳይጠፋ የእሳቱን ባሕርይ (ሙቀትና ብርሃን) እንደሚካፈል ሁሉ፣ የክርስቶስ ሥጋም መለኮትን በመዋሐዱ ሕያውና ቅዱስ ሆነ። ስለዚህ የምንሰግድለት ክርስቶስ አንድ ነው፤ እርሱም አምላክ ወሰብእ (አምላክም ሰውም የሆነ) መድኃኒት ነው።" => ቅዱስ ቄርሎስ ክርስቲያኖች በሃይማኖታቸው ሊኖራቸው ስለሚገባ ጽናት ሲመክር፦ "ልባችሁን በእግዚአብሔር ቃል ቀድሱት። ሃይማኖት ያለ ግብረ ገብነት (ያለ ምግባር) የደረቀ ዛፍ ነው፤ ምግባርም ያለ ሃይማኖት መሠረት የሌለው ቤት ነው። ስለዚህ በሁለቱም በርትታችሁ ቁሙ። ዓለም በብዙ ማዕበል ብታውካችሁም፣ እናንተ ግን በክርስቶስ ድንጋይነት ላይ የታነጻችሁ መሆናችሁን አትዘንጉ። ነቅታችሁ ጸልዩ፤ የጠላት ውጊያ የሚሸነፈው በትሕትናና በእግዚአብሔር ቃል ነውና።"

=> ቅዱስ ኒፎን ሰይጣን ሰውን የሚጥልበት ትልቁ መሣሪያ "ተስፋ ማስቆረጥ" እንደሆነ ያስተምራል። እንዲህም ይላል፦ "ልጄ ሆይ! ብትወድቅ እንኳን ተስፋ አትቁረጥ፤ እንዲያውም ሰባት ጊዜ ብትወድቅ ሰባት ጊዜ ተነሣ። እስከ መጨረሻው ትንፋሽህ ድረስ የእግዚአብሔር ምሕረት ከኃጢአትህ እንደሚበልጥ እመን። ሰይጣን የሚደሰተው በኃጢአትህ ሳይሆን በኃጢአትህ ምክንያት ተስፋ ስትቆርጥ ነው። ስለዚህ ውደቅ እንጂ ተኝተህ አትቅረ!" => ቅዱስ ኒፎን የሰውን ኃጢአት ሳይሆን የራሱን ብቻ በማየት የታወቀ አባት ነው። የእርሱ ንግግር እንዲህ ይላል፦ "በወንድምህ ላይ አትፍረድ፤ ይልቁንም በራስህ ላይ ፍረድ። ሌላው ቢበድል እግዚአብሔር ዳኛ አለው፤ አንተ ግን የራስህን በደል ብቻ ተመልከት። የራሱን ኃጢአት የሚያይ ሰው የሌላውን ጉድፍ ለማየት ጊዜ የለውም። በሰዎች ላይ የምትፈርድ ከሆነ እግዚአብሔር ካንተ ላይ ጸጋውን ያርቃል፤ ራስህን የምትወቅስ ከሆነ ግን ሰማያዊ ብርሃን ይጎበኝሃል።" => ቅዱስ ኒፎን ትሕትና ሰይጣንን የሚያቃጥል ሰይፍ እንደሆነ ሲመክር እንዲህ ይላል፦ "ከፍታን ከፈለግህ ወደ ታች ዝቅ በል፤ እውነተኛ ክብር በትሕትና ውስጥ ትገኛለችና። ራስህን ከፍጥረት ሁሉ በታች አድርገህ ብትቆጥር፣ የእግዚአብሔር ጸጋ በላያህ ላይ ያርፋል። ትሑት ልብ የሰይጣንን መመኪያ ይሰብራል። ሰይጣን ሁሉንም ነገር ሊመስል ይችላል፤ ትሕትናን ግን ፈጽሞ ሊመስላት አይችልም።" => ቅዱስ ኒፎን ዘወትር ነፍስን በጸሎት ማነቃቃት እንደሚገባ ሲመክር፦ "ነፍስህ እንዳትዝል ዘወትር በጸሎት ትጋ። ሰይጣን የሚዋጋህ አንተ ስትተኛ (በመንፈሳዊ ሕይወት ስትዘናጋ) ነው፤ ስለዚህ ልብህ ዘወትር ከእግዚአብሔር ጋር ይሁን። ጸሎት ለነፍስ እንደ ትንፋሽ ነው፤ ነፍስ ካልጸለየች ትሞታለች። በጸሎት እሳትነት የጠላትን ቀስት አምክን።"

ነገሮች ለዘገየባችሁ ይኼንን መዝሙረ ዳዊት ሰባት ጊዜ ጸልዩ ተዓምር ታያላችሁ!! ቅዱስ ዳዊት በደረቱ ተኝቶ የጸለየው አስገራሚው ጸሎት!! #መዝሙረ_ዳዊት_69 https://youtu.be/M0GTvinvlLE

መንፈሳዊ ሕልምና ፍቺዎቻቸው ብዙ ነገር የምትማሩበት የላይቭ ቆይታችን ነው ሁላችሁም ካላያችሁ ተመልከቱ! ከክፍል 1 ጀምሮ እስከ ክፍል 4 ድረስ ከታች ባለው ልንክ ገብታችሁ ማዳመጥ ብዙ ነገሮችን እንድታውቁ ያደርጋል። በርቱ ክፍል 1: https://www.youtube.com/watch?v=-E4DQuQLet4&t=3184s ክፍል 2: https://www.youtube.com/watch?v=0R_00dEaJjA&t=2294s ክፍል 3: https://www.youtube.com/watch?v=BI4af7XgyBA&t=4984s ክፍል 4: https://www.youtube.com/watch?v=LGm4MK0rC5A&t=336s&pp=0gcJCa4KAYcqIYzv

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሠላሳ በዚህች ዕለት ለቅዱስ ማርቆስ መንበር አንድ መቶ ዐሥራ ስድስተኛ የሚሆን የጳጳሳት አለቃ ጻድቅና የእግዚአብሔር ሰው ብፁዕ ወቅዱ
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሠላሳ በዚህች ዕለት ለቅዱስ ማርቆስ መንበር አንድ መቶ ዐሥራ ስድስተኛ የሚሆን የጳጳሳት አለቃ ጻድቅና የእግዚአብሔር ሰው ብፁዕ ወቅዱስ አባ ቄርሎስ ስድስተኛ ዐረፈ። ይህ ቅዱስ አባት መንገዱን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረግ ድንቅ ድንቅ ተዓምራትን ያደረገ ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ አባት ጸሎት ይማረን አሜን።

4ተኛ Live መንፈሳዊ ሕልምና ፍችዎቻቸው! ሕልማችሁን ጻፉልኝ በዚሁ እንወያያለን! #ሕልም Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live!

መምህር ዘለዓለም ወንድሙ፣ ለአገልግሎት በሄዱበት በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። መምህር ዘላለም ወደ አሜሪካ ያቀኑት ለተለመደው መንፈሳዊ አገል
መምህር ዘለዓለም ወንድሙ፣ ለአገልግሎት በሄዱበት በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። መምህር ዘላለም ወደ አሜሪካ ያቀኑት ለተለመደው መንፈሳዊ አገልግሎት የነበረ ሲሆን፣ በድንገት በገጠማቸው የጤና መታወክ ምክንያት ለሦስት ቀናት ያህል በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዕለተ ቅዳሜ ከድካመ ሥጋ ዐርፈዋል። ነፍስህን ያገለገልከው ፈጣሪ ይቀበላት!

ማንያዘዋል እሸቱ ላይ የተላከው አደገኛው መተትና ማወቅ የሚገባቸው ነገሮች https://youtu.be/dyQkT_xqWsw?si=U3NfIRO8DjCsrXSC

ሰይጣን ጸሎታችን እንዳልተመቸው የሚያሳዩ ምልክቶችና ማወቅ ያለባችሁ ነገሮች!! በጸሎት ሰዓት የቡዳ መንፈስን ለመለየት ይኼንን አድርጉ!! #ጸሎት #ሰይጣን https://youtu.be/KAUxHcFlq_s?si=8f4T3EzzNHyCT7Ou

መምህር ተስፋዬ ጠንቋይ ቤት ገብቶ የገጠመውና ያጋለጠው ከባድ መረጃ!! አግብቶ የፈታውና ክህነቱን ያፈረሰው ደብተራ! በከራማ መንፈስ የተመረቁ ልጆች የገጠማቸው https://youtu.be/UxXSc1ZPl4A

🛑በሐሰት ተከሳችሁ መከራችሁን እያያችሁ ከሆነ ይኼንን መዝሙረ ዳዊት ጸልዩ! ፍርድ ቤት ከመሄዳችሁ በፍት ይኼንን ጸልዩ! በሐሰት ሴራ የተከበቡ ሰዎች ይጸልዩት! https://youtu.be/Dv-FCLRSTs8?si=nLhriGqJIECEnUW2

ሰው ስትሆን እንዲህ ታስባለህ። እግዚአብሔር ሀገራችንን ኢትዮጵያን በእውነት ሰላም ያድርግልን። ተድሮስ ካሳሁን ወንድማችን እናመሰግናለን።
ሰው ስትሆን እንዲህ ታስባለህ። እግዚአብሔር ሀገራችንን ኢትዮጵያን በእውነት ሰላም ያድርግልን። ተድሮስ ካሳሁን ወንድማችን እናመሰግናለን።

የኢራን ደጋፊዎች እና የእስራኤል ደጋፊዎች ከኢትዮጵያ ሆነው የቃላት ጦርነት ከፍተዋል። እኔ ምለው፦ ሀገራችሁ ኢትዮጵያ ግን ሰላም ናት?