HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 279
Підписники
Немає даних24 години
+57 днів
+3230 день
Архів дописів
መምህር ምትኩ የመናፍስትን ሴራ ላለማውራት የሄደበት ርቀት እጅግ ያሳዝናል!! የመምህሩ ግራ የገባው መልስ ለተጨነቀች ነፍስ!! መምህር ተስፋዬ ያጋለጠው መረጃ! https://youtu.be/Kup6IjYHQxQ
#ይኼንን_ምስክርነት_አንብቡ!!
=> እሁድ ለት በነበረው አገልግሎት በጣም የምያስገርም እና የሚደንቅ ነገር ነበር የሆነው እኔ ዱባይ ነኝ አንድ ወንድሜ በጣም ተጨንቆ በቴሌግራም እህቱ 13 አመት ሙሉ በኩላሊት በሽታ እንደተሰቃየችና አሁን ግን ዶክተሮች ተስፋ የለሽም እንዳሏት ነገረኝ እኔም በጊዜው ተረበሽኩና ስለሱ ውጊያ ከጀመረ ምን ያህል ጊዜ እንደሆነ ጠየኩት እሱም ገና አዲስ እንደሆነ ነገረኝ እኔም የአምልኮ ስግደቶቹን ላኩለትና እሷ መንቀሳቀስ አትችልም ስላለኝ ክርስትና ስሟን እጅህ ላይ ፅፈህ ስገድ አልኩት ወዲያው ግን እግዚአብሔር ድንቅ ነውና በዚሁ fb ላይ አንድ የመምህር ግርማ ተማሪ የሆነና የጸሎት ማህበር ያላቸውን ሰው ተዋወኩ እሱ ስለ ማህበሩ ሲነግረኝ ቶሎ ብዬ ስለ ኩላሊት ታማሚዋ ልጅ ነበር የነገርኩት እሱም ወንድሟ እንደምንም ብሎ ማህበር ላይ ይዟት ይምጣ ይለኛል እኔም ለወንድሟ እንደምንም ብለህ እዚህ ማህበር ላይ ይዘሃት ህድ ብዬ አድራሻቸውን ሰጠሁት ይዟት ሄደ እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው የ13 አመት በሽታ መተት ሆኖ ተገኘ ከዚያ መንፈሱ ሲያዝላት እሷም ጸሎቱንም ስግደቱንም ጀመረች ይህ የሆነው ቢየንስ ከሁለት ወር በፊት ነው አሁን እሁድ ለት በመምህር ግርማ እጅ ተሸኘላት ለአባታችን እድሜና ጤና ይስጥልኝ ውሻ በማያውቀው ሰው ላይ ነውና የሚጮሀው ስለሚጮሁት ሰዎች አንጨነቅም ይህ በረከት እንዳያልፋችሁ ግን እላለሁ።
#ሸር አድርጉ!
አብዝቶ ሰግዶ መተኛት በአጋንንት ላይ ያለው የበላይነትና ግዴታ ማወቅ ያለባችሁ ነገር!! ፓስተር ቢኒያም ሽታዬ ከመምህር ተስፋዬ የሚፈልገው ምንድነው? ከግለ ወሲብ ለመላቀቅ የሚረዱ 5 ወሳኝ መፍትሔዎች! የማይቆረብበት ትዳር በጭራሽ አያጸድቅም!! https://youtu.be/8ezVygzgDl4
ከስግደት ጋር በተገናኘ ሁሉም ኦሮቶዶክሳዊ ማወቅ የሚገባው 4 ወሳኝ ነጥቦች!! ሱባኤ ለመያዝ ጊዜ የሌላችሁ አሁኑኑ ይኼንን አድርጉ ብዙ ታተርፋላችሁ!! #ጸሎት https://youtu.be/8Voxv8XvaUA
✨ የጌታዬ እናት ማርያም
የበረከት ምንጭ የሰላም
መከራ በዝቶ ተጨንቀናል
ድንግል ነይልን ተማፅነናል
🙏 የኪዳነ ምሕረት ረድኤት በረከት በሁላችን ላይ ይደር። እንኳን አደረሳችሁ ውድ ቤተሰቦቼ!
=> "ይህ የሕይወት እንጀራ ነው፤ የበላውም አይሞትም።" ቍርባን ዝም ብሎ ሥርዓት ሳይሆን የነፍሳችን መድኃኒት ነው። ሥጋችን ሲታመም ወደ ሐኪም እንደምንሮጥ ሁሉ፣ ነፍሳችን በኃጢአት ቁስል እንዳትሞት በቍርባን መድኃኒትነት ልታክሟት ይገባል። መድኃኒቱ በደጃችሁ እያለ በበሽታ (በኃጢአት) አትሙቱ። "ሁለት የሰም ሻማዎች ቀልጠው ሲዋሐዱ አንድ እንደሚሆኑ ሁሉ፣ የክርስቶስን ሥጋና ደም የሚቀበል ሰውም ከክርስቶስ ጋር አንድ ይሆናል።" የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከጌታ ጋር ካልተዋሐድን እንዴት ሕይወት ሊኖረን ይችላል? ቍርባን የፈጣሪን ባሕርይ ገንዘብ የምናደርግበትና በጸጋ የምንከብርበት ብቸኛው መንገድ ነው።
=> አባቶቻችን እንዲህ ብለው ይገሥጹናል፦ "ዛሬ በቁመትህ ሳለህ በንስሐ ታጥበህ ካልቆረብክ፣ ነገ በሬሳ ሳጥን ውስጥ ሆነህ ቢቀድሱብህ ምን ይጠቅምሃል?" ሞት ቀጠሮ የለውምና "አረጅቼ እቆርባለሁ" የሚለው የሰይጣን ማታለያ እንዳያታልላችሁ። አሁኑኑ ወደ ንስሐ አባታችሁ ቅረቡ፤ ለሰማያዊው ማዕድ ራሳችሁን አዘጋጁ። ወንድሜ ሆይ! እኅቴ ሆይ! ጌታችን በወንጌል "ሥጋዬን ካልበላችሁ ደሜንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም" (ዮሐ ፮፥፶፫) ብሎናል። ስለዚህ ሕይወት እንዲኖራችሁ፣ ጠላትን ድል እንድታደርጉና ከፈጣሪ ጋር አንድ እንድትሆኑ በንስሐ ታጥባችሁ ይህንን የከበረ ሥጋና ደም ለመቀበል አሁኑኑ ተነሡ።
"እግዚአብሔርን ቅመሱትና ቸር እንደ ሆነ እዩ።" (መዝ. ፴፫፥፰)
=> የአባታችን የመምህር ግርማ ወንድሙ ቀጣይ አገልግሎት በመጋቢት 20/07/2018 በእለተ እሁደ ስለሆነ ሁላችሁም ላልሰማ በማሰማት የበረከቱ ተካፋይ እንድትሆኑ መረጃውን አጋራለሁ። ብዙዎች ስትጠይቁ ስለነበረ ይኼው ተጠቀሙ ውዶች።
=> አድራሻ፦ ከመገናኛ በጎሮ ለሚ ኢንዱስትሪ ከሰሚት ኮንዶሚኒየም በ3ኛ በር ለሚ እንዱስትሪ ብለው ብመጡ ቤተክርስቲያኑን በቀላሉ ያገኛሉ።
መልካም ምሽት ለሁላችሁ ይሁን!
ሸር አድርጉ ላልሰሙ አሰሙ!
ፍታችሁንና ጸጉራችሁን በቁስል የሚመታ ውስጣችን ያደፈጠ የአጋንንት ሴራና ተንኮል!! በውቤታችንና በመልካችን የሚቀናው የዓይነጥላ መንፈስ ጉዳቶች!! #ጸሎት https://youtu.be/A3tNcZrc7ls
መጋቢት ፲፬ /14/
በዚችም ቀን ደግሞ ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ ሰባት ዓመት ያህል የጋኔን ግንኙነት በአስቸገራት በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን አደረገ።
ሐዋርያ ቶማስንም በአየችው ጊዜ የክርስቶስ ሐዋርያው ሆይ እጅግ ከሚያሠቃየኝ ጠላት አድነኝ ብላ ወደርሱ ጮኸች እርሱም በምን ምክንያት አገኘሽ አላት እርሷም ከመታጠቢያ ከውሽባ ቤት ስወጣ እንደ ሰው ድው ድው እያደረገ በመታወክ መጣ ድምጡም ሰላላና ቀጪን ነው በሴትና በወንድ ሥራ ሁሉ ነይ እርስበርሳችን አንድ እንሁን አለኝ በተኛሁም ጊዜ በሌሊት መጥቶ ከእኔ ጋራ አንድ ሆነ ብሸሽም አይተወኝም መጥቶ ያሠቃየኛል እንጂ።
እኔም ከጸሎትህ የተነሣ አጋንንት እንደሚንቀጠቀጡ አውቃለሁና ጸልይልኝ አድነኝም አለችው። ሐዋርያ ቶማስም ሰምቶ ጸለየ ጋኔኑንም ከእርሷ እንዲወጣ አዘዘው ያንጊዜም በእሳትና በጢስ አምሳል ከሴቲቱ ላይ ወጥቶ ተበተነ።
ከዚህ በኋላ በክርስቶስ መስቀል በላይዋ አማተበ ሥጋውንና ደሙንም አቀበላት ወደ ዘመዶቿም አሰናበታት። ልዩ የሆነች በረከቱም በሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ላይ ትደር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
=> በዚህ ኅብስት ውስጥ የተሰወረ ኃይል አለ፤ በዚህ ጽዋ ውስጥ የሚነድ መንፈስ አለ። ኅብስቱን ብሉ፤ እሳቱንም ጠጡ። እሳቱንና መንፈሱን በውስጣችሁ አሳድሩ። እሳቱ የኃጢአታችሁን እሾህ ያቃጥላል፤ መንፈሱ ደግሞ የጠወለገች ነፍሳችሁን ያለመልማል። ሞት የሰውን ልጅ ሊያጠፋ ሲመጣ፣ በደጃፉ (በአፉና በልቡ) ላይ የክርስቶስን ደም ምልክት ካየ ይርቃል፤ ማጥፋትም አይችልም። (ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ)
=> ከዚህ ቅዱስ ማዕድ (ከቁርባን) ተቀብለን ስንወጣ፣ እንደ አንበሳ እሳት እንደሚተነፍሱ ሆነን መውጣት ይገባናል። ሰይጣን እኛን ሲያየን ሊቋቋመን የማይችል እሳት መስለን ልንታየው ይገባል። ምክንያቱም የክርስቶስን ደም የተቀበለች አንደበት እንደ መንፈሳዊ ሰይፍ ስለት አላት፤ ሰይጣንም የንጉሡን ደም በአፋችን ላይ ሲያይ ይርዳል፤ ይሸሻልም። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
እባካችሁ ውድ ቤተሰቦቼ እንቁረብ የክርስቶስን ሥጋና ደም እንቀበል። እንቀደስ እንባረክ!
ይኼንን ቪዲዮ አይታችሁ አሳባችሁን አካፍሉን! https://youtu.be/I63SaRgf-S4?si=5yKZ6niXnmS9Ja1p
"ለፕሮተስታንት ወንድሞች የተሳሳተ አመለካከት የተሰጠ መልስ!"
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "ኦርቶዶክሳውያን ለድንግል ማርያም ይሰግዳሉ፣ ይህ ደግሞ አምልኮ ነው፤ አምልኮ ደግሞ ለእግዚአብሔር ብቻ ነው የሚገባው።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለድንግል ማርያም የምትሰጠው ክብር "የጸጋ ስግደት" (Veneration/Hyperdulia) እንጂ "የባሕርይ ስግደት" (Worship/Latria) አይደለም። አምልኮ ለሥላሴ ብቻ ነው። እኛ የምንሰግድላት የእግዚአብሔር እናት ስለሆነችና እግዚአብሔር ስላከበራት ነው።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ ራሷ ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ "እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል" ብላለች (ሉቃስ ፩፥፵፰)። ትውልድ ሁሉ እንዲያከብራት እግዚአብሔር ወዶአል። መላእክትም አክብረዋታል (ሉቃስ ፩፥፳፰)።
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "ማቴዎስ ፩፥፳፭ ላይ 'የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም' ይላል፤ 'እስከ' ካለ ከወለደች በኋላ አውቋታል (ግንኙነት አድርገዋል) ማለት ነው።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ "እስከ" የሚለው ቃል ድርጊቱ ከዚያ በኋላ ተፈጽሟል የሚል ትርጉም ሁልጊዜ አይሰጥም።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ ፪ኛ ሳሙኤል ፮፥፳፫፦ "የሳኦል ልጅ ሜልኮል እስክትሞት ድረስ ልጅ አልወለደችም" ይላል። ታዲያ ከሞተች በኋላ ወለደች ማለት ነው? አይደለም። ማቴዎስ ፳፰፥፳፦ "እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ" ይላል። ታዲያ ዓለም ሲያልፍ ጌታ ይተወናል ማለት ነው? አይደለም። ስለዚህ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን "እስክትወልድ አላወቃትም" ማለቱ፣ ጌታ በተአምር መወለዱን ለማረጋገጥ እንጂ ከልደቱ በኋላ ግንኙነት ማድረጋቸውን አይገልጽም።
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስ ወንድሞች ይላል (ማቴ ፲፫፥፶፭)፤ ስለዚህ ድንግል ማርያም ሌሎች ልጆች ነበሯት።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ "ወንድም" የሚለው ቃል ለቅርብ ዘመድ፣ ለወንድም ልጅ ወይም ለክርስቶስ ተከታዮች ይሠራበታል። ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ እናቱን ለሐዋርያው ዮሐንስ አደራ የሰጠው (ዮሐ ፲፱፥፳፮-፳፯) ሌላ ልጅ ስላልነበራት ነው። ሌላ ልጅ ቢኖራት ኖሮ ለባዕድ ሰው አደራ አይሰጥም ነበር።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ አብርሃም ሎጥን "ወንድሜ ነህ" ብሎታል (ዘፍ ፲፫፥፰)፤ ግን ሎጥ የአብርሃም የወንድሙ ልጅ እንጂ የሥጋ ወንድሙ አልነበረም። የጌታ "ወንድሞች" የተባሉት የዮሴፍ ልጆች ወይም የድንግል ማርያም እህት (የማርያም ቀለዮጳ) ልጆች እንደሆኑ ታሪክና መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳሉ።
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "መካከለኛው አንድ ክርስቶስ ብቻ ከሆነ (፩ኛ ጢሞ ፪፥፭) ድንግል ማርያም እንዴት ታማልዳለች?"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ በ"ቤዛዊ መካከለኛ" እና በ"ልመና አማላጅ" መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት ያስፈልጋል። ክርስቶስ ቤዛዊ መካከለኛ (Mediator of Redemption) ነው፤ በደሙ የገዛን እርሱ ብቻ ነው። ቅድስት ድንግል ማርያም ግን በጸሎትና በልመና የምታማልድ ባለሟል ናት።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት (ዮሐንስ ፪) ላይ ጌታ ገና "ጊዜዬ አልደረሰም" እያለ በእናቱ አማላጅነት (ልመና) ውኃውን ወደ ወይን ለውጧል። ይህም የእርሷ ልመና በልጇ ዘንድ ምን ያህል ተሰሚነት እንዳለው ያሳያል። ቅዱስ ጳውሎስም "እርስ በርሳችሁ ጸልዩ" (ያዕ ፭፥፲፮) ካለ፣ ከቅዱሳን ሁሉ የምትበልጠው እናቱ መጸለይዋ እንዴት ስህተት ይሆናል?
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "ማርያም ጌታን ለማምጣት እንደ ኤንቨሎፕ ወይም እንደ መኪና (ትራንስፖርት) አገልግላ አልፋለች፤ ስለዚህ አሁን ልዩ ክብር አይገባትም።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ ይህ አመለካከት የጌታን ሰው መሆን (ምስጢረ ሥጋዌን) መካድ ነው። ጌታ ከሥጋዋ ሥጋን፣ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ነው ሰው የሆነው። እርሷ የባሕርይ እናቱ ናት እንጂ ተራ መያዣ አይደለችም። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ "የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?" በማለት ድንግል ማርያምን አክብራታለች (ሉቃስ ፩፥፵፫)። ድንግል ማርያም "ኤንቨሎፕ" ብትሆን ኖሮ "የጌታዬ እናት" አትባልም ነበር።
ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ድንግል ማርያምን የምታከብረው ስለ ራሷ ብላ ሳይሆን ስለ ልጇ ብላ ነው። እርሷን ማክበር ልጇን ማክበር ነው፤ እርሷን መናቅ ደግሞ ጌታ ከሰው የመወለዱን ምስጢር ማቃለል ነው። "የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች" (ያዕቆብ ፭፥፲፮) ከተባለ፣ ከሰው ልጆች ሁሉ በላይ ቅድስት የሆነችው የእግዚአብሔር እናት ጸሎትማ እንዴት ይበልጥ ኃይል አይኖረውም!
ወንድሞቻችን "ክርስቶስ እየሰማ ለምን በቅዱሳን በኩል ትሄዳላችሁ?" ይላሉ።
- ምክንያት ፩፦ እግዚአብሔር ራሱ እንዲህ ስለወደደ። ለምሳሌ አቢሜሌክን ይቅር ማለት ሲችል "ወደ አብርሃም ሂድ እርሱ ይጸልይልሃል" አለው (ዘፍ ፳፥፯)። የኢዮብን ባልንጀሮች "ወደ ባሪያዬ ወደ ኢዮብ ሂዱ... እርሱ ይጸልይላችኋል" አላቸው (ኢዮብ ፵፪፥፰)።
- ምክንያት ፪፦ ትሕትናን ለመለማመድ። እኛ ኃጢአተኞች ስለሆንን "ጌታ ሆይ በንጹሐን ወዳጆችህ ጸሎት ማረኝ" ማለት በአምላክ ፊት መወደድን ያመጣል።
- ምክንያት ፫፦ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማሳየት። በሰማይ ያሉትና በምድር ያሉት ቅዱሳን በክርስቶስ ፍቅር አንድ ናቸው።
ማጠቃለያ፦ ክርስቶስ የመዳን መንገድና የሕይወት ባለቤት ነው። ቅዱሳን ደግሞ የዚያ መንገድ ምስክሮችና አብረውን የሚጸልዩ ወንድሞቻችን ናቸው። ክርስቶስን "አማላጅ" ብቻ አድርጎ ማቅረብ አምላክነቱን ዝቅ ማድረግ ሲሆን፤ "ቅዱሳን አያማልዱም" ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የሰጠውን ቃል ኪዳን መካድ ነው። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ግን ክርስቶስን እንደ ባሕርይ አምላክ ታመልካለች፤ ቅዱሳንን ደግሞ እንደ ባለሟል ታከብራለች።
ከቅርብ ሰው የተላከ የመተት መንፈስ ካለባችሁ ይኼንን ምልክት ታያላችሁ!! መስገድ ስትጀምሩ ጆሯችሁ ይከፈታል ሕሊናችሁ የነቃ ይሆናል!! #መተት #አጋንንት https://youtu.be/YDByEoh-tos
የመምህር ቀጣይ አገልግሎት የፊታችን እሁድ! በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁኝ ቤተሰቦቼ ይኼው የመምህር አገልግሎት ሙሉ መረጃና አድራሻው። #ሸር አድርጉ ለሁሉም።
አዲስ ቪዲዮ ይኼው! ይድረስ ለማንያዘዋል ወንድማችን!
https://youtu.be/9XP7Y5qbUbk?si=ZdjxAAFBsVZUWswc
እጸልያለሁ እሰግዳለሁ ነገር ግን መናፍስት አይጋለጡም ምልክት አጣሁ ለምትሉ!! ለጸሎት እንግዳ የሆነው ትውልድና መከራው!! https://youtu.be/43l2mjBtodQ
