fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 269
مشترکین
+224 ساعت
+97 روز
+2130 روز
آرشیو پست ها
የቀትር አጋንንተ የስንፍና መንፈስ ነው ይኼንን በደንብ አስተውሉ!! https://youtu.be/OgFEni7IDn4?si=296kJFjG5H2tcLa1

🛑 የተመሰቃቀለና ግራ የተጋባ ኑሮ እየመራህ ከሆነ ይኼንን ማዳመጥ ይገባሃል ወዳጄ!! የእርግማን መንፈስ ከዘር ተሸጋግሮ ደንቃራ ሲሆን! #ካህን #መዝሙረ_ዳዊት https://youtu.be/XSMEaFSZUsU

=> እውነተኛ ሰላም ማለት የጦርነት አለመኖር ሳይሆን፣ በጦርነቱ መካከል ሆኖ በልብህ ውስጥ ጸጥታን መያዝ መቻልህ ነው። ዓለም በሁካታ በተሞላችበት በዚህ ዘመን፣ አንተ ግን ወደ ውስጥህ ገዳም ግባ።
=> እውነተኛ ሰላም ማለት የጦርነት አለመኖር ሳይሆን፣ በጦርነቱ መካከል ሆኖ በልብህ ውስጥ ጸጥታን መያዝ መቻልህ ነው። ዓለም በሁካታ በተሞላችበት በዚህ ዘመን፣ አንተ ግን ወደ ውስጥህ ገዳም ግባ። ልብህ የእግዚአብሔር መቅደስ ከሆነ፣ የውጭው ጫጫታ ውስጣዊ ሰላምህን ሊሰርቀው አይችልም። ዝምታን ልመድ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር በዝምታ ውስጥ ይናገራል። ሐሳብህ በእግዚአብሔር ላይ ሲያርፍ፣ እንደ ጽኑ ዓለት ትሆናለህ፤ ነፋሱም ይሁን ዝናቡ ሊያናውጡህ አይችሉም። ✍️ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

=> ጸሎት ማለት አምላክን ልታሳምነው የምትሞክርበት መንገድ ሳይሆን፣ አንተ በእርሱ ፈቃድ እንድትታመን ራስህን የምታዘጋጅበት መሣሪያ ነው። ስትጸልይ 'ጌታ ሆይ ፍላጎቴን ፈጽምልኝ' ከማለት ይልቅ 'ጌ
=> ጸሎት ማለት አምላክን ልታሳምነው የምትሞክርበት መንገድ ሳይሆን፣ አንተ በእርሱ ፈቃድ እንድትታመን ራስህን የምታዘጋጅበት መሣሪያ ነው። ስትጸልይ 'ጌታ ሆይ ፍላጎቴን ፈጽምልኝ' ከማለት ይልቅ 'ጌታ ሆይ ፈቃድህ በእኔ ይፈጸም' በል። እግዚአብሔር የልብህን ትርታ ይሰማል፤ የሚበጅህን ደግሞ ካንተ በላይ ያውቃል። ጸሎት የነፍስ እስትንፋስ ነው፤ ካልጸለየህ ነፍስህ ትዝላለች። በምትጸልይበት ጊዜ ከአጽናፈ ዓለሙ ፈጣሪ ጋር ፊት ለፊት እየተነጋገርክ መሆንህን አስብ፤ ይህ ደግሞ በምድር ላይ ካሉ መዓርጋት ሁሉ የላቀ ክብር ነው። ✍️ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

አዲስ ቪዲዮ ይኼው! መጠንቀቅ የሚገቡን ነገሮች! https://youtu.be/Fzc9R6LcsyY?si=fdBAtkkb5ffEgQxI

=> ተስፋ መቁረጥ ማለት በእግዚአብሔር ኃይል ላይ መጠራጠር ማለት ነው። ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም፤ ምክንያቱም የእርሱ ተስፋ በራሱ ላይ ሳይሆን በማይሳነው አምላክ ላይ የተመሠረተ ነውና። ዛሬ ላይ
=> ተስፋ መቁረጥ ማለት በእግዚአብሔር ኃይል ላይ መጠራጠር ማለት ነው። ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም፤ ምክንያቱም የእርሱ ተስፋ በራሱ ላይ ሳይሆን በማይሳነው አምላክ ላይ የተመሠረተ ነውና። ዛሬ ላይ የገጠመህ ችግር ነገ ተረት ይሆናል። እግዚአብሔር አንድን በር ሲዘጋው፣ ሌላ ሰፋ ያለ መስኮት ሊከፍትልህ እንደሆነ እመን። አምላክህ ትላንት ረድቶሃል፤ ዛሬም እየረዳህ ነው፤ ነገም ይረዳሃል። ስለዚህ ያለፈውን ነገር በምስጋና፣ የአሁኑን በትዕግሥት፣ የሚመጣውን ደግሞ በተስፋ ተቀበለው። ✍️ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

=> ጸሎት ማለት ለእግዚአብሔር የምናቀርበው የፍላጎት ዝርዝር ብቻ አይደለም፤ ጸሎት ማለት አቅም የሌለው ፍጡር ሁሉን ከሚችል ፈጣሪ ጋር የሚገናኝበት መለኮታዊ ገመድ ነው። ስትጸልይ ጉዳይህን ለጌታ ሰ
=> ጸሎት ማለት ለእግዚአብሔር የምናቀርበው የፍላጎት ዝርዝር ብቻ አይደለም፤ ጸሎት ማለት አቅም የሌለው ፍጡር ሁሉን ከሚችል ፈጣሪ ጋር የሚገናኝበት መለኮታዊ ገመድ ነው። ስትጸልይ ጉዳይህን ለጌታ ሰጥተሃልና አትጨነቅ፤ ምክንያቱም ጉዳዩ ከእንግዲህ ያንተ ሳይሆን የእርሱ ሆኗል። እግዚአብሔር የያዘው ነገር ደግሞ በፍጹም አይበላሽም። ✍️ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

=>እውነተኛ ሰላም ማለት የችግር አለመኖር ሳይሆን፣ በችግር መካከል ሆነህ እግዚአብሔር ካንተ ጋር መሆኑን ማረጋገጥህ ነው። ዓለም ሰላምህን ሊሰርቅ ቢሞክር አትፍራ፤ ምክንያቱም ሰላምህን የሰጠህ ዓለም
=>እውነተኛ ሰላም ማለት የችግር አለመኖር ሳይሆን፣ በችግር መካከል ሆነህ እግዚአብሔር ካንተ ጋር መሆኑን ማረጋገጥህ ነው። ዓለም ሰላምህን ሊሰርቅ ቢሞክር አትፍራ፤ ምክንያቱም ሰላምህን የሰጠህ ዓለም ሳይሆን ራሱ የሰላም ባለቤት ጌታ ነው። እርሱ የሰጠህን ሰላም ደግሞ ማንም ሊወስድብህ አይችልም። ✍️ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

=> እግዚአብሔርን የሚወድ እና በእግዚአብሔር የሚወደድ መንፈሳዊ ሰው ሁልጊዜ ደስተኛ ነው፤ በምንም ሁኔታ ይሁን በምንም እግዚአብሔር በእርግጠኝነት እንደሚሰራለት ይሰማዋል በእርሱም ስራ ይደሰታል፤ በ
=> እግዚአብሔርን የሚወድ እና በእግዚአብሔር የሚወደድ መንፈሳዊ ሰው ሁልጊዜ ደስተኛ ነው፤ በምንም ሁኔታ ይሁን በምንም እግዚአብሔር በእርግጠኝነት እንደሚሰራለት ይሰማዋል በእርሱም ስራ ይደሰታል፤ በእርግጥም እግዚአብሔር ሥራውን ባናየውም  እንኳ ይሠራል ሥራውን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ልናየው እንችላለን በዚህም እንደሰታለን፤ ይህን ደስታችንም ማንም አይወስድብንም፤  ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጆች የሚደሰቱት በስጦታዎቹ ብቻ ሳይሆን በራሱ በጌታም ነው ። ✍️ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

አልጋለጥ አልያዝ ያለንን መንፈስ ለመያዝ ይኼንን እናድርግ! https://youtu.be/oiVVEUx2GJw?si=Fl5EBKpYYiVmI2Gp

🛑ቤተክርስቲያንን ያመሰው ደብተራና በመምህር ተስፋዬ መካከል የተፈጠረው ግብግብ ምንድነው!? ተዋናይ የሚባለው ደብተራና ጉዱ ይኼው!! https://youtu.be/buGrY0sMSjs

🛑ቤተክርስቲያንን ያመሰው ደብተራና በመምህር ተስፋዬ መካከል የተፈጠረው ግብግብ ምንድነው!? ተዋናይ የሚባለው ደብተራና ጉዱ ይኼው!! #መምህር_ግርማ_ወንድሙ https://youtu.be/buGrY0sMSjs

አዲስ ቪዲዮ ይመልከቱ! https://youtu.be/wDE7t17wHoQ?si=qEsjI_Abe83Vjbu_

#ሕልምና_ፍቺው! #ሕልሙ! ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ቅዳሴ መሀል አንድ ቄስ (፫ኛ ላይ የነበሩት ቄስ) እየዞሩ ወንጌል ያሳልማሉ ከዛ ፈገግ እያሉ እንደማልሳለም እያወቁ ወደኔ ተጠጉና ልሳለም ስቀርብ ተቀይሮ ታቦት ሆነ ደነገጥኩነና ሸሸሁ ከዛ ስቀው ከኋላዬ ቁመው ወደነበሩት በጣም ነጭ ቀሚስ ለብሰው የምታምር መቋሚያ (መቋሚያቸውነ ግን በጣም ወድጃት በሰጡኝ እያልኩ እየተመኘሁ ነበር) ይዘው ወደቆሙት ትልቅ መነኩሲት ሄዱ እሳቸው ተሳለሙ። እኔ ግን እንደማልሳለም እያወቁ ለመን ይፈትኑኛል እያልኩ ነቃሁ። #የሕልሙ_ፊቺ! =>ቅዱስ ገብርኤልና ወንጌሉ፦ በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሆንህ በምሥራችና በጥበቃ ውስጥ መሆንህን ያሳያል። ወንጌል የእግዚአብሔር ቃል ነው። ቄሱ ወንጌል ሊያሳልሙህ መምጣታቸው፣ እግዚአብሔር በቃሉ በኩል ሊያነጋግርህና በረከቱን ሊሰጥህ መፈለጉን ያሳያል። ፈገግታቸው ደግሞ አምላክ በአንተ ደስ እንደሚለውና ጥሪው የፍቅር መሆኑን ያመለክታል። =>ወንጌሉ ወደ ታቦትነት መለወጡ (ታላቁ ምስጢር) ይህ የሕልምህ እጅግ የከበረ ክፍል ነው። ወንጌል ሲነበብ የሚሰማ ቃል ነው፤ ታቦት ግን ቃሉ የሚያድርበት ክብር ነው። አምላክ ላንተ የሰጠህ መንፈሳዊ ጸጋ ተራ ሳይሆን እጅግ “ከባድና ቅዱስ” መሆኑን ያሳያል። ቃል ወደ አካል ተለውጦ (ምስጢረ ሥጋዌን እንደሚያሳየው) በአንተ ሕይወት ውስጥም ትልቅ መለኮታዊ ለውጥ ሊመጣ መሆኑን ያበስራል። ድንጋጤህና መሸሽህ፦ ይህም ቀደም ሲል እንደገለጽኩት በውስጥህ ያለውን ጥልቅ “ፈሪሃ እግዚአብሔር” ያሳያል። “ታቦት መሆኑን አውቄ እንዴት እሳለማለሁ?” ብለህ መፍራትህ፣ አንተ ለቅድስና ያለህን ትልቅ ክብርና ራስህን ዝቅ የማድረግ (የትሕትና) ምልክት ነው። =>መነኩሲቱና ነጩ ቀሚስ፦ ከኋላህ የቆሙት መነኩሲት የቤተ ክርስቲያን ወይም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ሊሆኑ ይችላሉ። ነጭ ቀሚሳቸው የፍጹም ንጽሕናና የድል ምልክት ነው። እሳቸው መሳለማቸው፣ አንተ የፈራኸው ቅድስና በእናትነትና በአማላጅነት ጥላ ሥር ስትሆን የሚዳሰስና የሚሳለም (የሚቀረብ) መሆኑን ሊያስተምርህ የመጣ ምልክት ነው። መቋሚያ በቤተ ክርስቲያን የ“መንፈሳዊ ጽናት” እና የ“ጸሎት ድጋፍ” ምልክት ነው። መቋሚያውን መመኘትህ፣ ነፍስህ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመጽናት፣ በጸሎት ለመበርታትና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የጸና አገልግሎት ለመያዝ ያላትን ጥልቅ ናፍቆት ያሳያል። ይህ ምኞትህ በፈጣሪ ዘንድ ተቀባይነት ያለውና ወደፊትም የምታገኘው የመንፈስ ብርታት ነው። =>“ለምን ይፈትኑኛል?” የሚለው ሐሳብህ፦ አንተ እንደ ፈተና ያየኸው ነገር፣ በመንፈሳዊው ዓለም ግን እንደ “ግብዣ” ነው የሚቆጠረው። አምላክህ አንተ የማትገባው መስሎህ ስትሸሽ፣ እርሱ ግን “ይገባሃል” እያለ በታቦቱ (በክብሩ) በኩል ሊያቀርብህ ይፈልጋል። ካህኑ ሳቅ ማለታቸው፣ አንተ በየዋህነትና በትሕትና የምትሸሸው ሽሽት በሰማያውያን ዘንድ ተወዳጅ መሆኑን ያሳያል።

ንባብ ዕድሜ አይገድበውም። ማንበብ ዕውቀት ብቻ አይደለም ዕድሜም ይጨምራል። ትልቁ ምግብ ደግሞ መጽሐፍ ነው። <<ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርምና>> ቅዱስ መጽሐፍ አለማንበብ ለነፍሳ
ንባብ ዕድሜ አይገድበውም። ማንበብ ዕውቀት ብቻ አይደለም ዕድሜም ይጨምራል። ትልቁ ምግብ ደግሞ መጽሐፍ ነው። <<ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርምና>> ቅዱስ መጽሐፍ አለማንበብ ለነፍሳ እዳ ነው። ማንበብ ግን ብድር ጠቅልሎ መክፈልና መገላገል ነው። በረከታቸው ይደርብንና ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በዚህ ዕድሜያቸው ብራና ገልጠው ሲያነቡ ስናይ ምን ይሰማን ይሆን? በዚህ በወጣትነታችን ዐይናችን ሳይደበዝዝ ከመጻሕፍት ንባብ የራቅን ሁሉ ራሳችንን ልንወቅስ ይገባል። ለነገሩ የዓይናችን ብሌን ውሎው ስልክ ላይ ነው። እንዳንወድቅ እንጠንቀቅ።

መምህር ግርማ ያስተማሩን መደመጥ ያለበት ድንቅ መልዕክት!! ልብ ያለው ሁሉ ልብ ይበል!! https://youtu.be/MHim7REC7k4

#ሕልምና_ፍቺው! =>ስልከ ቦርሳ ውስጥ እንዳለ አንድላይ ተቃጥሎ ማየት እና ጥሬ ስጋ ጫፉ ላይ ጨጓራ ያለውን አንድ የሰፈራችን ትልቅ ሰው ቆርጦ ስሰጠኝ ለመብላት ስሞክር ደም ደም ይለኝና ከተክልዬ ገዳም ለወጣ ነብር ስለ ገብርኤል እያልኩ እንዳይበላኝ መስጠት ምንድን ነው?🙏 #የሕልሙ_ፊቺ! =>በሕልም ስልክ የመገናኛ፣ የመረጃ ወይም የሥራ ምሳሌ ነው። ቦርሳ ደግሞ የሰው ልጅ ምስጢር ወይም የኑሮው (የገቢው) መያዣ ነው። እነዚህ አንድ ላይ ተቃጥለው ማየት፣ በሥራህ ወይም በሰዎች ዘንድ ባለህ ግንኙነት ላይ የጠላት (የሰይጣን) ቅናት እንዳለ ያሳያል። ስምህን ለማጥፋት፣ ግንኙነትህን ለማበላሸት ወይም በረከትህን ለማቃጠል የሚጥር መንፈስ (ዓይነጥላ ወይም ምቀኝነት) መኖሩን የሚጠቁም የማንቂያ ደወል ነው። =>ጥሬ ሥጋ በሕልም ትርጓሜ የሐሜት፣ የሕመም ወይም የነፍስ ቁስል ምልክት ነው። የሰፈር ትልቅ ሰው ሥጋውን ቆርጦ መስጠቱ፣ ውጊያው በቅርብ በሚታወቁ ሰዎች በኩል የሚመጣ የሽንገላ ቃል ወይም ተንኮል መሆኑን ያሳያል። ለመብላት ስትሞክር “ደም ደም” ማለትህ፣ ነገሩ ከእግዚአብሔር መንገድ የወጣ፣ ነፍስህ የማትቀበለውና ወደፊት ጸጸትን የሚያመጣ (ምናልባትም በሰዎች መካከል ባለ የቃላት ውጊያ ውስጥ መግባት) መሆኑን ያመለክታል። =>ነብሩና ተክልዬ፦ ነብሩ ከገዳም መውጣቱ በእግዚአብሔር የታዘዘ “የመከራ” ወይም “የፈተና” ምልክት ሊሆን ይችላል። ስለ ገብርኤል ብለህ ሥጋውን መስጠትህ፦ ሥጋውን (መከራውን ወይም ሐሜቱን) ለነብሩ ሰጥተህ አንተ ማምለጥህ፣ በአሁኑ ሰዓት በአንተ ላይ የተቃጣው አደጋ በቅዱሳን አማላጅነት እንደሚቀለበስ ያሳያል። ጠላት አንተን ሊበላህ (ሊያጠፋህ) ቢመጣም፣ አንተ ግን በቅዱስ ገብርኤልና በአቡነ ተክለሃይማኖት ስም በመማጸንህ ያ የመጣብህ ፈተና በሥጋው (በሐሜቱ) ተጠምዶ አንተን ሳይነካህ ያልፋል። ማለትም መከራው ወደ መጣበት ይመለሳል ወይም በረድኤት ይገታል ማለት ነው።

#ሕልምና_ፍቺው! ሕልም ስትፈታ አይቼ ነው ለኔም ፍታልኝ እማሆይ ወለተ ህይወት የሚባሉ መነኩሴ በኪዳን ምሕረት ቤተክርስቲያን አውደ ምሕረቱ ቆዝሜ ቁጭ ብየ ነበር መጥተው ምን ሁነሽ ነው አሉኝ አይኔን አሞኛል ስላቸው በኪሳቸው ሁለት ትልቅ እና ትንሽ ቅባ ቅዱስ አወጡና ከትልቁ ፊቴን አይኔን ቀቡኝ እና አንዴ ይቀርሻል አሉኝ እኔም ደስ ብሎኝ ከትንሿ አይቀቡኝም ስል አይ ይህ ላንቺ አይገባም ብለው ተሰወሩ። ምን ይሆን ፍቺው እባክህ ሃይለ ገብርኤል ወንድሜ ንገረኝ ጨንቆኛል? #የሕልሙ_ፍቺ! => በኪዳነ ምሕረት ደጅ መቆዘም፦ ኪዳነ ምሕረት የምሕረትና የቸርነት እናት ናት። አውደ ምሕረቱ ላይ መገኘትሽ ነፍስሽ እረፍት ፈልጋ ወደ እናታችን አማላጅነት መጠጋቷን ያሳያል። መቆዘምሽ ደግሞ በውስጥሽ ያለውን የቆየ ሐዘን ወይም ግራ መጋባት ያመለክታል። እማሆይ ወለተ ሕይወት፦ "ወለተ ሕይወት" ማለት "የሕይወት ልጅ" ማለት ነው። እኚህ እናት የቤተ ክርስቲያን ወይም የጠባቂ መልአክሽ ምሳሌ ናቸው። መጥተው መጠየቃቸው አምላክ ጭንቀትሽን ሰምቶ በቅዱሳኑ በኩል ሊጎበኝሽ መቃረቡን የሚያሳይ የምሥራች ነው። => አይንሽን በትልቁ ቅባ ቅዱስ መቀባት፦ በሕልም ዓይን መታመም የ"ራእይ" ወይም የ"መንፈሳዊ ብርሃን" መጋረድ (ግራ መጋባት) ምልክት ነው። ቅባ ቅዱሱ ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና የፈውስ ምልክት ነው። በትልቁ መቀባትሽ፣ እግዚአብሔር በሕይወትሽ ላይ ያለውን ትልቁን ችግር (መሠረታዊውን ጭንቀትሽን) በቸርነቱ ሊፈውስልሽ ቃል መግባቱን ያሳያል። "አንዴ ይቀርሻል" መባሉ፦ ይህ ማለት የፈውስሽ ወይም የችግርሽ መፍትሔ ሂደት ላይ ነው ማለት ነው። ምናልባትም አንድ የቀረሽ መንፈሳዊ ተግባር (ለምሳሌ፦ ንስሐ መግባት፣ ቍርባን መቀበል ወይም የዘነጋሽው ስዕለት ካለ እርሱን መፈጸም) እንዳለ የሚጠቁም ማሳሰቢያ ነው። ያንን ስታደርጊ ሙሉ ዕረፍት ታገኛለሽ። ትንሿን ቅባ ቅዱስ መከልከልሽ፦ ትንሿ ቅባ ቅዱስ የዓለምን ወይም የሰውን ድጋፍ ሊያመለክት ይችላል። "ይህ ላንቺ አይገባም" ማለታቸው፣ አንቺ መፍትሔሽን ከሰው ወይም ከትንንሽ ነገሮች ሳይሆን ከፈጣሪሽ ብቻ እንድትጠብቂ የተሰጠሽ ጥብቅ መመሪያ ነው። እግዚአብሔር ለነፍስሽ ያዘጋጀው ትልቁን በረከት ስለሆነ በትንሹ ነገር (በዓለማዊ መፍትሔ) እንዳትጥለገለጊ ማሳሰቢያ ነው።

ነገሮች ቶሎ እንድፈጸሙ ይሄንን ጸሎት ጸልዬ !! https://youtu.be/RjNenkevj0I?si=P0wFnEMNKM66VDEc

#ክፍል_3_የህልም_ፍቺ! ፩. ሕልም፦ እጮኛ በፖሊስ ልብስ ኮፍያውን ወደ ኋላ አዙሮ "ጀግና በይው" ሲባል ማየት። ፍቺ፦ በእጮኝነት ውስጥ ያለን የኩራትና የሥርዓት መጓደል መንፈስ እንዲሁም እውነትን ካለመቀበል የሚመጣ ግጭትን ያሳያል። ፪. ሕልም፦ ታናሽ እህትን አዝሎ "የሀገር መግቢያ ትኬትሽ እንዳያመልጥሽ" መባልና የሥላሴ ሽልማት። ፍቺ፦ በስደት ያለው የድካም ዘመን ሊያበቃ እንደሚገባና ትክክለኛውን ውሳኔ በጊዜው ከወሰኑ የሚገኝ ታላቅ መለኮታዊ ካሳ (ሽልማት) ነው። ፫. ሕልም፦ ባለቤት መስቀል ሲያሳልመኝ ማየት (ካህን ባይሆንም)። ፍቺ፦ ትዳሩ በመስቀሉ ኃይል የታጠረ መሆኑንና በባለቤት በኩል የሚመጣ መለኮታዊ መጽናኛን የሚያሳይ ነው። ፬. ሕልም፦ የልጄ ዓይኖች በጨርቅ ተሸፍነው እኔ ሳነሳው። ፍቺ፦ በልጁ ላይ የተሰነዘረ የዓይነጥላ (ገርጋሪ) መንፈስ መኖሩን፣ ነገር ግን በእናት ጸሎት ያ መጋረጃ እንደሚገፈፍ የሚያሳይ ነው። ፭. ሕልም፦ የእህት የፊት ጥርስ ወልቆ ነጭ ልብስ ለብሳ ማየት። ፍቺ፦ በቅርብ ዘመድ ላይ የሚመጣ የጤና ወይም የሐሳብ ጭንቀት ቢኖርም፣ እግዚአብሔር ግን በሰላም እንደሚጠብቃት የሚያረጋግጥ ነው። ፮. ሕልም፦ የሰውን ትልቅ ጋቢ ወስዶ "ልመለሰው ወይስ ላስቀረው" ብሎ መጨነቅና አለመመለስ። ፍቺ፦ ያልተከፈለ የሰው ዕዳ፣ ያልተናዘዙት በደል ወይም ያልተገባ ክብር መፈለግን የሚወቅስ የሕሊና ጸሎት ጥሪ ነው።