fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 271
مشترکین
-424 ساعت
+127 روز
+2630 روز
آرشیو پست ها
#ተጠንቀቁ! የደላላውን የመናፍስት ጉዳትና ፈተና አዳምጣችሁ እራሳችሁን ፈትሹ!! ጎበዟ ጸሎተኛ እንዴት የመናፍስትን ውጊያ በቀላሉ ተረዳች!! #ጸሎት #ስግደት https://youtu.be/NujKn06fuRU

3ቱ ውሸቶች ስለ አባ ዮሐንስ ተስፋማሪያም የተነገሩ በብጹዓን አባቶች ስገለጽ!! ቆሞስ አባ ሳሙኤል ስለ መምህር ግርማ የተናገሩት! #ወንቅሸት #ገዳም #ጸሎት https://youtu.be/ycrMnag8pBk

እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ እና ለቅዱሳን አበው አብርሃም አባ_ሲኖዳ እና አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሥሉስ ቅዱስ በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው:: አብ :ወልድ : መንፈስ ቅዱስ በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና:: ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት "ቅድስት ሥላሴ" እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም:: የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው ያድራሉ:: ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር ለሚሻው በፍቅር ይመጣል:: አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!) ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: ቅድስት ሣራ ሳቀች:: እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ" ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው "ይስሐቅ" የተባለው:: ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ አብ ለአጽንኦ: መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ: ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና:: ሐምሌ 7 ሥሉስ ቅዱስ ለአብርሃም የተገለጠለት በቤቱም የተስተናገዱበት ዕለት ነው። ©ዝክረ ቅዱሳን ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ» አብርሃም ወሰዶ ለይስሐቅ ወልዱ ከመ ይሡዖ አውረደ ሎቱ ቤዛሁ በግዐ። ቤዛ ይስሐቅ በግዕ መጥቶ ይስሐቅን ከመታረድ እንዳዳነው ቤዛ አዳም ክር
«እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ» አብርሃም ወሰዶ ለይስሐቅ ወልዱ ከመ ይሡዖ አውረደ ሎቱ ቤዛሁ በግዐ። ቤዛ ይስሐቅ በግዕ መጥቶ ይስሐቅን ከመታረድ እንዳዳነው ቤዛ አዳም ክርስቶስ መጥቶም ሰው ሁሉ ከሞተ ሥጋ ከሞተ ነፍስ ድኗል። ያዳነን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሰገነ ይሁን። በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ። ፎቶ፦ ጎንደር ንግሥተ አድባራት ደብረ ብርሃን ሥላሴ

«እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ» አብርሃም ወሰዶ ለይስሐቅ ወልዱ ከመ ይሡዖ አውረደ ሎቱ ቤዛሁ በግዐ። ቤዛ ይስሐቅ በግዕ መጥቶ ይስሐቅን ከመታረድ እንዳዳነው ቤዛ አዳም ክርስቶስ መጥቶም ሰው ሁሉ ከሞተ ሥጋ ከሞተ ነፍስ ድኗል። ያዳነን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሰገነ ይሁን። በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ። ፎቶ፦ ጎንደር ንግሥተ አድባራት ደብረ ብርሃን ሥላሴ

የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ ረድኤት በረከት ይደርብን። አማላጅነቷ ከሁላችን ጋር ይሁን። #ጸሎት #አርሴማ #ቅድስት
የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ ረድኤት በረከት ይደርብን። አማላጅነቷ ከሁላችን ጋር ይሁን። #ጸሎት #አርሴማ #ቅድስት

በዝሙት መተት መያዛችንን የሚያሳዩ ምልክቶችና መፍትሔዎቹ!! የዝሙት መተት መንፈስን ለማሸነፍ ምን እናድርግ? የዝሙት መተትና ያልገባን የሕይወት ፈተናዎቻችን! https://youtu.be/tLhOp9xKDfc?si=iojQ9-ILzHmEAp-B

በቤታችሁ የጸሎት ቤት ሲኖራችሁ ይኼንን በረከትና መፈወስ ታገኛላችሁ!! የጸሎት ቤትና የዲያብሎስ ውጊያ!! የሰላቢን መንፈስ ለመዋጋት የጸሎት ቤት ያለው ጥቅሙ! https://youtu.be/qQm_jYccGps

ሐምሌ ፭ /5/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አምስት በዚች ቀን የክቡራንና የዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት የጴጥሮስና የጳውሎስ የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ ነው። ይህም ጴ
ሐምሌ ፭ /5/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አምስት በዚች ቀን የክቡራንና የዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት የጴጥሮስና የጳውሎስ የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ ነው። ይህም ጴጥሮስ ከቤተ ሳይዳ ነበር ዓሣ አጥማጅም ነበር ጌታችንም ከተጠመቀባት ዕለት ማግሥት አግኝቶ መረጠው ከእርሱ አስቀድሞም ወንድሙ እንድርያስን አግኝቶ መረጠው። መድኃኒታችንንም እስከ መከራው ጊዜ ሲአገለግለው ኖረ ፍጹም ሃይማኖት ለጌታውም ቅንዓትና ፍቅር ነበረው ። ስለዚህም በሐዋርያት ሁሉ ላይ አለቃ አድርጎ ሾመው። በመጨረሻም ተጋድሎውን ፈጽሞ ቁልቁል ተሰቅሎ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ጳውሎስ አስቀድሞ በክርስቶስ ያመኑትን የሚያሳድድ ነበረ እርሱም ከብንያም ወገን የፈሪሳዊ ልጅ ነው። ወላጆቹም ሳውል ብለው ስም አወጡለት ትርጓሜውም ስጦታ ማለት ነው። እርሱም ሕገ ኦሪትን አዋቂ ነበረ። ለሕጉም ቀናተኛ ሆኖ ምእመናን አሳዳጅ ነበረ። እግዚአብሔርም በመብረቅ ገስጾ ምርጥ እቃ አደረገው። በመጨረሻም ሐዋርያዊ አገልግሎቱን  በሰማዕትነት ፈጽሞ አንገቱን ተሰይፏል። አስራ አራት መልዕክታትንም ጽፏል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በትክክል መጸለይ ስትጀምሩ በጸሎት ውስጥ ያሉ ፈተናዎችን ማወቅ ትችላላችሁ!! ሕጻናትን ለቆሪጥ አጋንንት የሚገብሩ ባለሃብቶችና ያልተረዳነው የመናፍስቱ ጉዳት!! https://youtu.be/SgpNz1y5-Uw

«ትሕትና የሁሉም በጎነቶች መሠረት ነው። በክርስትና ሕይወት ውስጥ እውነተኛ ታላቅነት የሚገኘው ከሹመት ወይም ከኃይል ሳይሆን፣ በእግዚአብሔርና በሰዎች ፊት ካለን ትሕትና ነው። "ያለ ጸሎት ያለ ቀን
«ትሕትና የሁሉም በጎነቶች መሠረት ነው። በክርስትና ሕይወት ውስጥ እውነተኛ ታላቅነት የሚገኘው ከሹመት ወይም ከኃይል ሳይሆን፣ በእግዚአብሔርና በሰዎች ፊት ካለን ትሕትና ነው። "ያለ ጸሎት ያለ ቀን ያለ በረከት ነው" ጸሎት ግዴታ ብቻ ሳይሆን የነፍስ እስትንፋስ ነው፤ መጽሐፍ ቅዱስም የዕለት መንፈሳዊ ምግባችን ነው። በልብህ ጥላቻን ይዘህ ክርስቲያን ነኝ ማለት አትችልም፡ ሰላምና ይቅርታ፣ ክርስቶስ በእውነት በሚኖርበት ልብ ውስጥ የሚገኙ ምልክቶች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን የሥርዓት ቦታ ብቻ ሳትሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝባት ስፍራ ናት። ይህ የሚያስታውሰን የክርስትና ሕይወት የውጪ ተግባር ብቻ ሳይሆን፣ ይልቁንም በትሕትና፣ በጸሎትና በፍቅር የሚመጣ ጥልቅ መንፈሳዊ ለውጥ መሆኑን ነው።» (ቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ» (የማቴዎስ ወንጌል 21፡33-46) «ሌላ ምሳሌ ስሙ። የወይን አትክልት የተከለ ባለቤት ሰው ነበረ፤ ቅጥርም ቀጠረለት፥ መጥመቂያም ማሰለት፥ ግንብም ሠራና ለገበሬዎች አከ
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ» (የማቴዎስ ወንጌል 21፡33-46) «ሌላ ምሳሌ ስሙ። የወይን አትክልት የተከለ ባለቤት ሰው ነበረ፤ ቅጥርም ቀጠረለት፥ መጥመቂያም ማሰለት፥ ግንብም ሠራና ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። የሚያፈራበትም ጊዜ ሲቀርብ፥ ፍሬውን ሊቀበሉ ባሮቹን ወደ ገበሬዎች ላከ። ገበሬዎቹም ባሮቹን ይዘው አንዱን ደበደቡት አንዱንም ገደሉት ሌላውንም ወገሩት። ደግሞ ከፊተኞች የሚበዙ ሌሎች ባሮችን ላከ፥ እንዲሁም አደረጉባቸው። በኋላ ግን። ልጄንስ ያፍሩታል ብሎ ልጁን ላከባቸው። ገበሬዎቹ ግን ልጁን ባዩ ጊዜ እርስ በርሳቸው። ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ፥ እንግደለውና ርስቱን እናግኝ ተባባሉ። ይዘውም ከወይኑ አትክልት አወጡና ገደሉት። እንግዲህ የወይኑ አትክልት ጌታ በሚመጣ ጊዜ በእነዚህ ገበሬዎች ምን ያደርግባቸዋል? እነርሱም። ክፉዎችን በክፉ ያጠፋቸዋል፥ የወይኑንም አትክልት ፍሬውን በየጊዜው ለሚያስረክቡ ለሌሎች ገበሬዎች ይሰጠዋል አሉት። ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን? ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች ፍሬዋንም ለሚያደርግ ሕዝብ ትሰጣለች። በዚህም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ ድንጋዩ ግን የሚወድቅበትን ሁሉ ይፈጨዋል። የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን ሰምተው ስለ እነርሱ እንደ ተናገረ አስተዋሉ፤ ሊይዙትም ሲፈልጉት ሳሉ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስላዩት ፈሩአቸው።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»

ለመሆኑ በየፌስቡኩና በዩቲዩብ በቲክቶክ ሲሳደቡ ሲነቅፉ የሚውሉ እነርሱ ለቤተክርስቲያን ምን ሠርተዋል? አንድ ቤተክርስቲያን አሰርተዋል? ገዳማትን አቋቁመዋል? ጧሪ ቀባሪ ያጡ አረጋውያንን ሰብስበው ይረዳሉ? ወላጅ አልባ ሕጻናትን ያሳድጋሉ? ለቤተክርስቲያን ተገቢውን አሥራት ያወጣሉ? ወይስ እየተሳደቡ ሳንቲም ይለቃቅማሉ? ደግሞስ ማነው እኔ ምንም ኃጢአትና በደል የሌለብኝ ንጹሕ ነኝ የሚል? ሁላችን በቤቱ ያለነው በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ ስላልን አይደለም? አንዳንዶችማ አንድም ቀን ቤተመቅደስ ገብተው ቀድሰው፣ አወድሰው፣ ማኅሌት ቆመው፣ ሰዓታት አድርሰው የማያውቁ ወገበ ነጮች በቤተክርስቲያን ትምህርት የደከሙ ሊቃውንትንና ብፁዓን አባቶችን ሲሳደቡ ሲያዋርዱ እያየን አዕምሯቸው የቀነጨረ ምናምንቴ መሆናቸውን እየታዘብን ነው። ትናንት የፕሮቴስታንት ፓስተር ሆኖ ድንግል ማርያምንና ቅዱሳንን ሲሳደብ የኖረ ብንያም ሽታዬ የተባለ አንድ ተራ ግለሰብ ዘመናቸውን ሙሉ ቅዱሳንን ሲያከብሩ ለድንግል ማርያም ክብር ሲሰጡ በየገዳማቱና በየበረሃው ለአገልግሎት ሲተጉ የኖሩ አባቶችን በየሚዲያው ሲያበሻቅጥ ማየት እጅግ ያሳፍራል ከእርሱ ጋር ሆነው ሆያ ሆዬ የሚሉ ሰዎችም ከእርሱ የማይሻሉ ምናምንቴዎች ናቸው። ስለዚህ ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስቲያንን ክብር፣ ጥቅምና ሉዓላዊነትን ማዕከል በማድረግ በሕዝብ መካከል እየተነሳ ላለው ውዝግብ አስፈላጊውን መፍትሔ ይሰጥ ዘንድ በእክብሮት እንጠይቃለን። መ/ር ታሪኩ አበራ ሼር በማድረግ ለአባቶች አድርሱ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

† ለቅዱስ ሲኖዶስ † « ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን »1ኛ ቆር 14፥40 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት ታሪክና ጠንካራ ተቋማዊ የአስተዳደር መዋቅሯን ጠብቃ በክብር ዘመናትን የተሻገረች ታላቅ የእግዚአብሔር ተቋም ነች። ቤተክርስቲያኒቱ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን በምታስተላልፍበት ጊዜ ሁሉ መሠረቷ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ድንጋጌዎቿ ቤተክርስቲያንን ወደ ሰላም ወደብ እያሻገረ ከዘመናችን አድርሷታል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በመንጋ ፍርድና በማኅበራዊ ሚዲያ በሚፈጠሩ መርሕ አልባ ጩኽቶች የብፁዓን አባቶች ስም ሲሰደብና ሲዋረድ በተደጋጋሚ እየተመለከትን ነው። ይህ የቅዱስ ሲኖዶስን ክብርና ልዕልና የሚያንኳስስ የግለሰብና የጥቂት ቡድኖች ጫጫታ የብዙ ምዕመናንን ልቡና እያዋከ የሚገኝ ሲሆን እንደ ተቋም ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሌሎች ቤተ እምነቶች መቀለጃና መሳለቂያ እንድትሆን እየደረጋት ይገኛል። ለዚህ ሁሉ ችግር መከሰት ምክንያት ደግሞ የጠቅላይ ቤተክህነት የሕግ ክፍልና የሚዲያ ዲፓርትመንት የጋራ ጥምረት በመፍጠር የቤተክርስቲያኒቱን ክብርና ሉዓላዊነት የሚያዋርድ ተግባራት የሚፈጽሙ ግለሰቦችንና ቡድኖችን እየተከታተሉ በየትኛው የማኅበራዊ ሚዲያ ፕላት ፎርሞች ላይ ለሚመለከተው አካል ሪፓርት እያደረጉ ባለማዘጋታቸውና በቸልተኝነት ነገሮችን አቅልለው በመመልከታቸው የሚፈጠር ችግር ነው። በቅርቡ አባ ዮሐንስ የተባሉ መናኝ በሰሜን አሜሪካ ቤተክርስቲያን ሊከፍቱ ነው በሚል ምክንያት ብዙ ውዝግብና እሰጣገባ በየሚዲያው እየተመለከትን ነው። ጉዳዩ ከልክ በላይ እየተለጠጠ ሄዶ የቤተክርስቲያኒቱ ታላላቅ አረጋውያን ሊቃነ ጳጳሳት ሳይቀሩ ማንም እየተነሳ ሲሰድባቸው፣ ሲያንጓጥጣቸውና ሲዋርዳቸው እየተመለከትን ውስጣችን በጣም እያዘነ ነው። እነዚህ አረጋውያን ብፁዓን አባቶች ዕድሜያቸውን ሙሉ ቤተክርስቲያንን ሲያገለግሉ የኖሩ፣ በቤተክርስቲያን ትምህርት በቂ ሙያና ልምድ ያካበቱ፣ በፈተና ሰዓት ለቤተክርስቲያን የግንባር ሥጋ ሆነው መከራን የታገሉ፣ ሌሊትና ቀን የክርስቶስን ቤተመቅደስ በክህነት የሚያገለግሉ ለቤተክርስቲያን ዕድገትና ከፍታ ከማናችንም በላይ ግድ የሚላቸው ዋኖቻችን ናቸው። አለመታደል ሆኖ ግን ማንነታቸውና ምንነታቸው የማይታወቁ የፌስቡክ አርበኞች ከብፁዓን አባቶች በላይ ለቤተክርስቲያን አሳቢና ተቆርቋሪ መስለው ከጀርባቸው የተለያየ የፓለቲካና የጥቅም ድብቅ አጀንዳ ተሸክመው እግረ መንገዳቸውንም የዩ-ቲዩብና የቲክቶክ ምጽዋት ሳንቲሞችን ተስፋ አድርገው ነገሮችን በሚዛናዊነት መመልከት ያልቻሉ ምዕመናን ግራሲያጋቡ እየተመለከትን በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ውሳኔና ሕጋዊ እርምጃዎችን በመውሰድ የቤተክርስቲያንን ክብር ያስጠብቅ ዘንድ በአጽንዖት ማሳሰብ እወዳለሁ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ መናኝ ባሕታውያን የከበረ ሥፍራና የላቀ ጥቅም አላቸው በጸሎታቸው ሃገርን ከጥፋት ሕዝብን ከስደት ይጠብቃሉ፣ ከእግዚአብሔር በሚሰጣቸው መልዕክት ኃላፍያትንና መጻዕያትን በመናገር ቀናውን መንገድ ለሕዝብና ለካህናት ያመላክታሉ፣ ምዕመናን በፈሪሃ መለኮት፣ በቅድስና፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት እንዲኖሩ መልካም አርአያ በመሆን ትውልድን ለትሩፋት ሥራ ያነቃሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ እንደዛሬው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ከመሥፋፋቱና መንፈሳዊ ኮሌጆች ከመበራከታቸው በፊት በመላ ሃገሪቱ በመዘዋወር የወንጌል ብርሃንን ያዳረሱ ሕዝቡን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለሱ ፣ከአባይ ጠንቋይ፣ ከባዕድ አምልኮ እስራት አላቀው ወደ ክርስቶስ ፍቅር የሰበሰቡ ሰባኪ ባሕታውያን ናቸው። ከአጼ ኃይለ ሥላሴ እስከ ደርግ ዘመነ መንግሥት ከዚያም በኋላ ከኢኃዴግ አሁን እስካለሁ ሥርዓት ድረስ ለቤተክርስቲያን ጠበቃ በመሆን አምባገነን ፓለቲከኞችን ፊትለፊት በመጋፈጥ የቤተክርስቲያንን ክብርና ልዕልና ያስከበሩ በዚህም ብዙ እስርና እንግልት የተቀበሉ እነዚሁ መናኝ ባሕታውያን ናቸው። ከአጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመንግሥት በፊትም ምንም እንኳ ብዙ የከፋ የፓለቲከኞች ጫና ቤተክርስቲያንን ባይፈትናትም ባሕታውያን በተለያየ ጊዜ ብቅ እያሉ መንፈሳዊ መልዕክታቸውን ያስተላልፉ ነበር። ጸረ ኦርቶዶክስ ሥርዐት በኢትዮጵያ ከመጣበት ከደርግ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በመላ ኢትዮጵያ በመዘዋወር አዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲተከል ሕዝብ ያስተባበሩ፣ ገዳማትን በሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ በመርዳት ያጠናከሩ፣ ሃይማኖት እንዲሰፋ ምዕመናን በእምነት እንዲበረቱ ትልቅ አስተዋጽዖ ያደረጉ እነዚሁ መናኝ ባሕታውያን ናቸው። ከቅርብ ጊዜ ትዝታዎቻችን በዋነኝነት የምናስታውሳቸው። * ባሕታዊ አባ ገበሬው *ባሕታዊ አባ ገ/እግዚአብሔር * ባሕታዊ አባ መሸ በከንቱ *ባሕታዊ ቀለመወርቅ *ባሕታዊ ገ/መስቀል * ባሕታዊ አምሐ ኢየሱስና ሌሎችም በስፋት ይገለጻሉ። እነዚህ ባሕታውያን በወቅቱ ቤተክርስቲያንን በዘመናቸው ብዙ ቢጠቅሟትም አንዳንድ ክፉ ልብ ያላቸው ሰዎች በቅንዓት መንፈስ ሌሊትና ቀን ያለ እረፍት ስማቸውን በማጥፋትና በማሳደድ ከአገልግሎት ውጪ ሲያደርጓቸው እነዚህ መናንያን የሞት ሽረት ትግል አድርገው በቤተክርስቲያን ውስጥ አንገታቸውን ሰብረው እንዲኖሩ ተደርገዋል። እነዚህ መናንያንን ቤተክርስቲያን በአግባቡ ብትጠቀምባቸውና ሲያጠፉ እየገሰጸች፣ ሲያለሙ እያመሰገነች በመዋቅር ውስጥ ተይዘው በሕግና በሥርዓት አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ ብታደርግ ቤተክርስቲያኒቱ ብዙ ታተርፍ ነበር። አለመታደል ሆኖ ግን እጃቸውን አለስልሰው ምላሳቸውን አርዝመው የሰው ስም እያጠለሹ በብዕርና በምላስ መርዝ ብዙዎችን እየገደሉ የሚውሉ ለቤተክርስቲያን አንዳች ነገር ሳይሰሩ ሆድና ማጅራታቸውን እያሳበጡ ተቀምጠው በአገልግሎት የሚደክሙና የሚሰሩ ሰዎችን ሲያኮላሹ የሚኖሩ ርጉማን ሰዎች በየቤተክርስቲያኑ ተሰግስገው ቤተክርስቲያንን በጣም ጎድተዋታል። ይህ ብልሹ ያለፈ ታሪክ ዛሬም ሲደገም እያየን በጣም እያዘንን ነው። ባሕታዊ አባ ዮሐንስ ከ 10 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸዋል፣ ገዳማትን አልምተዋል፣ ጥርጊያ መንገድ አሰርተዋል፣ የአቅማቸውን ያህል ሕዝብን እያስተማሩ ብዙዎች ወደ መንፈሳዊ ሕይወት እንዲመጡ ሲጥሩ ይታያል ይህ ሁሉ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቀሪ ሐብትና ቅርስ ነው። የእሳቸውን ሩብ ያህል እንኳን መሬት ላይ ወርደው ያልሰሩ ሰዎች በየሚዲያው ሲሳደቡ፣ ሲራገሙ፣ አቃቄር ሲያወጡ እየተመለከትን በንግግራቸው እጅግ እያፈርን ነው። ሰውየው ያጠፉትና የተሳሳቱት ነገር ካለ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ አካል ቅዱስ ሲኖዶስና የሚመለከተው የጠቅላይ ቤተክህነት መምርያ ተከታትሎ እርምት በሚያስፈልገው ጉዳይ እርምት እየሰጠ፣ የዕውቀት ክፍተት ካለ በትምህርት የሚያድጉበትን መንገድ እያመቻቸ፣ ውይይት በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት እያደረገ፣ ከሰው ስህተትና ውድቀት አይጠፋምና ይህም በተጨባጭ ተገኝቶ ከሆነ በመንፈሳዊ ቀነኖ እያረሙ የቤተክርስቲያንን ጥቅም በማስቀደም እንዲህ ዓይነት ሰዎችን በመዋቅር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ በመያዝ ቤተክርስቲያን ልትጠቀምባቸው ይገባል እንጂ በየፌስቡኩ ሲንጫጩ በሚውሉ አውርቶ አደር ሥራ ፈት መንደርተኞች የቡና ወሬ ሕዝብ ሲታወክ ዝም ብሎ መመልከት አግባብ አይደለም።

ለእግዚአብሔር ብላቻሁ ያቆማችሁትና የተዋችሁት ነገር ምንድነው?? የጸሎትና የስግደት ጊዜ በማጣታችን ይኼ ሁሉ ሆነብን! #በጸሎትና #በሱባኤ #ጦርነት #መቁጠሪያ https://youtu.be/q9RvGPfBBpw

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!» (የማቴዎስ ወንጌል 18፡15-23) «ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁ
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!» (የማቴዎስ ወንጌል 18፡15-23) «ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና። በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ወደ እርሱ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ልተውለት? እስከ ሰባት ጊዜን? አለው። ኢየሱስ እንዲህ አለው። እስከ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ እስከ ሰባት ጊዜ አልልህም።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ማንንም፣ ምንምም እንጣ ከማንም በላይ በጨለማው ጊዜያችን የነበረውን ክርስቶስ ግን እንዳንተው! አደራ እርሱን ብቻ እንዳናጣ ሌላው ትርፍ ነው!»
«ማንንም፣ ምንምም እንጣ ከማንም በላይ በጨለማው ጊዜያችን የነበረውን ክርስቶስ ግን እንዳንተው! አደራ እርሱን ብቻ እንዳናጣ ሌላው ትርፍ ነው!»