HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 271
مشترکین
-424 ساعت
+127 روز
+2630 روز
آرشیو پست ها
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»
(የማቴዎስ ወንጌል 19፡16-30)
«እነሆም፥ አንድ ሰው ቀርቦ። መምህር ሆይ፥ የዘላለምን ሕይወት እንዳገኝ ምን መልካም ነገር ላድርግ? አለው። እርሱም። ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ አለው። እርሱም። የትኞችን? አለው። ኢየሱስም። አትግደል፥ አታመንዝር፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አባትህንና እናትህን አክብር፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው። ጐበዙም። ይህንማ ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ፥ ደግሞስ የሚጐድለኝ ምንድር ነው? አለው። ኢየሱስም። ፍጹም ልትሆን ብትወድ፥ ሂድና ያለህን ሸጠህ ለድሆች ስጥ፥ መዝገብም በሰማያት ታገኛለህ፥ መጥተህም ተከተለኝ አለው። ጐበዙም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ብዙ ንብረት ነበረውና እያዘነ ሄደ። ኢየሱስም ለደቀ መዛሙርቱ። እውነት እላችኋለሁ፥ ለባለጠጋ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት ጭንቅ ነው። ዳግመኛም እላችኋለሁ፥ ባለጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል አለ። ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው እጅግ ተገረሙና። እንኪያስ ማን ሊድን ይችላል? አሉ። ኢየሱስም እነርሱን ተመልክቶ። ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል አላቸው። በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ። እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን? አለው። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተስ የተከተላችሁኝ፥ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ፥ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ። ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። ነገር ግን ብዙዎቹ ፊተኞች ኋለኞች፥ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
3ቱ የቡዳ ዛር ዓይነቶችና ያልተረዳነው የጥቃት ስልታቸውና አያያዛቸው! ውስጣችንና ውጪያዊ እኛነታችንን የሚያጠቁ ክፉ መናፍስቶች! በንግግራችሁ ሰዎችን እያስቀየማችሁ ከተቸገራችሁ አዳምጡ! https://youtu.be/ufS5X7jqzeU?si=pSdU3EQtli7ZBEte
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ
(የማቴዎስ ወንጌል 20፡19-31)
«ያም ቀን እርሱም ከሳምንቱ ፊተኛው በመሸ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ተሰብስበው በነበሩበት፥ አይሁድን ስለ ፈሩ ደጆቹ ተዘግተው ሳሉ፥ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው። ይህንም ብሎ እጆቹንም ጎኑንም አሳያቸው። ደቀ መዛሙርቱም ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው። ኢየሱስም ዳግመኛ። ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ አብ እንደ ላከኝ እኔ ደግሞ እልካችኋለሁ አላቸው። ይህንም ብሎ እፍ አለባቸውና። መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ። ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው። ነገር ግን ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ ከእነርሱ ጋር አልነበረም። ሌሎቹም ደቀ መዛሙርቱ። ጌታን አይተነዋል አሉት። እርሱ ግን። የችንካሩን ምልክት በእጆቹ ካላየሁ ጣቴንም በችንካሩ ምልክት ካላገባሁ እጄንም በጎኑ ካላገባሁ አላምንም አላቸው። ከስምንት ቀን በኋላም ደቀ መዛሙርቱ ደግመው በውስጥ ነበሩ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበረ። ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ፤ በመካከላቸውም ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው። ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው። ቶማስም። ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት። ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው። ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤ ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ከልጆቻችን ጋር ቆርበን ስንመለስ ይኼ ተዓምር በጎረቤቶቻችን ተከሰተ!! እኛም የሰው ቃርሚያና በጎነት የራቀን ከሆንን ቆይተናል!! #hailegebriel #ጸሎት https://youtu.be/0wxpUnVXEyk
«ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፤ በቅድስት እናትህና በቅዱሳንህ ሁሉ ምልጃ ከቅናት፣ ከዓይነ ጥላና ከአጋንንት ኃይላት ሁሉ ታደገኝ። በመላእክትህ ክበበኝ፤ በመስቀልህ ጠብቀኝ፤ ነፍሴንም በክቡር ደምህ አንጻት። አሜን።»
"ዓይነ ጥላ የቅናትና የትዕቢት ዓይን ነው። የሚያቆስል እይታ ነው።" አቡነ ጴጥሮስ፣ ኢትዮጵያዊው ሰማዕት ጳጳስ
«ኃጢአት እየተለመደ ሲመጣ፣ ነፍስ ለውጥን ትቃወማለች። ፈቃድ በመንፈሳዊ ተግሣጽ ካልተሠለጠነ ይደክማል። ሰይጣን የኃጢአትን ጥፍጥና ያጋንናል፤ መርዙን ግን ይደብቃል። ከኃጢአት በኋላ የሚመጣው ኀፍረትና የጥፋተኝነት ስሜት፣ ከመዳን እጅግ እንደራቅን እንድናምን ያደርገናል። ስለዚህ በዚሁ አዙሪት ውስጥ እንቀጥላለን።»
"ሥጋ መጥፎ ጌታ ነው፤ ሲታዘዙት ግን እጅግ ጨካኝ ነው።" ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
«መንፈሳዊው አርአያነት ትኩረት ያልተሰጠው እንዲሆን፤ በክርስቶስ ርሕራሔና ቸርነት በይቅርታ በጸና፤ በፍቅር የጋራ ልብስ፣ በሃይማኖት ጥንካሬ፣ በዕውቀት የወንጌል ቃል ይዞታ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል እንዳይገለጥ፤ በውስጡ የተደበቀ አጀንዳ ካለው ዲያብሎስ ጋር የሚቀራረብ፤ ቀደም ብሎ በመንፈሳዊውም ሆነ በዓለማዊውም መንገድ፤ ለክፋትና ለጥፋት ከሴራ ጋር ተቀናጅቶ የሚሄድ ወገንና አገልጋይ፤ ጥቂት አይደለም፡፡ የቅድስና አርዓያነት አለመኖር፣ የእምነት ማጣት ችግር፣ የመንፈሳዊ ጸጋ፣ በረከትና ክብር መራቅ፣ የታሪክ ጥላቻና የንቀት ተግባር፣ በአገልጋዮች ዘንድ ቦታ ከያዘ፤ የቤተሰብ መፍረስና የወላጆች መዋረድ፣ የዜጎች መኮብለልና ስደት፣ የሰው ልጆች ሥቃይ፣ እንግልትና ሞት ካላስደነገጠን፤ አገልጋዮች፤ በክርስቲያኑ ወገናችን ፊት መቆማችን፤ ትርጉም አልባ ይሆናል፡፡
ተደናግሮ ማደናገር የዘመናችን ሙያዊ ዘዴ፣ እንጀራ፣ ደሞዝና ኑሮ ሆኖ፤ የውድቀት ማቆያና የብልጣብልጥ የአቋራጭ መንገድ፤ ዕውቀትና ማዕረግ ሆኖዋል፡፡
በአፍላ ትጀምራላችሁ በወረት ትተውታላችሁ። ያወቃችሁትን ትረሳላችሁ፤ ያላወቃችሁትን ለማወቅ ትጥራላችሁ፤ የያዛችሁትን ትረግጣላችሁ፣ የረገጣችሁትን ትይዛላችሁ። ምኞታቸሁ ልክ የለውም፤ አምሮታችሁ ብዙ ነው። የአማራችሁን ስታገኙ ወዲያው ይሰላቻችኋል። ተው የተባላችሁትን ትሽራላችሁ፤ የተከልከላችሁትን ትደፍራላችሁ፤ የተፈቀደላችሁን ችላ ትሉታላችሁ። ሁሉን ማወቅ ትፈልጋላችሁ፤ በአንዱም ግን አትጠቀሙበትም። ሁሉ አላችሁ፤ ግን ባዷችሁን ናችሁ። ሃይማኖት እንጅ እምነት የላችሁም!»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»
(የሉቃስ ወንጌል 1፡57-80)
«የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች። ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ። እናቱ ግን መልሳ። አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ አለች። እነርሱም። ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም አሉአት። አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት። ብራናም ለምኖ። ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ። ለጎረቤቶቻቸውም ሁሉ ፍርሃት ሆነ፤ ይህም ሁሉ ነገር በይሁዳ በተራራማው አገር ሁሉ ተወራ፤ የሰሙትም ሁሉ። እንኪያ ይህ ሕፃን ምን ይሆን? እያሉ በልባቸው አኖሩት፤ የጌታ እጅ ከእርሱ ጋር ነበረችና። አባቱ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ ሞላበትና ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ። የእስራኤል ጌታ አምላክ ይባረክ፥ ጐብኝቶ ለሕዝቡ ቤዛ አድርጎአልና፤ ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤ ማዳኑም ከወደረኞቻችንና ከሚጠሉን ሁሉ እጅ ነው፤ እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ፤ በእርሱም ከጠላቶቻችን እጅ ድነን በዘመናችን ሁሉ ያለ ፍርሃት በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ እንድናገለግለው ሰጠን። ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤ እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል። ሕፃኑም አደገ በመንፈስም ጠነከረ፥ ለእስራኤልም እስከ ታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የሰው ጠላቱ ቤተሰቡ ይሆናል የምለው ቃል ተፈጸመብን!! አጋንንትን ማውጣትና መሸኘት በስሙ ለሚያምኑ ሁሉ ይቻላል!! 4ቱ የመነኮሳት አባቶች የመናፍስት ፈተና!! https://youtu.be/JQz86-E8lAY
+ ርእሰ : ጻድቃን : #ዮሐንስ : መወለዱ : እንደምን : ደስ : አያሰኝ! +
+ በዮሐንስ መወለድ ነቢያት ደስ ይላቸዋል እርሱ ከተወለደ ጌታ መወለዱ ነውና። መላእክትም ደስ ይላቸዋል። ዮሐንስ ከተወለደ ጌታ ተወልዶ ሊያዩት ነውና፤ ወዲህም በንጽሕናው ሊመስላቸው ተወለደ። መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እርሱ ከሌሎች ነቢያት በተለየ ጌታውን ዳስሶ ያጠምቀው ዘንድ በፊቱ ይሔድ ዘንድ ይመሰክርም ዘንድ፥ መንገድ ይጠርግ ዘንድ ተወለደ።
+ ዮሐንስን የልዑል አምላክን መምጣት ይሰብክ ዘንድ፥ ጥምቀትን ለንሥሐ ለኃጢአት ይቅርታ ያስተምር ዘንድ ተወለደ፡፡ እነሆ ጌታችን መድኀኒታችን በማያልቅ ነገር በማይደክም ልሳን ይመጣል እያለ ያስተምር ዘንድ ተወለደ::
+ ነቢያት ብርሃን ጽድቁን እግዚአብሔር እንዲልክላቸው እየተማጸኑ አልፈዋል ነገር ግን ይህን ብርሃን በአካል ተገኝተው እንዳያዩ የዘመን መጋረጃ ጋረዳቸው ዮሐንስ ግን የዚህን ብርሃን የንጋት ኮከብ ሆኖ መንገድ ሊጠርግ ተወለደ። ሌሎቹ የመሥዋዕቱ በግ ወዴት ነው እያሉ እየቃተቱ አልፈዋል ዮሐንስ ግን የዓለሙን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ እነሆ ብሎ የሁላቸውን ጥያቄ ሊመልስ ለዓለሙ ሁሉ የሕይወት ምግቡን ያሳይ ዘንድ የሕይወት መምህር ሊሆን ተወለደ፡፡
+ ከአዳም እስከ ሙሴ ያሉት ሁሉ የመርገሙን ሸክም እንደ ተሸከሙ አልፈዋል ዮሐንስ ግን እርሱ እያጠመቀ ጌታ በእግሩ ተረግጦ የዕዳ ደብዳቤያችንን ሲደመስሰው የነበረ የተመለከተ የዚህ ምስጢር ተሳታፊ ሊሆን ተወለደ። ያዕቆብ ድንግልን በመሰላል ልጇን በንጉሥ ኃምሳል አየ ዮሐንስ ግን በእናቱ ቤት ንጉሡን በማኅፀኗ ተሸክማ መጣችለት ከማኅፀን ቃሏን ሰምቶ ዘለለ፡፡ እርስዋን ሰምቶ አደገ ጣዕሟንም ጠገባት ንጉሡንም ሊያጠምቀው #ተወለደ
+ ያዕቆብ ንጉሡን ከመሰላሉ ጫፍ ላይ አየው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ግን ንጉሡን ከእጆቹ በታች ሊያተጠመቀ ተወለደ፡፡ ሙሴ እግዚአብሔርን በደመና ውስጥ ሰማው፡፡ በዚያም ውስጥ ሰባቱ መጋረጃ፣ ጉም፣ መብረቅ፣ ንውጽውጽታ፣ ድልቅልቅ ነበር፡፡ እስራኤልም ከዚህ የተነሣ ደንግጠው እንደ ሻሽ ተነጥፈው እንደ ቅጠል ረገፉ፡፡ ዮሐንስ ግን ያንን የሚያስፈራ እሳት በእጆቹ ሊዳስሰው፤ በውኃም ሊያጠምቀው ተወለደ።
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ አንተ ለአባትህ ያደረግከውን አድርግልኝ እንጂ፤ አንተ የተዘጉ ነገሮቼን ሁሉ ክፈትልኝ እንጂ ስምህን ደግሜ ደግሜ እጽፈዋለሁ፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የዝሙት መንፈስ ውስጣችን ሆኖ ስልቱንና ጥቃቱን እንዴት ይቀይራል? 4ቱ የመነኮሳትና የገዳማዊያን አባቶቻችን ከባዱ የመናፍስት ፈተና!
4ቱ ልቦችና የዲያብሎስ ፍሬ እንዳናፈራ የሚዘረጋው ወጥመድ! ልባችን በዲያብሎስ ቁጥጥር ስር የመሆኑ ምልክቶች! https://youtu.be/xLVDpqRQNow?si=Do7gPNCUeHiKXaeY
ሰይጣን መንፈሳዊ ጋብቻን እንዴት ያፈርሳል? መንፈሳዊ ጋብቻን ለመጠበቅ የሚረዱ ምክሮች! ኦርቶዶክሳዊ ጋብቻና የዲያብሎስ ፈተና! https://youtu.be/bI18GOVSK9o?si=LnZz1oB0gHWGHVrw
ጸሎት በምትጸልዩበት ጊዜ ይኼንን ማድረጋችሁን በደንብ አስተውሉ! በንስሐ እንዳንመለስ የዲያብሎስ ማባበያ መንገዶች! በትዳር ውስጥ መኖር የሌለባቸው 4 ነገሮች! https://youtu.be/htmc9MqwONg
» በአምልኮት መንፈስና ጸጋ ያልተዋጁ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዓይኖች፤ ከደመና በላይ ያለ ሐቅንና ከአርያም የሚወርድ በረከትን ከማየት ታወሩ፣ መለኮታዊ ጸጋን እያዩ እንደማያዩ ሆኑ፣ ሰላምና መረጋጋት እንዲናፍቃቸው ተገደዱ፣ ሌላውን በክፉና በጠበኝነት መንፈስ ተሞልተው ተመለከቱ፣ የጸሎት መጽሐፍትንና ቅዱስ ነገራትን ለማየት ቀፈፋቸው፣ በዳንኪራና በዝሙት የተለወሰ መዝናኛን በየቀኑ አሳደዱ፡፡ "ምንዝር የሞላባቸው ኃጢአትንም የማይተዉ ዓይኖች አሉአቸው፤ የማይጸኑትን ነፍሳት ያታልላሉ፤ መመኘትን የለመደ ልብ አላቸው፤ የተረገሙ ናቸው።" (2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፥14)
» በአምልኮተ እግዚአብሔር ክብር ያልተባረኩት የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጆሮዎች፤ ቃለ ወንጌልን እንደ ስድብ ሁሉ ተጸየፉ፣ የፍቅርና የርኅሩነት ድምፆችን መስማት አብዝተው ጠሉ፤ የችግርና የሰቆቃ ሰበር ዜናዎችን በየወራቱ ለማድመጥ ተገደዱ፤ ክፉ ሐሜትን ሰምቶ ለማሰማት በፍጥነት ተጋበዙ፤ ዘወትር ሳቅና ምቾት ብቻ ለማግኘት ሲሉ የሕይወት ቁምነገርን ሸሹ፤ ሙዚቃን ማዳመጥ "ነፍሴ ነው፣ ውስጤ ነው፣ ማንነቴ ነው" በማለት ራሳቸውን የዙፋን ቅርጽ ለቀየረ የጣዖት ኃይል አሳልፈው ሰጡ፡፡
"ጆሮአቸው ያልተገረዘች ናት ለመስማትም አይችሉም፤ እነሆ፥ የእግዚአብሔር ቃል ለስድብ ሆኖባቸዋል፥ ደስም አያሰኛቸውም።" (ትንቢተ ኤር 6፥10)
» በዚህ በማይሰግደውና በማይጸልየው በኛ ዘመንና ትውልድ ደግሞ፤ የመናፍስት አጥፊ ስውር እጅ በእጅጉ ረዝሞ፤ ከቤተ-እግዚአብሔር ቅጥር አልፎ ሳይቀር እየገባ ክርስትናችንን ገለባ አደረገው፡፡ በዚህ ስለዚህ የነበረንን፣ ያለንንና የሚኖረንን ሁሉ አራግፈን በአንዴ ጥለን፤ "ራሳችንን የምንወድ፥ ገንዘብን የምንወድ፥ ትምክህተኞች፥ ትዕቢተኞች፥ ተሳዳቢዎች፥ የማንታዘዝ፥ የማናመሰግን፥ ቅድስና የሌለን፥ ፍቅር የሌለን፥ ዕርቅን የማንሰማ፥ ሐሜተኞች፥ ራሳችንን የማንገዛ፥ ጨካኞች፥ መልካም የሆነውን የማንወድ፥ ከዳተኞች፥ ችኩሎች፥ በትዕቢት የተነፋን፥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የምንወድ ሆነን" ቁጭ ብለናል (ይህም ሲሆን፥ እንደ ኖኅ ጎረቤቶች ቅንጣት አያስጨንቀንም)፡፡ (2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3፥2-4)
» የእያንዳንዳችን የግል ኑሮ የባቢሎንን ግንብ የቋንቋ ድብልቅልቅ ገጽታ ወርሶ፤ እናት ከልጅ፣ ቤተሰብ ከአዝማድ፣ ጓደኛ ከወዳጁ፣ ወገን ከዜጋው ጋር በአንድ ቃል እየተነጋገረም መግባባት አቅቶት፤ በቂም በተበረዘና በቁጣ በተለወጠ ድምፅ እየተቀጣቀጥን፤ በተለዋወጥነውም ኃይለ ቃል እልህ እየቋጠርን፤ በከፉ መናፍስቶች የከፋው ስብእናችን ከፍቶ ከፍቶ የክፋት ጣራን ጫፍ ሲነካ "ለምን እገሌ ምንም የለውም?" ብለን ምንም ባጣ ሰው ላይ እንኳን እየቀናን፤ እርስ በእርስ በጥላቻና በምቀኝነት ሰንሰለት ተሳስረን ተሳስረን፤ ምኑ ጋር ተጀምሮ ምኑን ማስተካከል እንደሚቻል እጅግ ግራ እስኪያጋባ ድረስ ሕልውናችን ውስብስብ ፈተና ውስጥ መግባቱን ስንመለከት፤ የማጥፋት ጥንተ ግብሩን በተቀናጀ ስልትና የጨለማ ጥበብ በዝምታ የሚፈጽመው የዲያለቢሎስ ሠራዊት ከሕብረተሰባችን በስተኋላ ድብቅ ሕብረተሰብ ሆኖ ተዳብሎ እንዳደፈጠ ፈጽሞ አያወላዳም፡፡
"ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥ በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 3፥11-12)
እኛም የኃያሉ አምላካችን የእግዚአብሔር ጥበቃና ምሕረት አብሮን እስካለ ድረስ፤ እንደተያዝን አንቀርም፡፡ ከታሰርንበት እንፈታለን፤ ከወደቅንበትም እንነሣለን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ከ መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
«ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ፣ ልቤን በመገኘትህ ሙላው። ባዶ አድርገህ አትተወኝ፤ ይልቅስ በመንፈስህ በውስጤ ኑር። ክፉና ርኩስ መንፈስን ሁሉ ከእኔ አርቅልኝ፤ ለዘላለም ያንተ ሆኜ እንድኖር በጸጋህ አትመኝ። አሜን።»
«አባቶቻችን ስለ አስትሮሎጂና ኮከብ ቆጠራ የነገሩን!»
» ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፦ ከዋክብት አልፈጠሩንም፣ ድርጊቶቻችንንም አይመሩም… ይህን ማለት እግዚአብሔርን ፍትሕ አያደርግም ብሎ እንደ መክሰስ ነው፤ ምክንያቱም እርሱ የሚሸልመን ወይም የሚቀጣን እንደ ሆሮስኮፓችን (የኮከብ ትንበያችን) ሳይሆን እንደ ሥራችን ነው። የቀደመችው ቤተክርስቲያን ቀኖና (የሐዋርያት ሥርዐት) ክርስቲያኖች በኮከብ ቆጠራ እንዳይጠመዱ ወይም ኮከብ ቆጣሪዎችን እንዳያማክሩ ይከለክላል።
» ቅዱስ አውግስጢኖስ ዘሂፖ (354–430 ዓ.ም.) ወደ ክርስትና ከመመለሱ በፊት አብዛኛውን የወጣትነት ዘመኑን በኮከብ ቆጠራ አሳልፏል። ኮከብ ቆጣሪዎችን አማክር ነበር፤ አንተ እውነተኛው አምላክ ግን እነዚህ ነገሮች ሐሰት መሆናቸውን አሳየኸኝ። በኮከብ ቆጠራ ማመን ማለት በፈጣሪው ፈንታ በተፈጠሩ ነገሮች ላይ እምነትን መጣል ነው። ያደረገው ነገር በይፋ ንስሐ ገብቷል፣ (በሐዋርያት ሥራ 19:19 እንደተገለጸው) ሌሎችም የኮከብ ቆጠራ መጻሕፍትን እንዲያቃጥሉ አበረታትቷል፣ አጋንንት አእምሮን በባርነት ለመግዛት ኮከብ ቆጠራን እንደሚጠቀሙ አስጠንቅቋል።
» ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት (ዘእንዚናዙ) ኮከብ ቆጠራን በእጣ ፈንታዊ አስተሳሰቡ ምክንያት ነቅፎታል፦ ከዋክብት ሊያበሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን አይገዙንም። ነጻነታችንን ለሰማይ ተረቶች አሳልፈን አንስጥ። ትምህርቱ፦ በዞዲያክ (በከዋክብት) እጣ ፈንታ ማመን የሰውን ነጻ ፈቃድና በውስጡ ያለውን የእግዚአብሔርን መልክ ይክዳል። ክርስቲያኖች የተጠሩት ለመንፈሳዊ ነጻነት እንጂ፣ ለኮከብ ባርነት አይደለም።
» ኢሳይያስ 47:13-14 ኮከብ ቆጣሪዎችህ፣ ትንቢት የሚናገሩት ከዋክብት ተመልካቾችህ... ይቅረቡ። እነሆ እነርሱ እንደ ገለባ ናቸው፤ እሳትም ያቃጥላቸዋል።
» ዘዳግም 18:10-12 በመካከላችሁ... ምዋርተኛ ወይም ምልክቶችን ተርጓሚ... ማንም አይገኝ። እነዚህን ነገሮች የሚያደርግ ማንኛውም ሰው በጌታ ዘንድ አስጸያፊ ነው።
» የሐዋርያት ሥራ 19:19 አዲስ ያመኑት ሰዎች የአስማትና የኮከብ ቆጠራ መጻሕፍቶቻቸውን በይፋ አቃጠሉ — ይህም በክርስቶስ ማመን ማንኛውንም ድብቅ የጥንቆላ ሥራ መተው እንደሚያስፈልግ ያሳያል።
ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ፦ የከዋክብትን አካሄድ መመልከትና የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ችላ ማለት ምክንያታዊ ያልሆነች ነፍስ ምልክት ነው።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»
(የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 16፡19-31)
«ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር። አልዓዛርም የሚባል አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥ ከባለ ጠጋውም ማዕድ ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው ቍስሎቹን ይልሱ ነበር። ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት፤ ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ። በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ። እርሱም እየጮኸ። አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ። አብርሃም ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደ ተቀበልህ አስብ አልዓዛርም እንዲሁ ክፉ፤ አሁን ግን እርሱ በዚህ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ። ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛና በእናንተ መካከል ታላቅ ገደል ተደርጎአል አለ። እርሱም። እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና፤ እነርሱ ደግሞ ወደዚህ ሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ይመስክርላቸው አለ። አብርሃም ግን። ሙሴና ነቢያት አሉአቸው፤ እነርሱን ይስሙ አለው። እርሱም። አይደለም፥ አብርሃም አባት ሆይ፥ ነገር ግን ከሙታን አንዱ ቢሄድላቸው ንስሐ ይገባሉ አለ። ሙሴንና ነቢያትንም የማይሰሙ ከሆነ፥ ከሙታንም እንኳ አንድ ቢነሣ አያምኑም አለው።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
