fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 373 مشترک است و جایگاه 5 571 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 195 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 373 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 05 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 30 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.08% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 418 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 397 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 373
مشترکین
-424 ساعت
-197 روز
+3030 روز
آرشیو پست ها
✣✤#ገዳመ_ጽጌ_ድንግል_፤ የአቡነ ጽጌ ድንግል ገዳም በ14ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተው በታላቁ አባት በአቡነ ጽጌ ድንግል ሲኾን፤ እኝህ ታላቅ አባት እጅግ ሰፊ ኾኖ የሚያምረውንና ዕጹብ ድንቅ የሚያሰኘውን ባለሦስት ክፍል (ቅኔ ማሕሌት፣ ቅድስትና መቅደስ) ያለውን የገዳመ ጽጌን ውቅር ዋሻ ቤተክርስቲያን ያነጹ፣ ከሰባቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ (አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል፥ አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፥ አቡነ ያዕቆብ ዘቀዳሚት ግሸን ደብረ ከርቤ፥ አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት፥ አቡነ ዘካርያስ ዘወለቃ፥ አቡነ ዮሴፍ ዘወለቃ፥ የዝቋላው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘምስካበ ቅዱሳን ገዘዛ) አንዱ የኾኑና የወርቃማ ዘመን ወርቃማ ደራሲ የኾኑ በዚህም በቤተክርስቲያናችን ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ የምንጸልይበትንና የምናመሰግንበትን ማሕሌተ ጽጌን ባለ ፭ት አርኬና እንደ መዝሙረ ዳዊት በ፻፶ መዝሙር ልክ አድርገው የደረሱና ጸሐፊያቸው በኾኑ ጓደኛቸው አቡነ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ አጽፈው ለትውልድ ያስተላለፉ፤ እንዲሁም ሰቈቃወ ድንግልን ከጓደኛቸው አቡነ ገብረ ኢየሱስ ዘገዳመ መጕና ጋር አብረው የደረሱ ቅዱስ አባት ናቸው፤ እንዲሁም በዘመናቸው ከነበሩት ከጓደኛቸው ከታላቁ አባት አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ጋር ብዙ ገቢረ ተዓምራትን የሠሩ (የወለቃ ወንዝ ድልድይን ጨምሮ ያነጹ)፥ አሁንም ብዙ ገቢረ ተዓምራትን የሚሠሩ አባት ናቸው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ በወግዲ ወረዳ ልዩ ስሙ ደብረ (ገዳመ) ጽጌ ጫቀታ በሚባል ቦታ፤ ለዐባይ ወንዝ ገባሮች ከኾኑትና በበረሀ ውስጥ ከሚጓዙት አንዱ በኾነው በወለቃ ወንዝ አቅራቢያ ነው፡፡ ገዳሙ ለታላቁ አባት በተሰጠው ቃል ኪዳን መሠረትም አኹንም ድረስ ፈውሰ ሥጋ፥ ፈውሰ ነፍስ እየሰጠ ይገኛል፤ የገዳሙ ፍየሎችና ከብቶችም በአካባቢው ከሚገኙት ነብሮች ጋር አብረው ያለምንም አደጋ ይኖራሉ፡፡ ገዳሙ በግራኝ መሐመድ ወረራ ወቅት 500 መነኰሳት በሰማዕትነት የተሰየፉበት ሲኾን ከዚህ ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ተዘግቶ ቆይቶ በልዑል ራስ ካሣ ኀይሉ አማካይነት ተከፍቶ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፤ በድጋሚ በጣሊያን ወረራ ወቅት አደጋ ደርሶበታል፤ በደርግ ዘመንም የገዳሙ 84 ጋሻ መሬት ስለተወሰደበት እንደገና እስከ ከ1995ዓ.ም. ገዳሙ ዘግቷል፤ ነገር ግን በ1995ዓ.ም. በበጎ አድራጊ ምዕመናን ድጋሚ ሊከፈት ችሏል፡፡ ማሕሌተ ጽጌ የተደረሰበት ይህ ገዳም እስከ 2008ዓ.ም. ማሕሌቱ ሳይቆምበት ቆይቶ ከ2009 ዓ.ም. ጀምሮ ማሕሌቱ እየተቆመ ይገኛል፡፡ ለበርካታ ዓመታት የሊቁ የአባ ጽጌ ድንግል በዓለ ዕረፍት መስከረም 27 መከበር አቁሞም ነበር፤ እንደ አምላከ አበው ፈቃድ ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ ክብረ በዓሉ በገዳም ሥርዐት እየተከበረ ይገኛል፡፡ ወደ ገዳሙ ለመሄድ ለሚፈለጉ ምዕመናን፤ (በተለይ ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ የተጓዛችሁ በዛው ለመሄድ ቅርብ ነው፡፡) 1ኛ) ከደሴ ከተማ ለምትነሱ ወግዲ በሚል መኪና ከተሳፈሩ በኋላ ከተወሰኑ የእግር ጕዞ በኋላ ይገኛል፤ 2ኛ) ከጎጃም በመካነ ሰላም ለምትነሱ ወግዲ በሚል መኪና ከተሳፈሩ በኋላ ከተወሰኑ የእግር ጕዞ በኋላ ይገኛል፤ 3ኛ) በመርሐ ቤቴ በሚዳ ለምትነሱ ወግዲ በሚል መኪና ከተሳፈሩ በኋላ ከተወሰኑ የእግር ጕዞ በኋላ ይገኛል፡፡ † በዚሁ አጋጣሚ የታለቁ ሊቅ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በዓለ ጽንሰታቸውም ጥቅምት 3 ስለሚከበር አብሮ ማክበር ይቻላል፡፡ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/ (የገዳሙን ኹኔታ የዘገበልንን ወንድማችንን አምላከ አባ ጽጌ ድንግል ወጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ይስጥልን፤ በረድኤት በበረከት ቅዱሳን ሊቃውንቱ ይጎብኙልን፡፡)

#_ቀን _ከሌት_ለምትደክሙ ለደብራችን አገልጋይ ካህናት #_ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ እስከዛሬ ድረስ #_በማኅሌቱ፣ #_በሰዓታቱ ፣ #_በቅዳሴው፣ #_በሰርክ_ጉባኤው በተለይ ደግሞ ታላላቅ ገዳማት በሚደርሰው ምህላ ሁልጊዜ ወር ከገባ ከ1-7 ባሉት ጊዜዎች #_ለሀገራችን ለቤተክርስቲያናችን ሳትሰለቹ የምትጸልዩ ፣ #_ደብራችንን ታላቅ እንዲሆን ያደረጋችሁ የምታደርጉ አብነት ት/ት ዘወትር ለተተኪዎች የምታስተምሩ አባቶቻችን ስለእናንተ ተናግረን አውርተን አንጠግብም፡፡ ይህ ሁሉ አገልግሎታችሁን ሳታቋርጡ ደግሞ ደብራችን #_ሰላም እንዲሆን፣ #_ቤተክርስቲያን ከግለሰቦች አያያዝ ተላቃ የምዕመናን እንድትሆን ፣ #_ሰላም የምትሰብክ ቤተክርስቲያን ሰላሟ እንዲበዛላት፣ #_ምዕመናን የሚሰጡት አስራት በኩራት ለሰጡበት አላማ ብቻ እንዲውል ጠንክራችሁ የምትሰሩ ፣ #_እውነትን ሳትሰለቹ የምትሰብኩ ለእናንተ ለሊቃውንት አባቶቻችን እጅ እንነሳለን፡፡ ይህ ልፋታችሁ በእኛ በልጆቻቸሁ ዘንድ #_ትልቅ _ዋጋ አለው፡፡ ትልቅ ትምህርት አስተምራችሁናል፡፡ ለእውነት በመቆማችሁ ስትገፉ አይናችን እያየ ዝም አንልም፡፡ #_የአካባቢው ጠንካራ ወጣቶች ማኅበራት (አይደለም ለዚህ ታላቅ ደብር ለሀገር የሚተርፉ) #_የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ዛሬም እንደትላንቱ አብረናችሁ ነን፡፡ በኑሯችሁ ሲመጡ፣ በህይወታችሁ ሲመጡ ፣ ካደጋችሁበት ደብር ሊያፈናቅሏችሁ ሲጥሩ፣ ታላቁን ደብር ሊያሳንሱ ሲጥሩ አይቶ እንዳላየ ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ መሆን #_አንችልም፡፡ ያን ጊዜ ትላንት እውነትን በመመስከራቸው፣ የእውነት ጥያቄ በመጠየቃቸው ባሳዩት ቁርጠኝነት ተነስተው ለነበሩት #_ለ_3ቱ_አባቶች እንደቆምነው ዛሬም ለሁላችሁም ዘብ እንቆማለን፡፡ ምንም እንኳን በመካከላችን ገብተው የሰ/ት/ቤቱን አባላት እና ካህናት አባቶችን ለማጣላት የሚፈልጉ ጥቂት ግለሰቦች ቢኖሩም እኛ ግን ትላንት መጥተው ነገ ለሚሄዱ ሰዎች ክፍተት አንፈጥርም በማለት በመነጋገር እዚህ ደርሰናል፡፡ ዛሬም ለዚህ ሳንበገር #_በፍቅር #_በአንድነት አገልግሎታችንን እናገለግላለን፡፡ ስለሆነም አሁንም ቢሆን #_አስተዳደራዊ በደል እየደረሰባችሁ ግን ልጆቻችሁንና ቤተሰባችሁን ህይወታችሁን ላለመበተን ስትሉ መናገር እየቻላችሁ መናገር ያልቻላችሁ #_አባቶችም #_ዲያቆናትም እናንተም እየቀረባችሁ የሚገጥማችሁን ፈተና እየተወያየን ከፊታችሁ ቆመን የምንጮህላችሁ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ #_ከፊት ተሰልፈን እውነታችሁን እንደግፋለን፡፡ ዛሬም አብረናችሁ ነን፡፡ #_ክብር_ለሚገባው_ክብርን_እንሰጣለን!!! share ያድርጉ ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እንኳን ለዘመነ ጽጌ (ከመስከረም ፳፮ - ኅዳር ፭) እና ለጽጌ ጾም በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፣ ተሠርገወት ምድር በሥነ ጽጌያት፡፡ ትርጕም፤ የክረምት ዘመን (ከሰኔ 26 - መስከረም 25) አለፈ፥ ሄደ /መኃ.2 11/፡፡ የጽጌ ዘመን (ከመስከረም 26 - ኅዳር 5) ተተካ፡፡ Like እና Share ያድርጉ #ማኅሌተ_ጽጌ #ማኅሌተ ጽጌ ከሁለት የግዕዝ ቃላት ጥምረት የተገኘ ነው፡፡ ማኅሌት ማለት ምስጋና፣ ማወደስ ማለት ሲኾን፤ ጽጌ ማለት ደግሞ አበባ፣ የፍሬ ምልክት፤ ውበት፣ ደም ግባት ያለው ማለት ነው፡፡ ማኅሌተ ጽጌ ተብሎ በአንድነት ሲነገር እና ሲተረጎም ደግሞ የአበባ ምስጋና ማለት ነው፡፡ ይህም ድንግል ማርያም እና የማሕፀኗ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየተመሰሉ በዳዊት መዝሙር መጠን በ150 እንዲሁም እንደ መልክዕ በባለ 5ት መስመር ግጥም ተደርጎ የሚመሰገኑበት ምስጋና ማለት ነው፡፡ ጽጌ የዘመን (የወራት) ስምም ይኾናል፤ ዘመነ (ወርኃ) ጽጌ 40 ቀን ነው ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ነው፡፡ በዚህ ወራት የሚጾመው ጾም ጾመ ጽጌ ሲባል ጾሙም የፈቃድ ጾም ነው፡፡ በሀገራችን ዘመነ ክረምት አልፎ መስከረም 26 ቀን ዘመነ ጽጌ ይጀመራል፡፡ ዘመኑ አበቦች የሚያብቡበት እና ሜዳዎችን እና ተራሮችን የሚስጌጡበት ዘመን ነው፡፡ ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ኹሉ በማኅሌተ ጽጌ እመቤታችንን በአበባ፥ ጌታችን በፍሬ፤ ወይም እመቤታችንን በፍሬ፥ ጌታችንን በአበባ እየተመሰሉ በምሥጢራዊ ግጥም ቀርበዋል፡፡ የማኅሌተ ጽጌ ደራሲ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግልም የአበቦችን ነገር ከእመቤታችን ስደት ጋር እያደረገ፣ እጅግ አስደናቂ የሆኑ ታሪኮችን እያጣቀሰ ማኅሌተ ጽጌ (የአበባ ማኅሌት) የተባለውን ጸሎት ደርሷል፡፡ በዘመነ ጽጌ ወቅት ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ማኅሌት ይቆማል፤ የሚቆመው ቁመትም አባ ጽጌ ድንግል የደረሱት ማኅሌተ ጽጌና ሰቈቃወ ድንግል ነው፡፡ አባ ጽጌ ድንግል ጓደኛቸው አባ ገብረማርያም የጀመሩትን ማኅሌተ ጽጌ አብነት በማድረግ በተለይም በጎንደር ዘመነ መንግሥት በእቴጌ ምንትዋብ ዘመን በጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቊም ማርያም የማኅሌተ ጽጌ ቁመት መቆም ተጀምሯል፤ ቆይቶ ግን ይህ ማኅሌት ወደ ዘንሥር ዮሐንስ ማእከላ ለጎንደር ተዛውሮ እስከ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ድረስ ሲቆም ቆይቶ በመምህር ተክሌ ጊዜ ወደ መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም ተዛውሮ በጎንደር አብያተ ክርስቲያናት በብቸኝነት በዚህችው ደብር የጎንደር አድባራት ሊቃውንት በመሰባሰብ ሲቆም ቆይቷል፤ በሌሎች የሃገራችን ክፍሎች አዲስ አበባን ጨምሮ ባሊ አብያተ ክርስቲያናትም የጽጌ ቁመት ተስፋፍቷል፡፡ ከ1999(2000)ዓ.ም. ጀምሮ በጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቋምና የተወሰኑ የጎንደር አብያተ ክርስቲያናት የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ጀምረዋል፤ ነገር ግን ቢጀምሩም ቅሉ አሁንም ግን የጎንደር አድባራት ሊቃውን በዋነኛነት በመካነ ነገሥት ግምጃቤት እየተሰባሰቡ የሚቆሙት የማኅሌተ ጽጌ ቁመት እጅግ በጣም ልብን የሚማርክና ኅሊናን የሚመስጥ በሃገራችን በኢትዮጵያ ደረጃም ተወዳዳሪ የሌለው ነው፡፡ በሌሎች የሃገራችን ክፍሎችና በመዲናችን በአዲስ አበባ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ የአገልጋይ ካህናት እጥረት በሌለባቸው ኹሉ ይቆማል፡፡ #ሰቈቃወ_ድንግል፤ ማለት እመቤታችን ከልጇ ከመድኀኔዓለም፥ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር በስደቷ ወቅት ያየችውን መከራ፥ ልቅሶ፥ ዋይታ የሚዘከርበት የማኅሌተ ጽጌ አርኬ ነው፡፡ ፎቶዎቹ፤ #ቤተ_ክርስቲያኖች_ *ደብረ ጽጌ ገዳም፤ የአባ ጽጌ ደንግል ገዳም፤ ማኅሌተ ጽጌ የተደረሰበት፤ ወሎ ወግዲ አጠገብ፤ ኅዳር 6 ይከብራል፡፡ *ጎንደር ደብረ ፀሐይ ማርያም፤ ለበርካታ ዘመናት ማኅሌተ ጽጌ ይቆምባት የነበረች ታላቋ ደብር፡፡ *ጎንደር ዘንሥር ዮሐንስ፤ እስከ አፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን የጎንደር የ44ቱ ታቦታት ሊቃውንት አየተሰበሰቡ ማኅሌተ ጽጌ ይቆሙበት የነበረ ደብር፡፡ *ጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም፤ ከአፄ ኃይለ ሥላሴ እስከ አሁን ድረስ የጎንደር የ44ቱ ታቦታት ሊቃውንት አየተሰበሰቡ ማኅሌተ ጽጌ የሚቆሙባት ታላቂቷ ደብር፡፡ #መምህራን_ ✤ #መምህር_ተክለማርያም_፤ የታለቁ ገዳም የማኅበረ ሥላሴ አበምኔት፤ የግምጃ ቤት ማርያም የሐዲሳት መምምህር፤ የድጓና የአቋቋምም መምህር፤ የጎንደር አድባራት በጋራ በመኾን የማኅሌተ ጽጌን ቁመት በአንድ ላይ ይቆሙበት ከነበረው ዘንሥር ማዕከላ ለጎንደር ዮሐንስ ወደ መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ያመጡ ታላቁና ይህ ቀረሽ የሚይባሉ ሊቅ ✤፠ #መምህር_ክፍለ_ማርያም_ይመር_፤ የመጻሕፍት ትርጓሜ ብርሃን፤ የየቀኑን ምሥጢር ከድጓ፣ ከጾመ ድጓ፣ ከዝማሬ መዋሥዕት፣ ከቅዳሴ፣ ከሰዐታት እየተመለከቱና እያውጣጡ ዚቁን ያዘጋጁ፤ ይህ ቀረሽ የማይባሉ የሊቆች ሊቅ፡፡ ✤፠ #ሊቀ_ማዕምራን_ወመጋቤ_ሐዲስ_ወሰንበት_ባይነሳኝ_፤ የጽጌ ዚቅን (የላይ ቤትን) አቀናብረው ያቀረቡ፤ የመጻሕፍተ ሐዲሳት ዋና ምስክርና የመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም ዋና አስተዳዳሪ፤ የሚያስተምሩት የሚኖሩ፤ ሊቅነትና ከትሕትና የያዙ፤ ከቀደምት ዐበይት ሊቃውንት መካታቻ የሆኑ፤ በቅርቡ ያረፉ፤ ጕባኤ እያሄዱ (እያስተማሩ) የሚያሳይ ፎቶ ✤፠ ሊቀ ማዕምራን ሐዋዝ ጥሩነህ፤ የግምጃ ቤት ማርያም አለቃ፤ ከላይ የተጠቀሱ ሊቃውንት የደረሱትን ዚቅ በእጅ ጽሑፍ ለትውልድ ያቆዩ ብልህ አስተዳዳሪ፡፡ ✤፠ #መምህር_ክፍሌ_ወለደ_ጻድቅ፤ የጽጌ ዚቅን (ዚቅን) (የታች ቤትን) አቀናብረው ያቀረቡ፤ የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ የአቋቋም ዋና ምስክር የነበሩ፡፡ የአሁንን ዝክረ ቃልን በቀድሞ ስሙ አባጃሌ የተባለውን መጽሐፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕትመት ያበቁ፡፡ ✤ #መምህር_ላዕከ_ጊዮርጊስ_ደምሴ፤ የግምጃ ቤት ማርያም የሐዲሳት ምክትል መምህር የነበሩና ዜማ አዋቂ ምሁር፤ በወርኃ ጽጌ የዕለቱን ምሥጢር በተመለከተ ዚቅ እያዘጋጁ ለሊቃውንቱ ያቀርቡ የነበሩ ✣✤✣ #መካነ_ነገሥት_ግምጃ_ቤት_ማርያም፤ ለሃገራችን ኢትዮጵያና ለኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ባለውለታ የኾነች ጥንታዊት ቤ.ክ.፤ በደርቡሽ ወረራ ጊዜ መመህራን ጕባኤያችንን (ማስተማራችንን የታሪክ መዘክርነታችንን) ለቅቀን አንሔድም በማለት ሰማዕት የኾኑባት፡፡ **የብዙ ሊቃውንተ መፍለቂያ፤ እስከ ዐፄ ኀይለሥላሴ ዘመን ድረስ (ከሠለስቱ ምዕትና ከልደታ አብያተ ክርስቲያናት ጕባኤ ቤት በመቀጠል) በሃገራችን ኢትዮጵያ ብቸኛዋ የታች ቤት የመጻሕፍት /አንድምታ ትርጓሜ/ (የ4ቱ ጕባኤያት) ብቸኛ ማስመስከሪያ፡፡ /በአሁኑ ሰዓት በዋነኛነት በኢትጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ ሐዲሳት የታች ቤት ትርጓሜ ዋና ማስመስከሪያ መካነ አእምሮ (university)/፡፡ እዲሁም የላይ ቤት የአቋቋም የዜማ የድርሰት ማዕከልና ዋና አብነት ነች፡፡ በውስጧ ተዓምረኛ የኾነች የእምቤታችን ሥዕል ይገኝባተል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2whttps:/ /t.me/medihanaelem በቅርቡ ደግሞ በ finotehiwotsundayschool.com Like እና Share ያድርጉ

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - آمار و تحلیل کانال تلگرام @finotehiwott