fa
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

رفتن به کانال در Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام የጥበብ ማዕድ

کانال የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 974 مشترک است و جایگاه 5 411 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 116 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 974 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 604 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -23 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 2.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.10% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 419 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 334 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 974
مشترکین
-2324 ساعت
+1447 روز
+60430 روز
آرشیو پست ها
እስቲ አንዳንድ ቦታ መልካምና ምስኪን ሁን ልባቸውን የምር ታገኘዋለህ።

ሰው የሚኖረው የሰው ልብ ውስጥ ነው፡፡

ሳሸንፍ  ሃሴት ኣላደርግም ላንተ ይከፋኛል ስሸነፍ እኔም ሰው ነኝና ለራሴው ያመኛል ኣንድ ነፍስ ተካፍለን  እንኖር ይመስል ድልና ሽንፈቱ ኣንድ ነው ስሜቱ meron

፡፡፥፥፡፡ ለካስ አይፈቀድም!! ፡፡፥፥፡፡
የዓለማችን ቆነጃጅቶች አለባበሳቸው እና ለየት ያለው ስርዓታቸው የራሳቸውን መድረክ አስደምሞ የእኛውንም ትኩረት ሰቅዞ መያዙን ቀጥሏል። ታዲያ ለምን ይሆን? ስንል ለካስ በዓለም የተፈጥሮ ህግ ይህ የክብር ማጋለጥ ወይም የብልግና ዓድማ አይፈቀድ ኖሯል። እንዴት ቢሉ ? ለስብሰባ ከተከማቸን በኋላ ሁሉም ሰው ወደ መድረኩ እንጂ እምብዛም እራሱ ላይ ትኩረት አያደርግም። የጎረቤቴ 20,000 ብር የሚገመት ስልኩ ሲወድቅ አየሁት እና ተጋፍቼ በማንሳት እሰጠዋለሁ። አመሰግናለሁ...ብቻ ብሎኝ የተረጋገጠውን ጫማየን እንኳን ሳያስተውል ወደ መድረኩ .... እኔም እያጉተመተምኩ ወደ ነበርኩበት ... ከልቤ አልወጣም ...ብስጭቴ .. ፊት ለፊቴ አንድ አዛውንት ኪስ ውስጥ ስዓት ነገር አያለሁ ...ሹ...ል...ክ,,,,ሳ...,ብ። መልኩ የሚስብ ሆኖ ሳይሆን መድረኩን ለመሳብ.... ነገር ግን ከኋላ ያየኝ ሰው ስለነበር ጮሆ አሲያዘኝ ...መድረክ ላይ ወጣሁ...ሰው በደንብ ይታያል..እኔንም ሁሉ አየኝ ...ደስ አለኝ ..እንደ ንጉስ መሆኔ። ለካስ የሌላ ሰው ስዓት መዉሰድ በህዝቡ እና በህጉ ዘንድ አይፈቀድ ኖሯል።  ለየዋህ እህቶቻችን!!!
 Tewodros D.

የምሬን እንደ መጓጓት መሰናክል የለም!

መዝገበ ቃላቱ "እና " የምትለዋን ቃል እንደ አያያዥ ፤ ብቻዋን የማትቆም ቁንፅል ይላታል ። በአጭር ምሳሌ" እና " እኔ ነኝ ። በሸረኞችና በደህነኞች መሃል ያለሁ ወይ አልሸርር ወይ አልደህንን " እና " እኔ ነኝ ። ምንም ታሪክ ምንም ትርጉም የለኝም ። ስራዬም ባህሪዬም በሆኑ ነገሮች መሃል መደበቅ ይበዛበታል " እና " ነኝ !! እና ምን ይጠበስ ። 📖 ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም

በጠዋቱ ስራ ለመግባት ነዳጅ ረግጨ በፍጥነት እየበረርኩ ነው ። ሁለት እናቶች መንገድ ላይ ቁመው እጃቸውን በይሉኝታ መንፈስ በስሱ አውለበለቡና ቆሙ ። እኔም ብዋከብም ልያዛቸው አልኩና አጠገባቸው ደርሸ ቆምኩኝ ። " ኑ ግቡ " አልኳቸው ገብተው ቁጭ አሉ ። ደና አደራቹ ? አልኳቸው ከፊት ለፊቴ ባለው መስታየት እያየኋቸው ። አንደኛዋ ፈጠን ብላ " እግዛብሔር ይመስገን " አለች " ወዴት እየሄዳቹ ነው " ? አልኳቸው " ለቅሶ ነው ልጄ " አሉኝ " የቆማችሁበት ቦታ'ኮ ታክሲ አይቆምም ሞልቶ ስለሚመጣ አይዟችሁም ። የተሳሳተ ቦታ ላይ ነበረ የጠበቃችሁ " አልኳቸው " አይይይ!! አይ ልጄ እኛ ምኑን አውቀን ብለህ ነው ከቤት ከወጣን ቆየን እንዲያውም የዚ ሃገር ምስጥ ሰንፎ ነው እንጂ በቆምንበት ይይዘን ነበረ " አለች አንድኛዋ " ሃ ሃ ሃ ምስጥማ እዚ ከተማ ምን ይሰራል እዚያው በለመደበት ገጠር ኩይሳ ይስራ'ጂ " አልኩ "አይይይ ! ልጄ አላወክም እንዴ" ? አለች አንድኛዋ ሰማይ ሰማይ እያየች ቆይታ "ምን" አልኩ "እዚ ከተማ ምስጥ መኖሩን " "አረ ! አላወኩም " " የገጠሩ ምስጥ የእርሻ መሬት ላይ አፈር ነፍቶ ኩይሳ ይሰራበትና መሬቱ እንዳይታረስ ተራራ ይሰራል ። የከተማው ግን ሰውና ሰው ነው ሚስጥ ። ትዕቢት የሚባል ምስጥ ውስጣችን ላይ ገብቶ ልባችንን ነፋፍቶ ተራራ ይሰራበታል ። ጎረቤት መጠየቅ የለ ሰው ሰላም ማለት የለ የሚያለቅሰውን ሰው ጠጋ ብሎ አባብሎ ( ባይደርስለት እንኳን ) እኔ አለሁ ብሎ ሚጠይቅ የለ " .... ብላ ዝም አለች ። " ልቤ ውስም ትንሽዬ ምስጥ አለች ( ሳይቃጠል በቅጠል ) እንደሚባለው ተራራ ሳትሰራብኝ ማጥፈት አለብኝ " አልኩ በልቤ " ጋሻው ጋራዥ ጋ ያዝልን " ብለው ወርደው መርቀውኝ ሄዱ ። እኔም ወደ ስራዬ በረርርርርርርርርርርርርርርርርኩ። ✍ Henok

በዝምታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ" "ሰው ቢረሳህ እግዚአብሔር አይረሳህም፤ ዓለም ብትጨክንብህ ፈጣሪ ይራራልሃል። ዛሬ የሚያስጨንቅህ ነገር ነገ በታሪክ ይለወጣል። ብቻ አንተ በጸሎት በርታ፣ በትዕግ
በዝምታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ" "ሰው ቢረሳህ እግዚአብሔር አይረሳህም፤ ዓለም ብትጨክንብህ ፈጣሪ ይራራልሃል። ዛሬ የሚያስጨንቅህ ነገር ነገ በታሪክ ይለወጣል። ብቻ አንተ በጸሎት በርታ፣ በትዕግስትም ጠብቀው።" ሰናይ ቀን✨ ሰላም ያውለን!❤️‍🔥

የሕመምን ጥግ ለመረዳት ማበድ ያስፈልጋል።

፡ ጀምበር'ም መፍለቋ፡ መሻሽታ መጥለቋ፡ የማይቀር ሁናቴ ፡ የተፈጥሮ 'ማተም፡ ውቅያኖስ መናወጥ ፡ 'ረግቶ መታተም፣ ፍጥረት ፡ በተፈጥሮ፡ ዑደት ውስጥ መሽከርከር፣ ሲጀመር በለቅሶ፡ ሲቋጭም በለቅሶ፡ 'ላፈር መሆን ማገር፣ አዲስ ሕይወት የለም፡ ከትላንት የቀረ፣ ትርፉ…ታሪክ ሆኖ፡ መባል ነው ነበረ! ✍አቡ

የፀሀይ ጉዞ ማለዳ በመውጣት ጀምሮ ምሽት በመጥለቅ እንደሚጠናቀቅ ። የሰው ህይወትም በመወለድ ተጀምሮ በሞት ይጠናቀቃል ። 📖 ከማዕዘኑ ወዲህ

እውነታውን ኣንዴ ካወክ ኣለማወቅ ኣችልም። ኣንዴ ካየህ ኣለማየትም ኣችልም ከሆነ ኣለመሆን የለምና...ላለመቀበል በታገልን ቁጥር ለመኖር እየደከምን እንሄዳለን.

ትክክለኛ ያልሆነ ትችት በተዘዋዋሪ ምስጋና መሆኑን አስተውል ። ማንም የሞተን ውሻ እንደማይደበድብ አስታውስ ። 🗣 ዴል ካርኔጊ

photo content

አመጣጥህ ዛሬ ስላገኘኸው ዋጋ ይናገራል!!!

ግማሹ ተጓዘ... ቀሪውን በጸጋ ያሳርፈን!
"እነሆ ሙሽራው ይመጣል፤ ተነሱና ተቀበሉት!" (ማቴ. 25፡6) ዛሬ ደብረ ዘይት ነው። የጾማችን እኩሌታ፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓትና የፍርዱ ቀን የሚታሰብበት ዕለት። ጾሙን ግማሽ መንገድ አሳልፈን ለዚህ ላደረሰን አምላክ ምስጋና ይሁን። ያለፈውን በንስሐ፣ የቀረውን ደግሞ በብርታትና በጸሎት ለመጨረስ ያብቃን። እንኳን ለደብረ ዘይት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!🍂

ያለ ገልጋይ ያላስታራቂ ሳይሸመግለን የውስጥ ኣዋቂ ስንቴ ተኳርፈን ስንቴ ታርቀናል ዝም መባባል መች ያስችለናል እንደከፋን ውለን ሳንገናኝ ከርመን በናፍቆት ሰንብተን ችሎ መረሳሳት እንዴት ሊሆንልን ኣያስጨክነንም ችሎ ኣያስችለንም ኣንዳችን ባንዳችን ኣናወራም እንጂ ተጋምዷል ልባችን ተዋውቋል ኣይናችን ልል እፈልግና...... ኣንደበት ያጥረኛል ድፍረት የሚሆነኝ መች ተስፋ ሰጠህኝ እንደ ቀትር ጥላ ስትሸሸኝ ስቀርብህ እምነትን ኣጣለው የራሴን ልብ እንጂ ያንተን ምን ኣውቃለው meron

ሟች ሆነህ ሞትን ፊትህ እየመጣ ስታየው ምን ይሰማህ ይሆን? ያኔ ምን ይታሰብ ይሆን?! አይናቸው እያየ የሞቱት ፤ ሌሎችን ታድገው የሞቱት ነፍሳቸው ከመልካሙ ይኑር!!!

መፅሐፍትን ማንበብ እና በተለይ ስነ ፅሑፍን ማንበብ የሌላ ሰው ጥልቅ ስሜት ውስጥ እንዲገቡ ያስችልዎታል ። የሌሎችን ልብ ወይም ነፍስ ለመግባት በጣም ቀጥተኛ መንገድ ነው ። ስለዚህ ብዙ ትርጉም አለው ። በዚህ ውስጥ መግባትና መውጣት እና ደጋግሞ ወደ ራስህ በመመለስ በዚህ ሂደት ውስጥ የራስህ ድንበር ተለዋዋጭ ይሆናል ። የበለጠ ክፍት እና የበሰለ መሆን ትችላለህ ። ፅሁፎችን ማንበብ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ይሰማኛል ። 🗣 ሃን ካንግ