es
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Ir al canal en Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የጥበብ ማዕድ

El canal የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 974 suscriptores, ocupando la posición 5 411 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 116 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 974 suscriptores.

Según los últimos datos del 25 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 604, y en las últimas 24 horas de -23, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 2.64%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.10% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 419 visualizaciones. En el primer día suele acumular 334 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 26 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 974
Suscriptores
-2324 horas
+1447 días
+60430 días
Archivo de publicaciones
እስቲ አንዳንድ ቦታ መልካምና ምስኪን ሁን ልባቸውን የምር ታገኘዋለህ።

ሰው የሚኖረው የሰው ልብ ውስጥ ነው፡፡

ሳሸንፍ  ሃሴት ኣላደርግም ላንተ ይከፋኛል ስሸነፍ እኔም ሰው ነኝና ለራሴው ያመኛል ኣንድ ነፍስ ተካፍለን  እንኖር ይመስል ድልና ሽንፈቱ ኣንድ ነው ስሜቱ meron

፡፡፥፥፡፡ ለካስ አይፈቀድም!! ፡፡፥፥፡፡
የዓለማችን ቆነጃጅቶች አለባበሳቸው እና ለየት ያለው ስርዓታቸው የራሳቸውን መድረክ አስደምሞ የእኛውንም ትኩረት ሰቅዞ መያዙን ቀጥሏል። ታዲያ ለምን ይሆን? ስንል ለካስ በዓለም የተፈጥሮ ህግ ይህ የክብር ማጋለጥ ወይም የብልግና ዓድማ አይፈቀድ ኖሯል። እንዴት ቢሉ ? ለስብሰባ ከተከማቸን በኋላ ሁሉም ሰው ወደ መድረኩ እንጂ እምብዛም እራሱ ላይ ትኩረት አያደርግም። የጎረቤቴ 20,000 ብር የሚገመት ስልኩ ሲወድቅ አየሁት እና ተጋፍቼ በማንሳት እሰጠዋለሁ። አመሰግናለሁ...ብቻ ብሎኝ የተረጋገጠውን ጫማየን እንኳን ሳያስተውል ወደ መድረኩ .... እኔም እያጉተመተምኩ ወደ ነበርኩበት ... ከልቤ አልወጣም ...ብስጭቴ .. ፊት ለፊቴ አንድ አዛውንት ኪስ ውስጥ ስዓት ነገር አያለሁ ...ሹ...ል...ክ,,,,ሳ...,ብ። መልኩ የሚስብ ሆኖ ሳይሆን መድረኩን ለመሳብ.... ነገር ግን ከኋላ ያየኝ ሰው ስለነበር ጮሆ አሲያዘኝ ...መድረክ ላይ ወጣሁ...ሰው በደንብ ይታያል..እኔንም ሁሉ አየኝ ...ደስ አለኝ ..እንደ ንጉስ መሆኔ። ለካስ የሌላ ሰው ስዓት መዉሰድ በህዝቡ እና በህጉ ዘንድ አይፈቀድ ኖሯል።  ለየዋህ እህቶቻችን!!!
 Tewodros D.

የምሬን እንደ መጓጓት መሰናክል የለም!

መዝገበ ቃላቱ "እና " የምትለዋን ቃል እንደ አያያዥ ፤ ብቻዋን የማትቆም ቁንፅል ይላታል ። በአጭር ምሳሌ" እና " እኔ ነኝ ። በሸረኞችና በደህነኞች መሃል ያለሁ ወይ አልሸርር ወይ አልደህንን " እና " እኔ ነኝ ። ምንም ታሪክ ምንም ትርጉም የለኝም ። ስራዬም ባህሪዬም በሆኑ ነገሮች መሃል መደበቅ ይበዛበታል " እና " ነኝ !! እና ምን ይጠበስ ። 📖 ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም

በጠዋቱ ስራ ለመግባት ነዳጅ ረግጨ በፍጥነት እየበረርኩ ነው ። ሁለት እናቶች መንገድ ላይ ቁመው እጃቸውን በይሉኝታ መንፈስ በስሱ አውለበለቡና ቆሙ ። እኔም ብዋከብም ልያዛቸው አልኩና አጠገባቸው ደርሸ ቆምኩኝ ። " ኑ ግቡ " አልኳቸው ገብተው ቁጭ አሉ ። ደና አደራቹ ? አልኳቸው ከፊት ለፊቴ ባለው መስታየት እያየኋቸው ። አንደኛዋ ፈጠን ብላ " እግዛብሔር ይመስገን " አለች " ወዴት እየሄዳቹ ነው " ? አልኳቸው " ለቅሶ ነው ልጄ " አሉኝ " የቆማችሁበት ቦታ'ኮ ታክሲ አይቆምም ሞልቶ ስለሚመጣ አይዟችሁም ። የተሳሳተ ቦታ ላይ ነበረ የጠበቃችሁ " አልኳቸው " አይይይ!! አይ ልጄ እኛ ምኑን አውቀን ብለህ ነው ከቤት ከወጣን ቆየን እንዲያውም የዚ ሃገር ምስጥ ሰንፎ ነው እንጂ በቆምንበት ይይዘን ነበረ " አለች አንድኛዋ " ሃ ሃ ሃ ምስጥማ እዚ ከተማ ምን ይሰራል እዚያው በለመደበት ገጠር ኩይሳ ይስራ'ጂ " አልኩ "አይይይ ! ልጄ አላወክም እንዴ" ? አለች አንድኛዋ ሰማይ ሰማይ እያየች ቆይታ "ምን" አልኩ "እዚ ከተማ ምስጥ መኖሩን " "አረ ! አላወኩም " " የገጠሩ ምስጥ የእርሻ መሬት ላይ አፈር ነፍቶ ኩይሳ ይሰራበትና መሬቱ እንዳይታረስ ተራራ ይሰራል ። የከተማው ግን ሰውና ሰው ነው ሚስጥ ። ትዕቢት የሚባል ምስጥ ውስጣችን ላይ ገብቶ ልባችንን ነፋፍቶ ተራራ ይሰራበታል ። ጎረቤት መጠየቅ የለ ሰው ሰላም ማለት የለ የሚያለቅሰውን ሰው ጠጋ ብሎ አባብሎ ( ባይደርስለት እንኳን ) እኔ አለሁ ብሎ ሚጠይቅ የለ " .... ብላ ዝም አለች ። " ልቤ ውስም ትንሽዬ ምስጥ አለች ( ሳይቃጠል በቅጠል ) እንደሚባለው ተራራ ሳትሰራብኝ ማጥፈት አለብኝ " አልኩ በልቤ " ጋሻው ጋራዥ ጋ ያዝልን " ብለው ወርደው መርቀውኝ ሄዱ ። እኔም ወደ ስራዬ በረርርርርርርርርርርርርርርርርኩ። ✍ Henok

በዝምታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ" "ሰው ቢረሳህ እግዚአብሔር አይረሳህም፤ ዓለም ብትጨክንብህ ፈጣሪ ይራራልሃል። ዛሬ የሚያስጨንቅህ ነገር ነገ በታሪክ ይለወጣል። ብቻ አንተ በጸሎት በርታ፣ በትዕግ
በዝምታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ" "ሰው ቢረሳህ እግዚአብሔር አይረሳህም፤ ዓለም ብትጨክንብህ ፈጣሪ ይራራልሃል። ዛሬ የሚያስጨንቅህ ነገር ነገ በታሪክ ይለወጣል። ብቻ አንተ በጸሎት በርታ፣ በትዕግስትም ጠብቀው።" ሰናይ ቀን✨ ሰላም ያውለን!❤️‍🔥

የሕመምን ጥግ ለመረዳት ማበድ ያስፈልጋል።

፡ ጀምበር'ም መፍለቋ፡ መሻሽታ መጥለቋ፡ የማይቀር ሁናቴ ፡ የተፈጥሮ 'ማተም፡ ውቅያኖስ መናወጥ ፡ 'ረግቶ መታተም፣ ፍጥረት ፡ በተፈጥሮ፡ ዑደት ውስጥ መሽከርከር፣ ሲጀመር በለቅሶ፡ ሲቋጭም በለቅሶ፡ 'ላፈር መሆን ማገር፣ አዲስ ሕይወት የለም፡ ከትላንት የቀረ፣ ትርፉ…ታሪክ ሆኖ፡ መባል ነው ነበረ! ✍አቡ

የፀሀይ ጉዞ ማለዳ በመውጣት ጀምሮ ምሽት በመጥለቅ እንደሚጠናቀቅ ። የሰው ህይወትም በመወለድ ተጀምሮ በሞት ይጠናቀቃል ። 📖 ከማዕዘኑ ወዲህ

እውነታውን ኣንዴ ካወክ ኣለማወቅ ኣችልም። ኣንዴ ካየህ ኣለማየትም ኣችልም ከሆነ ኣለመሆን የለምና...ላለመቀበል በታገልን ቁጥር ለመኖር እየደከምን እንሄዳለን.

ትክክለኛ ያልሆነ ትችት በተዘዋዋሪ ምስጋና መሆኑን አስተውል ። ማንም የሞተን ውሻ እንደማይደበድብ አስታውስ ። 🗣 ዴል ካርኔጊ

photo content

አመጣጥህ ዛሬ ስላገኘኸው ዋጋ ይናገራል!!!

ግማሹ ተጓዘ... ቀሪውን በጸጋ ያሳርፈን!
"እነሆ ሙሽራው ይመጣል፤ ተነሱና ተቀበሉት!" (ማቴ. 25፡6) ዛሬ ደብረ ዘይት ነው። የጾማችን እኩሌታ፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓትና የፍርዱ ቀን የሚታሰብበት ዕለት። ጾሙን ግማሽ መንገድ አሳልፈን ለዚህ ላደረሰን አምላክ ምስጋና ይሁን። ያለፈውን በንስሐ፣ የቀረውን ደግሞ በብርታትና በጸሎት ለመጨረስ ያብቃን። እንኳን ለደብረ ዘይት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!🍂

ያለ ገልጋይ ያላስታራቂ ሳይሸመግለን የውስጥ ኣዋቂ ስንቴ ተኳርፈን ስንቴ ታርቀናል ዝም መባባል መች ያስችለናል እንደከፋን ውለን ሳንገናኝ ከርመን በናፍቆት ሰንብተን ችሎ መረሳሳት እንዴት ሊሆንልን ኣያስጨክነንም ችሎ ኣያስችለንም ኣንዳችን ባንዳችን ኣናወራም እንጂ ተጋምዷል ልባችን ተዋውቋል ኣይናችን ልል እፈልግና...... ኣንደበት ያጥረኛል ድፍረት የሚሆነኝ መች ተስፋ ሰጠህኝ እንደ ቀትር ጥላ ስትሸሸኝ ስቀርብህ እምነትን ኣጣለው የራሴን ልብ እንጂ ያንተን ምን ኣውቃለው meron

ሟች ሆነህ ሞትን ፊትህ እየመጣ ስታየው ምን ይሰማህ ይሆን? ያኔ ምን ይታሰብ ይሆን?! አይናቸው እያየ የሞቱት ፤ ሌሎችን ታድገው የሞቱት ነፍሳቸው ከመልካሙ ይኑር!!!

መፅሐፍትን ማንበብ እና በተለይ ስነ ፅሑፍን ማንበብ የሌላ ሰው ጥልቅ ስሜት ውስጥ እንዲገቡ ያስችልዎታል ። የሌሎችን ልብ ወይም ነፍስ ለመግባት በጣም ቀጥተኛ መንገድ ነው ። ስለዚህ ብዙ ትርጉም አለው ። በዚህ ውስጥ መግባትና መውጣት እና ደጋግሞ ወደ ራስህ በመመለስ በዚህ ሂደት ውስጥ የራስህ ድንበር ተለዋዋጭ ይሆናል ። የበለጠ ክፍት እና የበሰለ መሆን ትችላለህ ። ፅሁፎችን ማንበብ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ይሰማኛል ። 🗣 ሃን ካንግ