ch
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

前往频道在 Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

显示更多

📈 Telegram 频道 የጥበብ ማዕድ 的分析概览

频道 የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 974 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 411,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 116

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 974 名订阅者。

根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 604,过去 24 小时变化为 -23,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 2.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.10% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 419 次浏览,首日通常累积 334 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 974
订阅者
-2324 小时
+1447
+60430
帖子存档
እስቲ አንዳንድ ቦታ መልካምና ምስኪን ሁን ልባቸውን የምር ታገኘዋለህ።

ሰው የሚኖረው የሰው ልብ ውስጥ ነው፡፡

ሳሸንፍ  ሃሴት ኣላደርግም ላንተ ይከፋኛል ስሸነፍ እኔም ሰው ነኝና ለራሴው ያመኛል ኣንድ ነፍስ ተካፍለን  እንኖር ይመስል ድልና ሽንፈቱ ኣንድ ነው ስሜቱ meron

፡፡፥፥፡፡ ለካስ አይፈቀድም!! ፡፡፥፥፡፡
የዓለማችን ቆነጃጅቶች አለባበሳቸው እና ለየት ያለው ስርዓታቸው የራሳቸውን መድረክ አስደምሞ የእኛውንም ትኩረት ሰቅዞ መያዙን ቀጥሏል። ታዲያ ለምን ይሆን? ስንል ለካስ በዓለም የተፈጥሮ ህግ ይህ የክብር ማጋለጥ ወይም የብልግና ዓድማ አይፈቀድ ኖሯል። እንዴት ቢሉ ? ለስብሰባ ከተከማቸን በኋላ ሁሉም ሰው ወደ መድረኩ እንጂ እምብዛም እራሱ ላይ ትኩረት አያደርግም። የጎረቤቴ 20,000 ብር የሚገመት ስልኩ ሲወድቅ አየሁት እና ተጋፍቼ በማንሳት እሰጠዋለሁ። አመሰግናለሁ...ብቻ ብሎኝ የተረጋገጠውን ጫማየን እንኳን ሳያስተውል ወደ መድረኩ .... እኔም እያጉተመተምኩ ወደ ነበርኩበት ... ከልቤ አልወጣም ...ብስጭቴ .. ፊት ለፊቴ አንድ አዛውንት ኪስ ውስጥ ስዓት ነገር አያለሁ ...ሹ...ል...ክ,,,,ሳ...,ብ። መልኩ የሚስብ ሆኖ ሳይሆን መድረኩን ለመሳብ.... ነገር ግን ከኋላ ያየኝ ሰው ስለነበር ጮሆ አሲያዘኝ ...መድረክ ላይ ወጣሁ...ሰው በደንብ ይታያል..እኔንም ሁሉ አየኝ ...ደስ አለኝ ..እንደ ንጉስ መሆኔ። ለካስ የሌላ ሰው ስዓት መዉሰድ በህዝቡ እና በህጉ ዘንድ አይፈቀድ ኖሯል።  ለየዋህ እህቶቻችን!!!
 Tewodros D.

የምሬን እንደ መጓጓት መሰናክል የለም!

መዝገበ ቃላቱ "እና " የምትለዋን ቃል እንደ አያያዥ ፤ ብቻዋን የማትቆም ቁንፅል ይላታል ። በአጭር ምሳሌ" እና " እኔ ነኝ ። በሸረኞችና በደህነኞች መሃል ያለሁ ወይ አልሸርር ወይ አልደህንን " እና " እኔ ነኝ ። ምንም ታሪክ ምንም ትርጉም የለኝም ። ስራዬም ባህሪዬም በሆኑ ነገሮች መሃል መደበቅ ይበዛበታል " እና " ነኝ !! እና ምን ይጠበስ ። 📖 ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም

በጠዋቱ ስራ ለመግባት ነዳጅ ረግጨ በፍጥነት እየበረርኩ ነው ። ሁለት እናቶች መንገድ ላይ ቁመው እጃቸውን በይሉኝታ መንፈስ በስሱ አውለበለቡና ቆሙ ። እኔም ብዋከብም ልያዛቸው አልኩና አጠገባቸው ደርሸ ቆምኩኝ ። " ኑ ግቡ " አልኳቸው ገብተው ቁጭ አሉ ። ደና አደራቹ ? አልኳቸው ከፊት ለፊቴ ባለው መስታየት እያየኋቸው ። አንደኛዋ ፈጠን ብላ " እግዛብሔር ይመስገን " አለች " ወዴት እየሄዳቹ ነው " ? አልኳቸው " ለቅሶ ነው ልጄ " አሉኝ " የቆማችሁበት ቦታ'ኮ ታክሲ አይቆምም ሞልቶ ስለሚመጣ አይዟችሁም ። የተሳሳተ ቦታ ላይ ነበረ የጠበቃችሁ " አልኳቸው " አይይይ!! አይ ልጄ እኛ ምኑን አውቀን ብለህ ነው ከቤት ከወጣን ቆየን እንዲያውም የዚ ሃገር ምስጥ ሰንፎ ነው እንጂ በቆምንበት ይይዘን ነበረ " አለች አንድኛዋ " ሃ ሃ ሃ ምስጥማ እዚ ከተማ ምን ይሰራል እዚያው በለመደበት ገጠር ኩይሳ ይስራ'ጂ " አልኩ "አይይይ ! ልጄ አላወክም እንዴ" ? አለች አንድኛዋ ሰማይ ሰማይ እያየች ቆይታ "ምን" አልኩ "እዚ ከተማ ምስጥ መኖሩን " "አረ ! አላወኩም " " የገጠሩ ምስጥ የእርሻ መሬት ላይ አፈር ነፍቶ ኩይሳ ይሰራበትና መሬቱ እንዳይታረስ ተራራ ይሰራል ። የከተማው ግን ሰውና ሰው ነው ሚስጥ ። ትዕቢት የሚባል ምስጥ ውስጣችን ላይ ገብቶ ልባችንን ነፋፍቶ ተራራ ይሰራበታል ። ጎረቤት መጠየቅ የለ ሰው ሰላም ማለት የለ የሚያለቅሰውን ሰው ጠጋ ብሎ አባብሎ ( ባይደርስለት እንኳን ) እኔ አለሁ ብሎ ሚጠይቅ የለ " .... ብላ ዝም አለች ። " ልቤ ውስም ትንሽዬ ምስጥ አለች ( ሳይቃጠል በቅጠል ) እንደሚባለው ተራራ ሳትሰራብኝ ማጥፈት አለብኝ " አልኩ በልቤ " ጋሻው ጋራዥ ጋ ያዝልን " ብለው ወርደው መርቀውኝ ሄዱ ። እኔም ወደ ስራዬ በረርርርርርርርርርርርርርርርርኩ። ✍ Henok

በዝምታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ" "ሰው ቢረሳህ እግዚአብሔር አይረሳህም፤ ዓለም ብትጨክንብህ ፈጣሪ ይራራልሃል። ዛሬ የሚያስጨንቅህ ነገር ነገ በታሪክ ይለወጣል። ብቻ አንተ በጸሎት በርታ፣ በትዕግ
በዝምታ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ" "ሰው ቢረሳህ እግዚአብሔር አይረሳህም፤ ዓለም ብትጨክንብህ ፈጣሪ ይራራልሃል። ዛሬ የሚያስጨንቅህ ነገር ነገ በታሪክ ይለወጣል። ብቻ አንተ በጸሎት በርታ፣ በትዕግስትም ጠብቀው።" ሰናይ ቀን✨ ሰላም ያውለን!❤️‍🔥

የሕመምን ጥግ ለመረዳት ማበድ ያስፈልጋል።

፡ ጀምበር'ም መፍለቋ፡ መሻሽታ መጥለቋ፡ የማይቀር ሁናቴ ፡ የተፈጥሮ 'ማተም፡ ውቅያኖስ መናወጥ ፡ 'ረግቶ መታተም፣ ፍጥረት ፡ በተፈጥሮ፡ ዑደት ውስጥ መሽከርከር፣ ሲጀመር በለቅሶ፡ ሲቋጭም በለቅሶ፡ 'ላፈር መሆን ማገር፣ አዲስ ሕይወት የለም፡ ከትላንት የቀረ፣ ትርፉ…ታሪክ ሆኖ፡ መባል ነው ነበረ! ✍አቡ

የፀሀይ ጉዞ ማለዳ በመውጣት ጀምሮ ምሽት በመጥለቅ እንደሚጠናቀቅ ። የሰው ህይወትም በመወለድ ተጀምሮ በሞት ይጠናቀቃል ። 📖 ከማዕዘኑ ወዲህ

እውነታውን ኣንዴ ካወክ ኣለማወቅ ኣችልም። ኣንዴ ካየህ ኣለማየትም ኣችልም ከሆነ ኣለመሆን የለምና...ላለመቀበል በታገልን ቁጥር ለመኖር እየደከምን እንሄዳለን.

ትክክለኛ ያልሆነ ትችት በተዘዋዋሪ ምስጋና መሆኑን አስተውል ። ማንም የሞተን ውሻ እንደማይደበድብ አስታውስ ። 🗣 ዴል ካርኔጊ

photo content

አመጣጥህ ዛሬ ስላገኘኸው ዋጋ ይናገራል!!!

ግማሹ ተጓዘ... ቀሪውን በጸጋ ያሳርፈን!
"እነሆ ሙሽራው ይመጣል፤ ተነሱና ተቀበሉት!" (ማቴ. 25፡6) ዛሬ ደብረ ዘይት ነው። የጾማችን እኩሌታ፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓትና የፍርዱ ቀን የሚታሰብበት ዕለት። ጾሙን ግማሽ መንገድ አሳልፈን ለዚህ ላደረሰን አምላክ ምስጋና ይሁን። ያለፈውን በንስሐ፣ የቀረውን ደግሞ በብርታትና በጸሎት ለመጨረስ ያብቃን። እንኳን ለደብረ ዘይት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!🍂

ያለ ገልጋይ ያላስታራቂ ሳይሸመግለን የውስጥ ኣዋቂ ስንቴ ተኳርፈን ስንቴ ታርቀናል ዝም መባባል መች ያስችለናል እንደከፋን ውለን ሳንገናኝ ከርመን በናፍቆት ሰንብተን ችሎ መረሳሳት እንዴት ሊሆንልን ኣያስጨክነንም ችሎ ኣያስችለንም ኣንዳችን ባንዳችን ኣናወራም እንጂ ተጋምዷል ልባችን ተዋውቋል ኣይናችን ልል እፈልግና...... ኣንደበት ያጥረኛል ድፍረት የሚሆነኝ መች ተስፋ ሰጠህኝ እንደ ቀትር ጥላ ስትሸሸኝ ስቀርብህ እምነትን ኣጣለው የራሴን ልብ እንጂ ያንተን ምን ኣውቃለው meron

ሟች ሆነህ ሞትን ፊትህ እየመጣ ስታየው ምን ይሰማህ ይሆን? ያኔ ምን ይታሰብ ይሆን?! አይናቸው እያየ የሞቱት ፤ ሌሎችን ታድገው የሞቱት ነፍሳቸው ከመልካሙ ይኑር!!!

መፅሐፍትን ማንበብ እና በተለይ ስነ ፅሑፍን ማንበብ የሌላ ሰው ጥልቅ ስሜት ውስጥ እንዲገቡ ያስችልዎታል ። የሌሎችን ልብ ወይም ነፍስ ለመግባት በጣም ቀጥተኛ መንገድ ነው ። ስለዚህ ብዙ ትርጉም አለው ። በዚህ ውስጥ መግባትና መውጣት እና ደጋግሞ ወደ ራስህ በመመለስ በዚህ ሂደት ውስጥ የራስህ ድንበር ተለዋዋጭ ይሆናል ። የበለጠ ክፍት እና የበሰለ መሆን ትችላለህ ። ፅሁፎችን ማንበብ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ይሰማኛል ። 🗣 ሃን ካንግ