fa
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

رفتن به کانال در Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام የጥበብ ማዕድ

کانال የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 932 مشترک است و جایگاه 5 411 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 116 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 932 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 604 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -23 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 2.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.10% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 419 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 334 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 932
مشترکین
-2324 ساعت
+1447 روز
+60430 روز
آرشیو پست ها
🚛 ከባድ ተሽከርካሪው ገደላማ ስፍራ ላይ ሲጓዝ ሚዛኑን መጠበቅ ባለመቻሉ ወደ ገደላማው ስፍራ ሲወድቅ ታይቷል፡፡ መጋቢት 30 2018 - እሮብ ለበ ሲኖትራክ ይማር🙏

ማን ይጠረጥራል ጠልፎ እንደሚጥል ምርኩዝ ያደረጉት እኔስ ምን ኣውቃለው ኣቅም እንኳ እንደሚያንስ ጠጎ ለመነሳት የከርሞው እንዲሽር ማንን እና እንዴት ካሳ ይጠየቃል በገዛ ራስ ጥፋት.. . meron

ወገን ስለዚህ አስረዱን በነዳጅ ጭማሪ ምክንያት የማሳጅ ዋጋ በየጊዜው እየጨመረ ነው በማለት ደንበኞች ቅሬታ እያቀረቡ ነው?! በእርግጥ የቧንቧ ውሃ እስክትመጣ ለሳምንታት ሳንታጠብ እየጠበቅን ያለነውን
ወገን ስለዚህ አስረዱን በነዳጅ ጭማሪ ምክንያት የማሳጅ ዋጋ በየጊዜው እየጨመረ ነው በማለት ደንበኞች ቅሬታ እያቀረቡ ነው?! በእርግጥ የቧንቧ ውሃ እስክትመጣ ለሳምንታት ሳንታጠብ እየጠበቅን ያለነውን አይመለከትም!

" ሜሉ  ተሻለሽ ውሎሽ እንዴት ነበር "  አልኩኝ ጥያቄዎቼን አከታትዬ  እና ትኩስ ግንባሯን እየሳምኩ " ደናነኝ ብሩኬ  ግን ምሳ በልተካል "  አለችኝ ጤንነቷ ሳይሆን የኔ በርሃብ መዋሉ አሳስቧት " እኔማ በልቻለሁ ይልቅ ላንቺ እያሰብኩ ነበር ምሳ እንድትሰራልሽ ቤሪን ነግሬያት ነበረ መጥታለች " ? አልኩ " አሁን  አሁን ነው የወጣችው  መክሰስም ሰርታልሃለች " አለችኝ  አይን አይኔን በናፍቆት እያየች " እሺ ያከሆነ ተጣጥቤ ልብሴን ቀይሬ ምግቡን ይዤ መጣሁ "  ብዬ ሻውር ገብቸ ልብሴን ለባብሸ ምግቡን ይዤ ሜሉ ወደተኛችበት ሶፋ አመራሁ " ተነሺ ! ተነሺ ! " ብዬ የለበሰችውን አንሶለ ገለጥኩ "  እንዴ ! ለምንድነው ሻወር ወስደሽ ልብስ ያልቀየርሺው ? ደሞም ቅድም በስልክ ለቤሪም ነግሬያት ነበረ ትታጠብ ብዬ አልነገረችሽም ?"  አልኩኝ ንድድ ብየ " ነግራኛለች ግን እኔ እምቢ አልኩ " አለች ዝግ ባለ ድምፅ " አሁን ተነሺና ሻወር ውሰጂ " አልኳት ከሶፋው ቀና እያረኳት እምብዬው ! እምብዬው ! ብላ  ደረቴ ላይ ፊቷን ቀብራ ዝም አለች " ለምንድነው ማትታጠቢው ደሞም ዶክተሩን አናግሬዋለሁ መታጠብ ትችላለች ብሏል "  አልኩኝ ፊቷን ከደረቴ ቀና ለማድረግ እየሞከርኩ " እየበረደኝ ነው አልታጠብም አለች  "  ፊቷን ቅጭም እያደረገች " እሺ ውሃውን አሞቀዋለሁ " " ሙቁን አልወደውማ ! " አለች ትከሻዋን ሰበቅ አድርጋ " ጭራሽ በዚህ እንጨቃጨቅ ? ለምንድነው ምልሽን ማትሰሚ ?"  አልኩ ጥያቄዬን ከንዴት ጋር ቀላቅዬ " ኡፍ ! ብሩኬ  ኡፍ ! " ብላ  በተደገፈችው ትራስ ደረቴን መታ አድርጋ ለመታጠብ ገባች እኔም ሻወሯን እስከምትጨርስ ትኩስ ነገር ላፈላላት ኪችን ገባሁ ።      ✍ Henok

ሰበር 🔥 አሜሪካ እና ኢራን የ2 ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት አድርገዋል ። የሆርሙዝ ሰርጥም ሙሉ ለሙሉ ይከፈታል ። አሁን ገበያውን ጣሪያ ያወጣህ ነጋዴ ሁላ እኛ ሳንቀጥለው ጦርነቱን በጊዜ አውርድ!!!

አንድ ኪሎ ስጋ በ650 ብር‼️ #በአዲስ_አበባ ከተማ ሥጋ በኪሎ 650 ብር እንዲሸጥ ተወሰነ‼️ #የአዲስ_አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በከተማዋ የሸቀጦች እጥረት እንዳይከሰትና ገበያው እንዲረጋጋ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ቢሮው በተለይ የሥጋ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ በአንድ ኪሎ 650 ብር እንዲሸጥ መወሰኑን ይፋ አድርጓል። ​ መንግስት ደሞ April the fool. አለፈ እኮ

አንቺ ሴት ለምንድነው ምትጨነቂው ? ለምንድነው የምታለቅሺው?  በይ አሁን ተነሺ ! ወገብሽን እሰሪ የወንድ ጥገኛ አትሁኚ በራስሽ ቁሚ  ፈጣሪሽን ይዘሽ ወደ ፊት ቀጥይ 💪💪💪 ይቺ አለም የውድድር ናት ውድድሩን ምታሸንፊው ቁጭ ብለሽ አይደለም ይልቅ ቁጭ ያልሺበት ጊዜ አሁን አልቋል ። አሁን ጊዜው የምትንቀሳቀሺበት ነው ። ዓላማሺን ከፊት አድርጊው ለቤተሰቦችሽ መከታ ሁኚ ። ቤተሰቦችሽን ለመርዳት ፆታሽ ወንድ መሆን አያስፈልግም ዓላማና ወኔ ይኑርሽ ። የሀገራችን ኢኮኖሚ ለመንቀሳቀስ አመቺ ባይሆንም አንቺ ግን ልዩ ሴት ነሽ መንገድ አታጪም አንድን ጉንዳን ይዘን በአፈር ውስጥ በነፍሱ ብንቀብረው ጉንዳኑ ሲንቀሳቀስ አፈሩ እየተሸረሸረ ከተቀበረበት ይወጣል ያ የሚሆነው ደግሞ በመንቀሳቀሱ ነው ።  አንቺም ተንቀሳቀሺና ከላይሽ ላይ  ያሉትን ጭንቀቶችንሽ  አራግፊ ። ጠንካራ ሴት ሁኚ እሺ  ፈጣሪ ካንቺ ጋር ነው  አይዞሽ 💪💪💪💪     ✍ Henok

ሁሌም ከምቀመጥበት ቦታ ቁጭ ብየ አስባለሁ ። ማሰብን ትክዝ ማለትን ባንድ ነገር ላይ ትኩረት ሰጥቸ መመልከትን እወዳለሁ ። ሰው ቤት መጥቶ ስብስብ ሲል አልወድም ወደ ፀጥተኛውና ከቀዝቃዛው ክፍሌ እገባለሁ ። ብዙ ወሬ አልወድም በችሎታዬም አልኩራራም ። አለባበሴ ቀለል ያሉ ናቸው ። ቡና በጣም እወዳለሁ የቡና ደምበኛዬም ሜላት ናት እኔን ትረዳኛለች። ሁሌ ምቀመጥባት አብዛኛው ሰው ከሚቀመጥበት ቦታ ፈንጠር ብላ ያለች አንድ ወንበርና አንድ ጠረንጴዛ ያለች ቦታ ናት ። ሌሎች በጀማ ተቀምጠው ስለ ሀገራችን ኢኮኖሚ ፣ ስለ ፖለቲካ ፣ ስለ ግለሰብ ፣ ስለ ቤተሰባቸው ሚስጥርም ጭምር እዚ ቡና ቤት ቁጭ ብለው እንደ Party አበባ ይበትናሉ ። እኔ መፅሐፌን ከፍቸ ቡናዬ ጋ አጣጥማለሁ። አዲስ ሰውም ስተዋወቅ በቀይ መስመር ዙሪያዬን አጥራለሁ ። ያቺን ቀይ መስመር ካለፈ ግን ግንኙነቱን አቋርጣለሁ ስለ ራሴ ብዙ ማውራት አልወድም ። እኔን የሚመስጠኝ ሰው አዲስ ነገር ለማወቅ የሚጓጓ እንጂ የሰውን ደካማ ጎን አምጥቶ እኔ ጋ ለሃሜት የሚመጣን አልቀበልም ። ያ የራሴ ቀይ መስመር ነው ። ለዛም ይመስለኛል ብዙ ጓደኛ የሌለኝ ። ሃሜት ላይ የተመሰረተ ጓደኝነት አሸዋ ላይ እንደ ተሰራ ቤት ነው በትንሽ ስህተት ይፈርሳል ። እንደ ባዘቶ የጠራውን ብቸኝነቴን እወደዋለሁ ፀጥታ ላይ መቆየት ዝምምምምም ማለት ጭጭ ማለት ትኩረት ማድረግ እ ወ ዳ ለ ሁ ❤ ✍ Henok

ለሌላ ሰው አንተ ሌላኛው ሰው ነህ!

“ሰዎችን ኣልጠላቸውምነገር ግን ከኣጠገቤ በሌሉበት ጊዜ ጥሩ ስሜት ይሰማኛል!”🙂          — ቻርለስ ቡኮውስኪ

ድንበርን በእባብ እና አዞ‼️ ህንድ ድንበሯን ለመጠበቅ እባቦችን እና አዞዎችን ልትጠቀም መሆኑ ተሰማ‼️ ሂንዱ የሀገሪቱን የድንበር ደህንነት ሃይል መመሪያን በመጥቀስ እንደዘገበው በህንድ-ባንግላዴሽ
ድንበርን በእባብ እና አዞ‼️ ህንድ ድንበሯን ለመጠበቅ እባቦችን እና አዞዎችን ልትጠቀም መሆኑ ተሰማ‼️ ሂንዱ የሀገሪቱን የድንበር ደህንነት ሃይል መመሪያን በመጥቀስ እንደዘገበው በህንድ-ባንግላዴሽ ድንበር በሚገኙ ወንዞች፣ረግረጋማ ቦታዎች እና አስቸጋሪ የሆኑ ቦታዎች ላይ አዞ እና እባብን ለድንበር ጥበቃ ለማሰማራት እቅድ መነደፉን ዘገባው ጠቅሷል። ምስል-በ AI የበለፀገ

አንዳንዴ ውስጥህ ሊያታላልህ ሚሞክረው  አንዳንድ ነገሮች ከሌሎች ይልቅ ለአንተ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ በማሳመን ነው።     ለምሳሌ የምትሸጠው ነገር ለአንተ ገንዘብ ላይ ገንዘብ ማምጫ ሊሆን ይችላል ለአንዱ ግን የእለት እስትንፋሱ ነው።

የአባቴ ጥንካሬ ሁሌም ሳስበው ይገርመኛል ። አንድን ነገር አሳካለሁ ብሎ ላመነበት ነገር ተስፋ አይቆርጥም እስከ መጨረሻው ይፋለማል ። አባቴ ድንቁርናን አይወድም በመንጋ ማሰብን አይወድም ።  አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ በጠቆመበት መንገድ አይሄድም  ቆም ብሎ ያስባል፣ ይጠይቃል ያውቃል። ልጅ ሆኜ ከወንድሜ ጋ ኳስ እየተጫወትን " እኔንም አስገቡኝ "? አለ  እኛም ግባ ብለን መጫወት ጀመርን መሃል በገባ ጭዋታ ነበረ እየተጫወትን የነበረው እኔ ከመሃል ሁኜ ኳሷን ለመንካት እየታገልኩ እነሱ ( ወንድሜና አባቴ ) አላስነካ አሉኝ ። " አረ በቃኝ ደክሞኛል"  ብዬ ከጨዋታው  ወጣሁ  እሱም ወደ እኔ ተጠግቶ "  ይሀውልህ ልጄ መሃል በገባ ጨዋታ ላይ ያንተ እንቅስቃሴ ዝግ ያለ ከሆነ እነሱ እንዲያርፉ ክፍተት እየሰጠህ ነው ። አንተ በፍጥነት ሮጠህ ኳሷን መቀማት አለብህ ካልሆነ ይደክምሃል ተስፋም ትቆርጣለህ ። ያንተ ፍጥነት እነሱን ያስጨንቃቸዋል አንተ በሮጥክ ቁጥር ለማን ኳሷን እንደሚሰጡ ይወዛገባሉ አንተም ትቀማለህ ግን ለዚያ ደግሞ ያንተ ፍጥነትና ተስፋ አለመቁረጥ ትልቅ ሚና አላቸው ። "  አሁን እኮ ነው ያሰብኩት አባቴ ትልቅ መምህሬ ነው ። ሰሞኑን ስልችት ሲለኝ ያነቃቃኝ  የአባቴ ንግግር ።    ✍ Henok

Repost from N/a
መጸውነ ሰኑይ❤️‍🩹🥺

አውቃለሁ የሚል ሰው ዝምታ አይሆንለትም ። ዝምታ አለማወቅን ማወቅ ይሻል ። 📖 አርምሞ

<< በራስ ለመቆም ቆርጠን የተነሳል ለት ነኝ ብለን ያልነው ማንነት ይጠፋል። በቤተሰብ በጓደኛ በማህበረሰብ ተደግፈን ከሩቅ ሆነን የተቸነውን ህይወት እንኖራለን እንፈርድበት የነበረውን የሰው ድካም ሆነን እናገኘዋለን ። ኩራታችንና ፍርሃታችን የመኖር ጠላት ይሆኑን ይጀምራል ኣይመጥነኝም ያልነውን ጭራሽ እናሳድዳለን።  ህይወት የተነገረን እንዳልነበር የሰውን ተሞክሮ የመድገም ያህል ግልጽ እንዳይደል በራስ መቆም ስንጀምር ይገባናል። ከሰው ኣስተያየትና ኣመለካከት በላይ     የውስጥ ሰላም ምን ያህል ዋጋ እንዳለው እንረዳለን ትርምስምሱ ወደወጣበት ኣለም ስንነቃ የነበረው እንዳልነበር ይሆናል እኛም፡ያልሆነውን የመሆን እድል ይኖረናል ።     ብዙ ነገራችን ልክ እንዳልነበር  ካለንበትም ሰብረን መውጣት እንዳለብን ይሰማናል። ችግሩ ሚመጣው የመሰማቱ ግዜ፡ላይ ኣደለም ሰምተን መለወጥ እንዳለብን ያመንን ግዜ ላይ ነው። ችግሩ ትልቅ መነዋወጥን ያመጣል ይንን ኣውቆ መቀበል ተቀብሎም ወዳልነበርነው ማንነት እና  ሆነን ወደማናቀው ልንሆነው ወደምንሻው እኛ የመቀየር  መንገዱን ስንጀምር የዛኔ ግን ጀግንነቱ ይለያል። >>

ያረፈደ ንቃት ከመተኛት ይቆጠራል።

ከሞቱ አሟሟቱ!

ስለ ሆሳዕና (Palm Sunday) የሚገርሙና ምናልባትም የማታውቋቸው እውነታዎች፦ "ሆሳዕና" የሚለው ቃል ትርጉም ብዙዎቻችን "ሆሳዕና" ማለት የምስጋና ቃል ብቻ ይመስለናል፤ ነገር ግን ትርጉሙ "አሁን አድን" (Save us now/Please save) ማለት ነው። ሕዝቡ ኢየሱስን ሲቀበሉት "ጌታ ሆይ አሁን አድነን" ብለው እየለመኑትና እየጸለዩለት ነበር። የአህያዋ ምስጢር (ሰላም እንጂ ጦርነት አይደለም) በጥንት ዘመን ነገሥታት ለጦርነት ሲወጡ በፈረስ ላይ ይሳፈሩ ነበር። በሰላም ጊዜና ለደስታ ሲመጡ ግን በአህያ ላይ ይሳፈራሉ። ኢየሱስ በአህያ ላይ መሳፈሩ "እኔ የሰላም ንጉሥ እንጂ የጦርነት ንጉሥ አይደለሁም" የሚል ትልቅ መልእክት ለማስተላለፍ ነው። የዘንባባው (Palm) ምስጢር ዘንባባ በዛ ዘመን "የድል" (Victory) ምልክት ነበር። ሰዎች ዘንባባውን መሬት ላይ ያነጠፉት ኢየሱስን እንደ አሸናፊ ንጉሥ ስለቆጠሩት ነው። እኛም ዛሬ በጣታችን ላይ የዘንባባ ቀለበት የምናደርገው ያንን የድል ምልክት ለማስታወስ ነው። የሕፃናት ጩኸት በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንደተጠቀሰው፣ በዛን ዕለት በቤተ መቅደስ ውስጥ በከፍተኛ ድምፅ "ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ" እያሉ የጮሁት ሕፃናት ነበሩ። ሽማግሌዎቹና ፈሪሳውያኑ ዝም እንዲሉ ቢፈልጉም፣ ኢየሱስ ግን "እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ" ብሎ የሕፃናቱን ንጹሕ ምስጋና ተቀብሏል። የኢትዮጵያ ሆሳዕና ልዩነት በሌሎች ሀገራት ዘንባባውን ይዘው ብቻ ነው የሚሄዱት። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ግን ዘንባባውን ቀለበት፣ አክሊልና መስቀል አድርገን እንሰራዋለን። ይህ የሚያሳየው ኢየሱስን በልባችን አንግሰን፣ በመስቀሉ ድል ማግኘታችንን የምንገልጽበት የራሳችን ውብ ባህልና ዕምነት ነው። እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳች

ሆሳዕና❤️‍🩹 "ሕፃናት 'ሆሳዕና በአርያም'🌿 እያሉ በንጹሕ ልባቸው ዘመሩ... ጌታ ሆይ የእኛንም ልብ እንደ ሕፃናቱ ንጹሕ አድርግልን። Enkuan aderesachu evry1🫶🏻