fa
Feedback
EB-ACADEMY ARADA.9-12 EDUCATION CHANNEL🇪🇹🇪🇹🇪🇹!!

EB-ACADEMY ARADA.9-12 EDUCATION CHANNEL🇪🇹🇪🇹🇪🇹!!

رفتن به کانال در Telegram

"An investment in knowledge pays the best interest" Benjamin Franklin...

نمایش بیشتر
1 512
مشترکین
-224 ساعت
-77 روز
-1030 روز
آرشیو پست ها
Condensed Physics curriculum.pdf5.29 KB

የፈተና ስጋት 2018 ዓ.ም ኢቢ-አ.docx4.20 MB

ለኢቢ አካዳሚ ከ9ኛ-12ኛ ወላጆች አሳዳጊዎች የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከቤት ወደትምህርት ቤት እንደሄዱ ነው ወላጅ የሚያውቀው ነገር ግን አንዳንድ ተማሪዎች ወደ ት/ቤት እየመጡ እንዳልሆነ ክትትል ባደረግነው መሰረት ያልተገባ ቦታ እየዋሉ እንደሆነ ደርሰንበታል በዚሁ መሰረት በተለየ ሁኔታ ከዚህ በኋላ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በትምህርት ገበታችሁ ላይ ሳትገኙ የቀራቹ ተማሪዎች ፈተና ላይ የማናስቀምጥ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ👉 የትምህርት ቤት ወርሃዊ ውዝፍ ክፍያና የቅዳሜ ማጠናከሪያ ክፍያ ያለባቹ ተማሪዎች ክፍያ ሳታጠናቁ ፈተና ላይ የማትቀመጡ እንደሆነ ከወዲሁ እናሳውቃለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 01/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

Condensed Curriculum 6th Month (2).zip13.34 MB

ለኢቢ አካዳሚ ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ። ✅ሰኞ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ብሔራዊ ምርጫ ስለሆነ ት/ት የለም!! ✅ከማክሰኞ-ረዕቡ(ግንቦት 25 እና 26) የፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለሚሰራ ት/ት አይኖርም! ✅ሐሙስ ግንቦት 27/09/2018 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት የሚኖር ሲሆን ተማሪዎች እንደተለመደው ዩኒፎርም ፣የትምህርት መርጃ መሳሪያ ፣ምግባችሁና የመጠጥ ውኃ ይዛቹ የትምህርት ገበታቹ ላይ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ👉 የትምህርት ቤት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ ያለባቹ ተማሪዎች ከወዲሁ ክፍያችሁን ወደ ብርሃን ባንክ በመሄድ እድታጠናቅቁ እናሳስባለን ። 🇪🇹የኢቢ አካዳሚ የስራ አመራር ኮሚቴ             21/09/2018 ዓ.ም🇪🇹

ለኢቢ አካዳሚ ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ እንደሚታወቀው ሰኞ በ24/09/2018 ዓ.ም ሀገራዊ ምርጫ የሚካሄድበት ቀን ስለሆነ በዚህ መሰረት ት/ቤት ከሰኞ-ረቡዕ ለተማሪዎች ዝግ እንደሆነ እያሳወቅን ሀሙስ በ27/09/2018 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት የሚኖር ሲሆን ተማሪዎች እንደተለመደው ዩኒፎርም ፣የትምህርት መርጃ መሳሪያ ፣ምግባችሁና የመጠጥ ውኃ ይዛቹ የትምህርት ገበታቹ ላይ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ👉 የትምህርት ቤት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ ያለባቹ ተማሪዎች ከወዲሁ ክፍያችሁን ወደ ብርሃን ባንክ በመሄድ እድታጠናቅቁ እናሳስባለን ። 🇪🇹የኢቢ አካዳሚ የስራ አመራር ኮሚቴ             21/09/2018 ዓ.ም🇪🇹

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በ667 የፈተና ማዕከላት እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጻል፡፡   (ግንቦት 11/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል፡፡   የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት  የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።   ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡     ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።   በየክልሎች ፣ በከተማ አስተዳደሮች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።     ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል።

✔️ሞዴል ፈተና መፈተን የሚያስገኛቸው ጥቅሞች:- ✅1. ያላችሁን እውቀት መመዘን እና ድክመታችሁን መለየት፡ ሞዴል ፈተናዎች በእጃችሁ ያለውን እውቀት ምን ያህል እንደሆነ ለመገምገምና የትኞቹ አካባቢዎች ላይ የበለጠ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ እንድታውቁ ያግዛሉ። ✅ ለምሳሌ፣ አንድን ሞዴል ፈተና ከሰራችሁ በኋላ በተወሰኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ደጋግማችሁ እንደተሳሳታችሁ ከተመለከታችሁ፣ በእነዚያ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ጥናት ማድረግ ትችላላችሁ። ✅2.ከፈተና ጥያቄዎች እና የፈተና ሁኔታ ጋር መለማመድ፡ ሞዴል ፈተናዎችን መለማመድ የፈተና ጥያቄዎችን ቅርፅና አቀራረብ እንድታውቁ ይረዳችኋል። በተጨማሪም፣ በፈተና ጊዜ ሊያጋጥሟችሁ የሚችሉትን ጭንቀቶች ለመቀነስና ከፈተናው ሁኔታ ጋር እንድትላመዱ ያደርጋል። ✅3. የፈተና ጊዜ አጠቃቀም ክህሎትን ማሳደግ፡ ሞዴል ፈተናዎችን ስትሰሩ፣ ለእያንዳንዱ ጥያቄ ምን ያህል ጊዜ መመደብ እንዳለባችሁ ትማራላችሁ። ይህም በፈተናው ወቅት ጊዜያችሁን በአግባቡ እንድትጠቀሙበት ይረዳችኋል። ⭐️ ለምሳሌ፣ በአንድ ጥያቄ ላይ ብዙ ጊዜ እንደምታጠፉ ከተመለከታችሁ፣ በቀጣይ ፈተናዎች ላይ ጊዜያችሁን በአግባቡ ለመጠቀም ስልት መንደፍ ትችላላችሁ። ✅4. በራስ መተማመንን መጨመር እና የፈተና ላይ ጭንቀትን መቀነስ፡ በተደጋጋሚ ሞዴል ፈተናዎችን መስራት በራስ መተማመናችሁን ይጨምራል እንዲሁም በፈተና ጊዜ የሚሰማችሁን ጭንቀት ይቀንሳል። ✅በሞዴል ፈተናዎች ላይ ጥሩ ውጤት ስታገኙ፣ ለዋናው ፈተና የበለጠ በራስ መተማመን ይኖራችኋል። ✅5. የተማራችሁትን የማስታወስ እና የማስተዋል አቅምን መጨመር፡ ሞዴል ፈተናዎች የተማራችሁትን ነገር እንድታስታውሱና እንድትረዱ ያግዛሉ። ጥያቄዎችን ለመመለስ ስትሞክሩ፣ ቀደም ሲል ያጠኗችሁትን ርዕሰ ጉዳዮች በድጋሚ ታስታውሳላችሁ፣ ይህም ትምህርቱን በደንብ እንድትረዱት ያደርጋል። ✅6. የፈተና ጥያቄዎችን እና የተለያዩ የአጠያየቅ አይነቶችን ስልት ለማወቅ፡ ሞዴል ፈተናዎች የተለያዩ የጥያቄ አይነቶችን (ለምሳሌ፡ ምርጫ፣ እውነት ወይም ሐሰት፣ ወዘተ) እንድታውቁና ለእያንዳንዱ አይነት ጥያቄ እንዴት መልስ መስጠት እንዳለባችሁ እንድትረዱ ይረዳችኋል። ✅7. ትኩረት ማድረግ የሚያስፈልጉ ርዕሶችን እና አጠቃላይ ክለሳ ማድረግ ያለብንን ቦታዎች ለመለየት፡ ሞዴል ፈተናዎችን ከሰራችሁ በኋላ በየትኞቹ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እንደተሳሳታችሁ በመገምገም፣ በእነዚያ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ትኩረት ማድረግ ትችላላችሁ። ✅ይህም ለፈተናው ስትዘጋጁ የትኞቹ አካባቢዎች ላይ ማተኮር እንዳለባችሁ እንድታውቁ ይረዳችኋል። ✔️በአጠቃላይ፣ ሞዴል ፈተናዎችን መፈተን እውቀታችሁን ለመገምገም፣ ለፈተናው ሁኔታ ለመለማመድ፣ ጊዜያችሁን በአግባቡ ለመጠቀም፣ በራስ መተማመናችሁን ለመጨመር እና ለዋናው ፈተና በተሻለ ሁኔታ ለመዘጋጀት ጠቃሚ ነው::

ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ! የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ አድርጓል። ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከነገ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉ ተገልጿል።

የ2018 የ2ኛ መ/ዓመት የ12ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና ከግንቦት12-14/2018 ዓ.ም ስለሚሰጥ ተማሪዎች ከወዲሁ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ወላጆች ለልጆቻችሁ ድጋፍና ክትትል  እንድታደርጉላቸው እያሳሰብን👉 ውዝፍ የት/ቤት ወርሃዊ ክፍያ ያልከፈላችሁ ከወዲሁ እንድትከፍሉ በጥብቅ እናሳስባለን።         🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 2ኛ ደረጃ ከ9ኛ-12ኛ          07/09/2018 ዓ.ም🇪🇹

Condensed Curriculum 6th Month.zip13.34 MB

Mathematics Grade 10 Worksheet(Unit(1-7)) (2).pdf6.27 KB

የፈተና የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ‼️ የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል። በሌላ በኩል ፦ - የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ - የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም - የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም - የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ይሰጣል።

የፈተና የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ‼️ የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል። በሌላ በኩል ፦ - የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ - የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም - የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም - የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ይሰጣል።