es
Feedback
EB-ACADEMY ARADA.9-12 EDUCATION CHANNEL🇪🇹🇪🇹🇪🇹!!

EB-ACADEMY ARADA.9-12 EDUCATION CHANNEL🇪🇹🇪🇹🇪🇹!!

Ir al canal en Telegram

"An investment in knowledge pays the best interest" Benjamin Franklin...

Mostrar más
1 519
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
+230 días
Archivo de publicaciones
🇪🇹ለኢቢ አካዳሚ ኹ9ኛ-12ኛ ክፍል ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ በሙሉ ሰርተፍኬት ዚሚሰጥበት ቀን ነገ ቅዳሜ በቀን 27/10/2018 ዓ.ም እስኚ 6:00 መሆኑን እያሳወቅን ወላጆቜ ነገ ኹ2:30 ጀምሮ በት/ቀት ቅጥር ግቢ ኚልጆቻቜሁ ጋር ተገኝታቜሁ ሰርተፍኬት እድትወስዱ እናሳስባለን ። 👉ማሳሰቢያ:-ዚልጆቻቜሁን ሰርተፍኬት ዚምትወስዱት ዚትምህርት ቀት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ አጠናቃቜሁ መሆኑን ኚወዲሁ እናሳውቃለን ። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ                              26/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

🇪🇹በኢቢ አካዳሚ ኹ9ኛ-12ኛ ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ነገ ዚተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎቜ በጠዋት በተመደባቜሁበት መፈተኛ ጣቢያ ጠዋት 2:30 መድሚስ አለባቜሁ ስጚርሱ ወደ ት/ቀታቜሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። 👉ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎቜ 4:00 ሰዓት በት/ቀቱ ተገኝታቜሁ አድሚሜን ካርድ እንድትወስዱ። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 21/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

Update      ጥብቅ መልዕክት 👉እንዎት ቆያቜሁ ጥብቅ ማሳሰቢያ 👉1ኛ:- ዚፊታቜን ሰኞ ጠዋት 1:30 ዚተፈጥሮ ሳይንስ /Natural / 1st Round ላይ ዚተመደቡ ሁሉ ተማሪዎቜ በዹመፈተኛ ጣቢያ እንዲገኙና ዹፈተና ኊሚን቎ሜን እንዲወስዱ በጥብቅ ጥሪው እንዲተላለፍ 👉2ኛ:- ሰኞ ኚሰዓት 6:30 ዚተፈጥሮ ሳይንስ/Natural // 2nd Round  ዚተመደቡ ሁሉም ተማሪዎቜ ዹፈተና ኊሚን቎ሜን እንዲወስዱ በጥብቅ ጥሪው እንዲተላለፍ:: 👉3ኛ:- ተማሪዎቜ ኊሚን቎ሜን ዚሚወስዱት በ131 መፈተኛ ጣቢያ መሆኑን አውቃቜሁ ጥሪው ይተላለፍ ለምሳሌ:- በትምህርት ቀት፣በዩኒቚርሲቲዎቜ፣በአብርሆት፣በአድዋ፣በTVT ኮሌጅ ፣ በተግባሚ ዕድ ሌሎቜም በሁሉም መፈተኛ ጣቢያ።        ðŸ‘‰áˆ›áˆ³áˆ°á‰¢á‹«:- 1ኛ➡ ተማሪዎቜ ዚጠዋቱም ሆነ ዚኚሰዓቱም ላይ መታወቂያና አድሚሜን ካርድ ይዘው መምጣት አለባ቞ው እንዳይሚሱ ይነገር። 2ኛ➡ተማሪዎቜ ኊሚን቎ሜ ላይ መገኘት  አለባ቞ው። 3ኛ➡ዚማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎቜ  ኊሚን቎ሜን በሌላ ቀን ዚምናሳውቃቜሁ ይሆናል::

🇪🇹​ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞቜ ዹተዘጋጀ ዚመልካም ምኞት መልእክት ​ውድ ዚሀገራቜን ተስፋዎቜ፣ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ! ​ዚብዙ ዓመት ጥሚታቜሁ ውጀት ዚሚለካበት እና ለወደፊት ህይወታቜሁ መሰሚት ዚሚጣልበት ታላቁ ዚብሄራዊ ፈተና ጊዜ ደርሷል። እናንተ ዚቀተሰቊቻቜሁ ብቻ ሳይሆን፣ ዚሀገራቜን ትልቅ ተስፋ እና መጪው ጊዜ ተሚካቢዎቜ ናቜሁ። በምናደርገው ክትትልና ድጋፍ በኩል ዚእናንተን ብቃት በልበ ሙሉነት እናደንቃለንፀ በስኬታቜሁም ላይ ትልቅ እምነት ጥለናል። ይህ ፈተና እናንተን ዚሚፈትን ብቻ ሳይሆን፣ በትምህርት ቀት ቆይታቜሁ ዚገነባቜሁትን እውቀት፣ ተሰጥኊ እና ብስለት ዚምታሳዩበት ትልቅ መድሚክ ነው። ​ፈተናውን በአግባቡ ለመወጣት ካስቀመጥና቞ው መመሪያዎቜ ባሻገር፣ ዚሚኚተሉትን ነጥቊቜ በአእምሯቜሁ ይያዙፊ ​በራስ መተማመን ይኑራቜሁ፡ እስካሁን ድሚስ ያደሚጋቜሁት ዝግጅት እና ያካበታቜሁት እውቀት ለስኬታቜሁ በቂ ነው። ፈተናው ላይ ስትቀመጡ በራስ መተማመን እና በትኩሚት ስራቜሁን አኚናውኑ። ​ለዝርዝር መመሪያ ትኩሚት ስጡ፡ ​ለቮክኒክ ቜግሮቜ መሚጋጋትን ይላበሱ፡           ፈተናው ኩንላይን በመሆኑ ምክንያት ሊያጋጥሙ ዚሚቜሉ ዚኔትወርክ ወይም ዚመብራት መቆራሚጊቜ ቢኖሩ፣ በፍጹም አትደናገጡ። ተሚጋግታቜሁ ሁኔታውን በመጠባበቅ እና ለሚመለኚታ቞ው አካላት በማሳወቅ ፈተናቜሁን መቀጠል እንደምትቜሉ አስታውሱ።     ​ስሜታቜሁን ተቆጣጠሩ፡ መሚጋጋት ዚስኬት ቁልፍ ነው። ጭንቀት ኚተሰማቜሁ ጥልቅ ትንፋሜ በመውሰድ አእምሮአቜሁን በማሚጋጋት ወደ ፈተናቜሁ በሙሉ ትኩሚት ተመለሱ።    ​ስትራ቎ጂያዊ አቀራሚብ ይኑራቜሁ፡ ጊዜን በአግባቡ ማስተዳደር እና እርግጠኛ ያልሆናቜሁባ቞ውን ጥያቄዎቜ ለጊዜው በማለፍ ዚሚያውቋ቞ውን በመጀመሪያ መስራት ዚተሻለ ውጀት እንድታመጡ ይሚዳቜኋል።       ​ዚመጚሚሻ ፍተሻ፡ ፈተናውን ኚመጚሚሳቜሁ በፊት መልሶቻቜሁን በሙሉ በስርዓት መፈተሻቜሁን አሚጋግጡ። ​ዚእናንተ ስኬት ዚቀተሰቊቻቜሁ፣ ዚትምህርት ቀታቜሁ እና ዚሀገራቜን ኩራት ነው። እጅግ ተሚጋግታቜሁ፣ በአእምሮ ዝግጅት እና በጥንቃቄ ፈተናቜሁን እንድትወጡ መልካም ፈቃድና ምኞታቜን ነው። ​በድል ተወጡ።🇪🇹🇪🇹🇪🇹

+1
Natural - EB ACADEMY - Copy.xlsx0.18 KB

በኢቢ አካዳሚ ኹ9ኛ-12ኛ ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ነገ ዹሞክ ፈተናው ይቀጥላል ተማሪዎቜ በፕሮግራሙ መሰሚት ጠዋት ዚተፈጥሮ ሳይንስ ኚሰዓት ዚማህበራዊ ሳይንስ ሲሆን ሰዓት እንዳታሚፍዱ በካ቎ድራሉ ዚልጃገሚዶቜ ት/ቀት እንገናኛለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 18/10/2018 ዓ.ም🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በኢቢ አካዳሚክ ኹ9ኛ-12ኛ ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ በሙሉ ነገ በ18/10/2018 ዓ.ም ዚማትሪክ ፈተና በበይነ መሚብ (on line) በካ቎ድራል ዚልጃገሚዶቜ ት/ቀት ልምምድ ስለምታደርጉ ጠዋት ዚተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) በት/ቀቱ 2:00 እንድትገኙ ዚማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) ኚሰዓት በኋላ 7:00 በት/ቀቱ እንድትገኙ እያሳሰብን ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ አድሚሜን ካርድ(admission card) ይዛቹ መገኘት ይኖርባቜኋል ምክንያቱም በበይነ መሚብ (on line) ስትጠቀሙ በአድሚሜን ካርድ ቁጥር ስለሚገባ። 👉ማሳሰቢያ:- ሁሉም ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ዚተፈጥሮ ሳይንስና ዚማህበራዊ ሳይንስ ዩኒፎርም መልበስ ይኖርባቜሀል ዚት/ቀት መታወቂያና አድሚሜን ካርድ መያዝ እንዳለባቹ እናውቃለን ። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ               17/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

🇪🇹በኢቢ አካዳሚ ኹ9ኛ-12ኛ ክፍል ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ በሙሉ ነገ በ17/10/2018 ዓ.ም ዓብርሆት ቀተ መፅሀፍት (abrihot Library) ዚማትሪክ ፈተናን በተመለኹተ ገለፃ(Orientation) ስለሚሰጥ ሁሉም ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ 5 ሰዓት በት/ቀት ቅጥር ግቢ እንድትገኙ እናሳውቃለን። 👉ማሳሰቢያ:- ሁሉም ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ነገ ወደገለፃ(Orientation) ዚሚኬደው ኚት/ቀት ተገኝቶ በአንድ ላይ ስለሆነ ተማሪዎቜ እንደተለመደው ዩኒፎርም መለበስ አለበት ዚት/ቀት መታወቂያ መያዝ አለበት ። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ ጉለሌ ቅርንጫፍ 16/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

በኢቢ አካዳሚክ ኹ9ኛ-12ኛ ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ በሙሉ ኹነገ ጀምሮ ኹ16-18/10/18 ዓ.ም ድሚስ ዚምትሪክ ጥያቄዎቜ በበይነ መሚብ (on line) በት/ቀት ልምምድ ስለምታደርጉ አድሚሜን ካርድ(admission card) ይዛቹ መገኘት ይኖርባቜኋል ምክንያቱም በበይነ መሚብ (on line) ስትጠቀሙ በአድሚሜን ካርድ ቁጥር ስለሚገባ። 👉ማሳሰቢያ:- ዚተማሪዎቜ ወላጅ/አሳዳጊ ኹ9ኛ-12ኛ ክፍል ውዝፍ ዹ/ቀት ወርሃዊ ክፍያ ያለባቹ እንዲሁም ዹ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎቜ ሁላቜሁም ክፍያ ሳታጠናቁ መፈተኛ አድሚሜን ካርድ ዚማይሰጥ መሆኑን አውቃቹ ክፍያ እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 15/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

ዹ2018 ትምህርት ዘመን ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዚሚሰጥበትን ዹጊዜ ሰሌዳ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ አገልግሎት ዹ2018 ዚትምህርት ዘመን ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዚሚሰጥበትን ዹጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠሚት በኩንላይን (Computer-based Testing (CBT) ዹሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር ዹሚፈተኑ ሲሆን ኹአንደኛ እስኚ ሶስተኛ ዙር ዚተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞቜ ይፈተናሉ። ኚአራተኛ እስኚ ስድስተኛ ዙር ዚማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞቜ ዹሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወሚቀት ዹሚፈተኑ ተፈታኞቜ ዚተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ ዹሚፈተኑ ሲሆን ዚማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቚርሲቲ ውስጥ ዹሚፈተኑ ይሆናል።

🇪🇹በኢቢ አካዳሚ ኹ9ኛ-12ኛ ክፍል ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ዚመፅሄት ክፍያ በተኹፈተው ዚንግድ ባንክ አካውንት 2700 ብር ገቢ እንድታደርጉ እያሳሰብን ኚወዲሁ መልካም ፈተናና ውጀት እንመኛለን። 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 07/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

Condensed Physics curriculum.pdf5.29 KB

ዹፈተና ስጋት 2018 ዓ.ም ኢቢ-አ.docx4.20 MB

ለኢቢ አካዳሚ ኹ9ኛ-12ኛ ወላጆቜ አሳዳጊዎቜ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ኚቀት ወደትምህርት ቀት እንደሄዱ ነው ወላጅ ዚሚያውቀው ነገር ግን አንዳንድ ተማሪዎቜ ወደ ት/ቀት እዚመጡ እንዳልሆነ ክትትል ባደሚግነው መሰሚት ያልተገባ ቊታ እዚዋሉ እንደሆነ ደርሰንበታል በዚሁ መሰሚት በተለዹ ሁኔታ ኹዚህ በኋላ ዹ12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ በትምህርት ገበታቜሁ ላይ ሳትገኙ ዚቀራቹ ተማሪዎቜ ፈተና ላይ ዚማናስቀምጥ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ👉 ዚትምህርት ቀት ወርሃዊ ውዝፍ ክፍያና ዚቅዳሜ ማጠናኚሪያ ክፍያ ያለባቹ ተማሪዎቜ ክፍያ ሳታጠናቁ ፈተና ላይ ዚማትቀመጡ እንደሆነ ኚወዲሁ እናሳውቃለን። 🇪🇹ኢቢ አካዳሚ አራዳ ቅርንጫፍ 01/10/2018 ዓ.ም🇪🇹

Condensed Curriculum 6th Month (2).zip13.34 MB

ለኢቢ አካዳሚ ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ በሙሉ። ✅ሰኞ ግንቊት 24/2018 ዓ.ም ብሔራዊ ምርጫ ስለሆነ ት/ት ዹለም!! ✅ኹማክሰኞ-ሚዕቡ(ግንቊት 25 እና 26) ዹፈተና ዚቅድመ ዝግጅት ስራ ስለሚሰራ ት/ት አይኖርም! ✅ሐሙስ ግንቊት 27/09/2018 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት ዹሚኖር ሲሆን ተማሪዎቜ እንደተለመደው ዩኒፎርም ፣ዚትምህርት መርጃ መሳሪያ ፣ምግባቜሁና ዚመጠጥ ውኃ ይዛቹ ዚትምህርት ገበታቹ ላይ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ👉 ዚትምህርት ቀት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ ያለባቹ ተማሪዎቜ ኚወዲሁ ክፍያቜሁን ወደ ብርሃን ባንክ በመሄድ እድታጠናቅቁ እናሳስባለን ። 🇪🇹ዚኢቢ አካዳሚ ዚስራ አመራር ኮሚ቎             21/09/2018 ዓ.ም🇪🇹

ለኢቢ አካዳሚ ወላጆቜ/አሳዳጊዎቜ በሙሉ እንደሚታወቀው ሰኞ በ24/09/2018 ዓ.ም ሀገራዊ ምርጫ ዚሚካሄድበት ቀን ስለሆነ በዚህ መሰሚት ት/ቀት ኹሰኞ-ሚቡዕ ለተማሪዎቜ ዝግ እንደሆነ እያሳወቅን ሀሙስ በ27/09/2018 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት ዹሚኖር ሲሆን ተማሪዎቜ እንደተለመደው ዩኒፎርም ፣ዚትምህርት መርጃ መሳሪያ ፣ምግባቜሁና ዚመጠጥ ውኃ ይዛቹ ዚትምህርት ገበታቹ ላይ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ👉 ዚትምህርት ቀት ውዝፍ ወርሃዊ ክፍያ ያለባቹ ተማሪዎቜ ኚወዲሁ ክፍያቜሁን ወደ ብርሃን ባንክ በመሄድ እድታጠናቅቁ እናሳስባለን ። 🇪🇹ዚኢቢ አካዳሚ ዚስራ አመራር ኮሚ቎             21/09/2018 ዓ.ም🇪🇹