የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
رفتن به کانال در Telegram
2 602
مشترکین
+324 ساعت
+87 روز
+2430 روز
آرشیو پست ها
እንኳን ለአባቶቻችን ሐዋርያት ጾም (ጾመ ሐዋርያት) በሰላም አደረሰን!
በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን በአዋጅ ከምንጾማቸው ሰባቱ አጽዋማት መካከል ዛሬ የጀመርነው የሐዋርያት ጾም አንዱ ነው። ቅዱሳን አባቶቻችን በጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን በበዓለ ሃምሳ ከተቀበሉ በኋላ የአገልግሎታቸው መጀመሪያ ያደረጉት ጾምን ነው። ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በ30 ዘመኑ ለአገልግሎት በወጣ ጊዜ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ተጠምቆ በቀጥታ ወደ ገዳመ ቆሮንጦስ በመጓዝ ጾምና ጸሎትን የአገልግሎት መጀመሪያ እንድናደርገው በተግባር አስተምሮናል። ሐዋርያትም ይህንን መሰረት አድርገው ጾምና ጸሎትን የአገልግሎታቸው መነሻ አደረጉት።
ሐዋርያዊት የሆነችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህንን የሐዋርያት አሰር በመከተል የእነርሱን ጾም በስማቸው ሰይማ እኛም እንድንጾም ታስተምረናለች።
የቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት በረከት በሁላችን ላይ ይደር። መልካም የጾም ወቅት ያድርግልን!! አሜን።
+9
የበዓለ ጰራቅሊጦስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ ።
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባረገ በአስረኛው ቀን በተነሳ በሃምሣኛው ቀን ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች አምሳል የወረደበት በተዘጋ ደጃፍ የነበሩ ሐዋርያት ኃይል ያገኙበት ፣በአንድ ቀን ሶስት ሺህ ነፍሳት የተመለሱበት ታላቁ የቤተክርስቲያን የልደት ቀን በዓለ ጰንጠቆስጤ ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብራችን በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ የሐረርጌ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድሕን ንጉሴ የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ገ/ሥላሴ በላይ የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ ዋና አስተዳዳሪ፣ የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አዕምሮ ምስጋናው እና ሌሎችም የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት፣መምሕራን፣ የየሰንበት ት/ት ቤት አገልጋዮችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ጰራቅሊጦስ
'' ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ዘሠረጸ እም አብ ንስግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ ዘነበበ በነቢያት''
በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን እርሱም ጌታ ሕይወትን የሚሰጥ ከአብ የሠረጸ ከአብና ከወልድ ጋር በአንድነት እንሰግድለታለን እናመሰግነዋለን፤ እርሱም በነቢያት አድሮ የተናገረው ነው።
መንፈስ ቅዱስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ
ጰራቅሊጦስ:- ናዛዚ ፣ መጽንዒ፣ መስተፍሥሒ ፣ የሚያጽናና፣ የሚመክር፣ የሚረዳ፣ የሚታደግ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው።
ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ''እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ'' ብሎ ለሐዋርያቱ በሰጣቸው ቃል መሠረት በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሳ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን ልኮላቸዋል፡፡ ሁሉም በአንድ ቦታ ተሰባስበው ሳሉ ድንገት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ከሰማይ ወርዶ የነበሩበትን ቤት መላው የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎችም በሁሉም ላይ አረፉባቸው በዚህ ጊዜ ሁሉም መንፈስ ቅዱስ ባደላቸው መጠን በተለያዩ በየሀገሩ ቋንቋዎች ሁሉ ተናገሩ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላም በአእምሮ ጎለመሱ፤ ጥቡዓን ሆኑ፣ ፍርሃት ከውስጣቸው ተወግዶ መንፈሳዊ ድፍረት አግኝተዋል፤ ጽኑዓን ኾነዋል፤ ሰማያዊ ሀብት ዕውቀትና ጸጋን ታድለዋል።
በዚህ ዕለት ሐዋርያት በተገለጠላቸው ቋንቋ ሲያስተምሩ ተቃዋሚ አይሁዳውያን ''ጉሽ ጠጅ ጠጥተው ሰክረው የሆነ ያልሆነውን ይቀባጥራሉ'' እያሉ ሐዋርያትን አሟቸው ቅዱስ ጴጥሮስም ሰክረዋል የምትሉ እናንተ እንደምትሉት አይደለም፡፡ ጊዜው ማለዳ ሰዓቱም ገና ጠዋት ሦስት ሰዓት ነው
ይልቁኑ እናንተ በተንኮል ሰቅላችሁ የገደላችሁት ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የተነሳው ኢየሱስ ክርስቶስ ማረጉንና ዳግም በክብር በምስጋና መጥቶ በሕያዋንና በሙታን ላይ የሚፈረድ መሆኑን በአይሁድ ፊት አሰምቶ ተናገረ፡፡በቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተማረኩ አሕዛብም ከክፋታቸው ተመልሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመኑ በዚያች ብቻ ሰዓት ሦስት ሺህ ሕዝብ በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ተመልሰዋል ዕለቱም የቤተክርስቲያን የልደት ቀን ይባላል።
ከሶስቱ አካላት አንዱ የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ጠብቆት አይለየን የቅዱሳን ሐዋርያት ረድኤታቸው በረከታቸው ይደርብን አሜን።
ጰራቅሊጦስ
“ጰራቅሊጦስ” የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ ለኾነው ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስሙ ሲኾን፣ ትርጕሙም መጽንኢ (በእምነት የሚያጸና)፣ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ)፣ ናዛዚ (ያዘኑትን የሚያረጋጋ)፣ መስተፍስሒ (የተጨነቁትን የሚያስደስት)፣ ከሣቲ (ምስጢርን የሚገልጽ) ማለት ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን ”እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ” አላቸውና ዐረገ፡፡ ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ በኢየሩሳሌም ከተማ በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ኾነው በጾምና በጸሎት ይተጉ ነበር፡፡ በሚያርግበት ጊዜም ለሐዋርያቱ በገባላቸው ቃል መሠረት ተሰብስበው በአንድነት ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዐረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን የጰራቅሊጦስ እለት ጧት በሦስት ሰዓት እንደ ዐውሎ ነፋስ ያለ ድምፅ ድንገት ከሰማይ መጣና የነበሩበትን ቤት ሞላው፡፡ ከዚያም እንደ እሳት የተከፋፈሉ የእሳት ላንቃዎች በኹሉም ላይ ተቀመጡባቸው፡፡
https://youtu.be/89NGmkNBgX4?si=ZbCkLomEs6Jq_Vwq
እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በሰላም አደረሳችሁ!!!
የበዓለ ጰራቅሊጦስ ዝማሬ
(በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅ/ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት)
የስሙ ምስክር
የስሙ ምስክር ያደረጋችሁ
ሐዋርያት ድንቅ ነው ግብራችሁ
ሐዋርያት ተገልጧል ክብራችሁ
ሑሩ ወመሀሩ ተብላችኋልና
እንዲሰማ ቃሉ የመንግሥቱ ዜና
አይታችኋልና የእጆቹን ተአምራት
ሰበካችሁ ለዓለም የመዳንን ብሥራት
መከራ መስቀሉን እንድትታገሱ
በበዓለ ሃምሳ ቃኝቷችሁ መንፈሱ
በአምሳለ እሳት ልሳናት ተከፍተው
አሕዛብ ተመለሱ በወንጌሉ አምነው
በዓለም ተነቦ ፊደል ሕይወታችሁ
በአንድ ቃል በአንድ ሐሳብ ታትሞ ልባችሁ
መሞት መነሣቱን ማረጉን ክርስቶስ
በበዓለ ሃምሳ ተሰብኳል በጴጥሮስ
የወንጌልን መረብ በእምነት ጥላችሁ
ለተጨነቀች ነፍስ ሰላምን ሰብካችሁ
የክርስቲያኖች ቤት በዓለም ተተክላ
ይኸው ታበራለች በክርስቶስ አምና
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
ግንቦት 20/2018 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ እህታችን ሣራ ተዘራ እና ወንድማችን ሱራፌል መዝገበ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
