fa
Feedback
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

رفتن به کانال در Telegram

ለአስተያየት ለጥያቄ በግል ለማውራት @abigezenige ይህን ይጠቀሙ። ሐምሌ 27/11 ዓ᎐ም

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

کانال አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ (@abizeeotc) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 323 مشترک است و جایگاه 7 152 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 717 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 323 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -259 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -18 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 16.06% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.34% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 979 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 782 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ለአስተያየት ለጥያቄ በግል ለማውራት @abigezenige ይህን ይጠቀሙ። ሐምሌ 27/11 ዓ᎐ም

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

12 323
مشترکین
-1824 ساعت
-617 روز
-25930 روز
آرشیو پست ها
ቅዳሴ ስታስቀድሱ የሚመጣው ጣፋጭ እንቅልፍ ከእግዚኦታ በኋላ ድራሽ አባቱ ይጠፋል። ቅዳሴ ላይ እንቅልፍ የሚመጣባችሁ.... ተሰጥኦ ስለማትመልሱ ነው። ኑ ተሰጥኦ መማማሪያ ግሩፕ ይግቡ @abizeeotckidase

የነሐሴ 21 ቀን (እርፈታ ለዕግዝእትነ ማርያም) የነግህና የቅዳሴ ግጻዌ ምንባባት፣ ምስባክና ወንጌል ✝️ የነሐሴ 21 ግጻዌ (የቀኑ ምንባባት) 🌅 የነግህ (የኪዳን) * ምስባክ፦ መዝሙር 44:9-1
የነሐሴ 21 ቀን (እርፈታ ለዕግዝእትነ ማርያም) የነግህና የቅዳሴ ግጻዌ ምንባባት፣ ምስባክና ወንጌል ✝️ የነሐሴ 21 ግጻዌ (የቀኑ ምንባባት) 🌅 የነግህ (የኪዳን) * ምስባክ፦ መዝሙር 44:9-10 > ግዕዝ፦ "ወትቀውም ንግሥት በየማንከ፤ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኍብርት፤ ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ እዝነኪ።" > ትርጉም፦ "በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸልማ ንግሥቲቱ በስተቀኝህ ትቆማለች፤ ልጄ ሆይ፥ ስሚ፤ እዪ፤ ጆሮሽን ወደ እኔ አዘንብዪ።" * ወንጌል፦ የሉቃስ ወንጌል 1:39 - 47 📖 የቅዳሴ መልእክታት * የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 7:25 - ፍጻሜ * የሐዋርያው ዮሐንስ መልእክት፦ 2ኛ ዮሐንስ 1:1 - 6 * የሐዋርያት ሥራ፦ ሐዋርያት ሥራ 16:13 - 18 🎼 የቅዳሴ ምስባክ > መዝሙር 44:9-10 > ግዕዝ፦ > "አዋልደ ነገሥት ለክብርከ፤ ወትቀውም ንግሥት በየማንከ፤ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኍብርት።" > ትርጉም፦ > "የነገሥታት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸልማ፤ ንግሥቲቱ በስተቀኝህ ትቆማለች።" ☦️ ወንጌልና ቅዳሴ * ወንጌል፦ የማቴዎስ ወንጌል 25:1 - 19 * ቅዳሴ፦ ቅዳሴ ማርያም አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

በሱባኤው ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 35ኛ ዙር በገና የሚያሸልመው እጣ አሁን ቀጥሏል። ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ቀርተዋል 60 ሰው በ200 ብር ከ1 እስከ 60 ቁጥር ቀድሞ ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በ
በሱባኤው ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 35ኛ ዙር በገና የሚያሸልመው እጣ አሁን ቀጥሏል። ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ቀርተዋል 60 ሰው በ200 ብር ከ1 እስከ 60 ቁጥር ቀድሞ ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በመምረጥ Awash👉🏦 013200909837300 CBE👉🏦 1000510909635 BOA👉🏦 47056497 Tele birr👉🏦 0933143133   አቤኔዘር ገዛኸኝ ብለው ከፍለው ስም ስልክ ሪሲት t.me/abigezenige ላይ ይላኩ። አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ያልተያዙ ቁጥሮች 31 32 38 39 41 50 51 53 54 55 58 59 60

የፊታችን እሁድ መተት ወደማይታደስባት ቃልኪዳን ወዳለው ጊሺ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ቤ/ክ እና ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ለንግስ የአዳር እና ደርሶ መልስ ጉዞ ተዘጋጅቷል። 0933143133

35ኛ ዙር በገና የሚያሸልመው እጣ ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ቀርተዋል 60 ሰው በ200 ብር ከ1 እስከ 60 ቁጥር ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በመምረጥ Awash👉🏦 013200909837300 CBE👉�
35ኛ ዙር በገና የሚያሸልመው እጣ ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ቀርተዋል 60 ሰው በ200 ብር ከ1 እስከ 60 ቁጥር ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በመምረጥ Awash👉🏦 013200909837300 CBE👉🏦 1000510909635 BOA👉🏦 47056497 Tele birr👉🏦 0933143133 አቤኔዘር ገዛኸኝ ብለው ከፍለው ስም ስልክ ሪሲት t.me/abigezenige ላይ ይላኩ። አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ያልተያዙ ቁጥሮች 31 32 38 39 41 51 53 54 55 58 59 60 አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

በሱባኤው ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 35ኛ ዙር በገና የሚያሸልመው እጣ አሁን ቀጥሏል። ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ቀርተዋል 60 ሰው በ200 ብር ከ1 እስከ 60 ቁጥር ቀድሞ ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በ
በሱባኤው ምክንያት ተቋርጦ የነበረው 35ኛ ዙር በገና የሚያሸልመው እጣ አሁን ቀጥሏል። ጥቂት ቁጥሮች ብቻ ቀርተዋል 60 ሰው በ200 ብር ከ1 እስከ 60 ቁጥር ቀድሞ ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በመምረጥ Awash👉🏦 013200909837300 CBE👉🏦 1000510909635 BOA👉🏦 47056497 Tele birr👉🏦 0933143133   አቤኔዘር ገዛኸኝ ብለው ከፍለው ስም ስልክ ሪሲት t.me/abigezenige ላይ ይላኩ። አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ያልተያዙ ቁጥሮች 30-33 35 36 38-41 49-51 53-55 57-60

ቅዱስ ቁርባን በተቀበሉበት ቀን ሥጋ መብላት ሃጢአት ሆኖ ሳይሆን ምናልባት ጥርሳችን ውስጥ ሊቀር ስለሚችል እና አጥንትም ሊኖረው ስለሚችል ባይበላ ይመከራል። በዕለቱ ከአፍ የሚወጣ ምንም ነገር ክልክል ነው።

የነሐሴ 16 (የእመቤታችን የዕርገት በዓል) የነግህና የቅዳሴ ግጻዌ ንባባት እና ትርጉም የሚከተለው ነው፦ ዘነግህ ምስባክ (መዝሙር 44:9-10) ግዕዝ፦ ወትቀውም ንግሥት በየማንከ ። በአልባሰ ወርቅ
የነሐሴ 16 (የእመቤታችን የዕርገት በዓል) የነግህና የቅዳሴ ግጻዌ ንባባት እና ትርጉም የሚከተለው ነው፦ ዘነግህ ምስባክ (መዝሙር 44:9-10) ግዕዝ፦ ወትቀውም ንግሥት በየማንከ ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኍብርት ። ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወኣጽምዒ እዝነኪ ። ትርጉም፦ ንግሥቲቱ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸሞንሙና በቀኝህ ትቆማለች። ልጄ ሆይ፥ ስሚ፤ እዪ፤ ጆሮሽንም አዘንብዪ። ወንጌል፦ ሉቃስ 1:39-47 የቅዳሴ ንባባት ሐዋርያት (ዲያቆን)፦ ፊልጵስዩስ 3:1-15 ካቶሊካዊት (ንፍቅ ዲያቆን)፦ 1 ጴጥሮስ 4:12-ፍጻሜ ግብረ ሐዋርያት (ንፍቅ ካህን)፦ የሐዋርያት ሥራ 9:1-8 ምስባክ (መዝሙር 117:18-19) ግዕዝ፦ ገሥፆሰ ገሠፀኒ እግዚአብሔር ። ወለሞትሰ ባሕቱ ኢመጠወኒ :: አርኀዉ ሊት አናቅጸ ጽድቅ ። ትርጉም፦ እግዚአብሔር ተቈጥቶ ገሠጸኝ፤ ነገር ግን ለሞት አላሳልፎ አልሰጠኝም። የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ። ወንጌል፦ ዮሐንስ 15:12-26 ቅዳሴ፦ ቅዳሴ ማርያም

ነገ ወደ ሰሚነሽ ኪዳነምህረት ገዳም ደርሶ መልስ ጉዞ አለን። መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ መገናኛ ጣፎ 12:00 0933143133

ነገ የእመቤታችን ቅድስት ኪዳነምህረት በዓል ከእኔ ጋር መዘከር የምትፈልጉ እንደለተመደው ድፎ ዳቦ እንዘክራለን። 1000145090176 አቤኔዘር የቻላችሁትን በማዋጣት አብረን እንዘክር። ሙሉ ዳቦ 1200 ብር

✝️ የነሐሴ 15 ግጻዌ (የቀኑ ምንባባት) 📖 መልእክታት የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 12:18 - ፍጻሜ የሐዋርያው ይሁዳ መልእክት፦ የይሁዳ መልእክት 1:17 - ፍጻሜ የሐዋርያት ሥ
✝️ የነሐሴ 15 ግጻዌ (የቀኑ ምንባባት) 📖 መልእክታት የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 12:18 - ፍጻሜ የሐዋርያው ይሁዳ መልእክት፦ የይሁዳ መልእክት 1:17 - ፍጻሜ የሐዋርያት ሥራ፦ ሐዋርያት ሥራ 12:1 - 15 🎼 ምስባክ መዝሙር 18:4-5 ግዕዝ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ፤" "ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ፤" "ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ።" ትርጉም፦ "ነገር የለም ንግግርም የለም ድምፃቸው የማይሰማበት፤" "ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ ወጣ፤" "ቃላቸውም እስከ ዓለም አጽናፍ ደረሰ።" ☦️ ወንጌልና ቅዳሴ ወንጌል፦ የማቴዎስ ወንጌል 10:1 - 15 ቅዳሴ፦ ቅዳሴ ሐዋርያት አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

መንበሩ ነዋኅ ወብሩህ ያለውን ይህን ባለመንበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ተርጉሞብሃል ብሎ ረትቶበታል በዚህ ጊዜ እሱን ተከራክረው ረትተው አውግዘው ለይተው ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ብለው ጨምረውበታል፡፡ ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኲሉ ጉባዔ ዘሐዋርያት፡፡ ሐዋርያት ባነጽዋት ከምኲራበ አረሚ ከምኲራበ አይሁድ በላይ በምትሆን ክብርት ንጽሕት ጽንዕት ልዩ በምትሆን ባንዲት ቤተክርስቲያን እናምናለን ሐተታ አሐቲ አለ በወርቅ በብር በጭቃ በጨፈቃ ቢሠራ በግብጽ በእስክንድርያ በጻድቃን በሰማዕታት በእመቤታችን ስም ቢሠራ አንድ ነውና በወርቅ በብር የተሠራ ቤተክርስቲያን ሥጋውን ደሙን ይለውጣል በጭቃ በጨፈቃ የተሠራ ቤተክርስቲያን ሥጋውን ደሙን አይለውጥም አያከብርም ብለዋልና አሐቲ አለ አንድም ሐዋርያት ያስተማሯት ያሳመኗት ያጠመቋት ከምዕመናነ አሕዛብ በላይ የምትሆን ክብርት ንጽሕት በምትሆን ባንዲት ምዕመን እናምናለን፡፡ ሐተታ አሐቲ አላቸው ምዕመናንን አንድ እምነት ያምናሉ አንድ ጥምቀትይጠመቃሉ አንድ ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉና አንድም ምዕመንን በሚያስተምሩ ባንድ መምህራን እናምናለን፡፡ ሐተታ መምህራንን አሐቲ አላቸው አንድ እምነት ያሳምናሉ አንድ ትምህርት ያስተምራሉ፡፡ አንድ ሥጋውን ደሙን ያቀብላሉና፡፡ አንድም በቤተክርስቲያን ምዕመናንን በሚያስተምሩ ባንድ በመምህራን እናምናለን፡፡ ሐተታ ሲያስተምሩ ሲያሳምኑ ሲያጠምቁ በቤተክርስቲያን ነውና ቅድስትን እንደ ሃይማኖተ አበው አትት፡፡ ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት፡፡ ኃጢአት በሚሠረይባት ባንዲት ጥምቀት እናምናል፡፡ ሐተታ በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም ቢጠመቁ አንድ ነውና በዐርባ ቀን በሰማንያ ቀን በዐርባ ዘመን በሰማንያ ዘመን ቢጠመቁ አንድ ነውና፡፡ እንድም በሊቀ ጳጳስ በጳጳስ በኤጲስ ቆጶስ በቄስ እጅ ቢጠመቁ አንድ ነውና አንድም በዐቢይ ባሕር በማዕከላዊ ባሕር በንዑስ ባሕር ቢጠመቁ አንድ ነውና ፡፡ ወንሴፎ ትንሣኤ ሙታን፡፡ ከፈረሱ ከበሰበሱ በኋላ አካል አግኝተው ታድሰው ሙታን እንዲነሡም እናምናለን አንድም አንዘ ንሴፎ ይላል ሙታን እንዲነሡ አምነን ባንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡ ሐተታ ማጥመቅ ትንሣኤ ሙታን ካሳመኑ በኋላ ነውና ወሕይወተ ዘይመጽእ ለዓለመ ዓለም፡፡ ሐይው ከመ መላእክት እንዳለ እናምናለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

ጸሎተ ሃይማኖት አንድምታ ትርጓሜ ሊቃውንት እንደተረጎሙት ነአምን በ፩ዱ አምላክ፡፡ በባሕርይ በሕልውና ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ አንድ አምላክ በሚሆን እግዚአብሔር አብ፡፡ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን፡፡ አኃዜ ኲሉ ገባሬ ሰማያት ወምድር፡፡ ሁሉን የሚገዛ፡፡ አንድም ሁሉን የፈጠረ እግዚኦ አኃዜ ኲሉ ዓለም እንዲል፡፡ አንድም ሁሉን እንደ ጥና እንደ እንቁላል በመሐል እጁ የያዘ፡፡ ሰማይን ምድርን የፈጠረ ሰማየ ሰማያት ለእግዚአብሔር ብሎ ምድረሰ በሀበ ለእጓለ እመሕያው ካለው ሲለይ፡፡ አንድም ኢትፍርህዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ ካለው ሲለይ አንድም መላእክትን ደቂቀ አዳምን የፈጠረ ዘያስተርኢ ወዘኢያስተርኢ፡፡ የሚታየውን ግዙፋኑን የማይታየውን ረቂቁን የፈጠረ፡፡ ዘያስተርኢ ሐተታ፡፡ የሚታየው ግዙፋኑ ወዘኢያስተርኢ የማይታዩት ረቂቃኑ በርኅቀት በርቀት፡፡ በርኅቀት አድማስ ናጌብ ብሄሞት ሌዋታን በርቀት ነፍሳት ነፋሳት መላእክት ናቸው አንድም ዘያስተርኢ በዘፈቀደ የሚገለጥ ወዘኢያስተርኢ፡፡ በባሕርዩ የማይገለጥ አንድም ለበቁት የሚገለጥ ላልበቁት የማይገለጥ፡፡ አንድም ዘይርኢ ወዘኢያስተርኢ ይላል ፡፡ የሚጠብቅ ሲጠብቅ የማይታይ፡፡ ወነአምን በ፩ዱ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ በተለየ አካሉ አንድ በሚሆን አንድም በባሕርይ በሕልውና ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ አንድ በሚሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን፡፡ ወልደ አብ ዋሕድ፡፡ ተቀዳሚ ተከታይ በሌለው የአብ የባሕርይ ልጁ በሚሆን፡፡ ዘህልው ምስሌሁ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም፡፡ ዓለም ሳይፈጠር በሱ ሕልውና፡፡ አንድም ከሱ ጋራ እንደሱ በነበረ፡፡ ብርሃን ዘእምብርሃን፡፡ ከብርሃን ከአብ በተገኘ በብርሃን በወልድ፡፡ አምላክ ዘእምአምላክ ዘበአማን፡፡ ከባሕርይ አምላክ ከአብ በተገኘ በባሕርይ አምላክ በወልድ፡፡ ዘተወልደ ወአኮ ዘተገብረ፡፡ በተወለደ ወአኮ ዘተገብረ ባልተፈጠረ፡፡ ሐተታ አርዮስ ሸክላ ሠሪ መሥሪያውን ሠርታ እንድትሠራ ደበናንሳ መዶሻውን ሠርቶ ዘመደ ሐፃውንትን እንዲሠራ ፈጥሮ ፈጠረበት ይላልና ወአኮ ዘተገብረ አለ፡፡ ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፡፡ በሥልጣን በጌትነት በባሕርይ ከአባቱ ጋራ አንድ በሚሆን፡፡ ዘቦቱ ኲሉ ኮነ፡፡ ሁሉ በእርሱ ቃልነት በእሱ ህልውና የተፈጠረ ወዘእንበሌሁሰ አልቦ ዘኮነ፡፡ ያለሱ ቃልነት ያለሱ ህልውና የተፈጠረ የሌለ፡፡ ወኢምንትኒ፡፡ ምንም የተፈጠረ የሌለ፡፡ ሐተታ አርዮስ ፈጥሮ ፈጠረበት ይላልና ወኢምንትኒ አለበት፡፡ ዘበሰማይኒ ወዘበምድርኒ፡፡ በሰማይ ያሉ ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት መላእክት በምድር ያሉ ዕፀው አዕባን እንስሳት አራዊት ሰውም ቢሆን ያለሱ የተፈጠረ ምንም የሌለ፡፡ ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ዘበእንቲአነና ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት ፩ድ ወገን ስለእኛ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ፡፡ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ፡፡ ወተሰብአ እመንፈስ ቅዱስ ይላል አብነት እም፡ በ፡ ነው በግብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ሐተታ የከፈለ ያነፃ ያዋሐደ መንፈስ ቅዱስ ነውና ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፡፡ እም እና እም አንድ ወገን ነው እመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው የሆነ፡፡ አንድም መንፈስ ቅዱስ ከመክፈሉ የተነሣ እመቤታችን ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ ከማለቷ የተነሣ ሰው የሆነ፡፡ ኮነ ብእሴ፡፡ የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሆነ፡፡ ወአመ ኮንኩ ብእሴ አውሰብኩ ብእሲተ ከመ ኲሉ ሰብእ እንዲል፡፡ ወተሰቅለ በእንቲአነ በመዋዕለ ጲላጦስ ጰንጤናዊ፡፡ የጳንጦስ ሰው ጲላጦስ ነግሦበት በነበረ ወራት ስለእኛ የተሰቀለ፡፡ ሐተታ፡፡ እንደ ሰማዕታት ዕሤት ሽቶ እንደ ሌባ እንደ ወምበዴ ስቶ አይደለምና በእንቲአነ አለ፡፡ ሐመ ወሞተ፡፡ ስለእኛ መከራ ተቀብሎ ሞተ፡፡ ወተቀብረ ተቀበረ፡፡ ወተንሥአ እሙታን አመ ሣልስት ዕለት በከመ ጽሑፍ ውስተ ቅዱሳት መጻሕፍት፡፡ ንጹሐት ክቡራት በሚሆኑ መጻሕፍት እንደተጻፈ በሦስተኛው ቀን ተነሣ ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ እሁብ እኩያነ ህየንተ ሞቱ ወአብዕልተ ህየንተ መቅበርቱ ወልድየ ዕርግ እምህዝዓትከ ተብሎ እንደተጻፈ አንድም በከመ ጽሑፍ ዓርገ ይላል፡፡ ዓርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፡፡ በብርሃን በቅዳሴ በክብር በሥልጣን ዐረገ፡፡ ወነበረ በየማነ አቡሁ፡፡ ባባቱ ዕሪና ኖረ፡፡ ሐተታ፡፡ ንጉሥ የተጣላውን ሰናፊል አትታጠቅ በትር አታንሣ እንዲህ ካለ ቦታ አትውጣ ብሎ ቦታ እንዲወስንበት ቦታ ወሰነበት ማለት አይደለም፡፡ በምልዓት ሲል ነው እስመ ብሂለ የማን ይመርኅ ኀበ ተዋሕዶቶሙ በክብር እንዲል ነበረ የእንግድነት የማን የባለቤትነት ነው፡፡ አንድም ነበረ የባለቤትነት ነው፡፡ እንግዳን ንበር ይሉታል እንጅ ነበረ ይሉታልን፡፡ ዳግመ ይመጽእ በስብሐት፡፡ ዳግመኛ በብርሃን በሥልጣን በቅዳሴ ይመጣል፡፡ ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ፡፡ በሕያዋን በሙታን ይፈርድ ዘንድ አንድም ሕያዋንን ሙታንን ይገዛ ዘንድ ፡፡ ሐተታ ሕያዋን ያላቸው ጻድቃን ናቸው በነፍስ ሕያዋን ናቸውና አንድም በነፍስ ሕያዋን የሚሆኑበትን ሥራ ይሠራሉና አንድም የሕያው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ናቸውና ሙታን ያላቸው ኃጥአን ናቸው በነፍስ ሙታን ናቸውና አንድም በነፍስ ሙታን የሚሆኑበትን ሥራ ይሠራሉና አንድም የምውት የዲያብሎስ ማደሪያ ናቸውና አንድም ኃጥአንን ሕያዋን አላቸው ጸላእትየሰ ሕያዋን ወይኄይሉኒ እንዲል በዚህ ዓለም ሕያዋን ናቸውና ጻድቃንን ሙታን አላቸው ምውት አነ በኀበ ዓለም ወዓለምኒ ምውት በኀቤየ እንዲል የሹትን አያገኙትምና አንድም ኃጥአንን ሕያዋን ሙታን አላቸው ሕያዋን እስከዕለተ ምጽአት ሙታን ከዕለተ ምጽአት በኋላ አንድም ሕያዋን አላቸው በዚህ ዓለም ሙታን አላቸው በወዲያው ዓለም አንድም ሕያዋን አላቸው በሥጋ ሙታን አላቸው በነፍስ አንድም ጻድቃንን ሕያዋን ሙታን አላቸው ሙታን አላቸው እስከዕለተ ምጽአት ሕያዋን አላቸው ከዕለተ ምጽአት በኋላ አንድም ሙታን አላቸው በሥጋ ሕያዋን አላቸው በነፍስ አንድም ሙታን አላቸው በዚህ ዓለም ሕያዋን አላቸው በወዲያው ዓለም፡፡ ወአልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ፡፡ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም ሐተታ፡፡ ዳዊት ሰሎሞን ቢገዙ ዐርባ ፤ ዐርባ ዘመን ነው ያውም እስከ ዳን እስከ ቤርሳቤህ ነው የሱ ግን ፍጻሜ የለውምና፡፡ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ እግዚእ ማኅየዊ፡፡ የባሕርይ ገዢ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን፡፡ ዘሠረፀ እምአብ፡፡ ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የሠረፀ፡፡ ንስግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ፡፡ ከአብ ከወልድ ጋራ እንስገድለት እንደ አብ እንደ ወልድ እናመስግነው፡፡ ዘነበበ በነቢያት፡፡ ምስለ አብ ወወልድ ዘነበበ በነቢያት ብለህ ግጠም ከአብ ከወልድ ጋራ በነቢያት አድሮ የተናገረ ንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ ከአብ ከወልድ ጋራ እናመስግነው፡፡ ታሪክ ከጉባዔ ኒቅያ እስከ ጉባዔ ቍስጥንጥንያ ሃምሳ አምስት ዓመት ነው በዚህ ጊዜ መቅዶንዮስ ለአብ መንበር እንዳለው እግዚአብሔርሰ ይነብር ዲበ መንበሩ ቅዱስ ተብሎ ተነግሯል ለወልድ መንበር እንዳለው መንበርከ እግዚኦ ለዓለመ ዓለም ተብሎ ተነግሯል ለመንፈስ ቅዱስ ግን መንበር እንዳለው የተነገረበት ቦታ የለምና ሕፁፅ ነው ብሎ ተነሣ ንጉሡ ዘየዓቢ ቴዎዶስዮስ ነው በቍስጥንጥንያ ጉባዔ ይሁን ብሎ አዋጅ ነገረ በዚህ ምክንያት መቶ ሃምሳ ሊቃውንት ተሰብስበዋል አፈ ጉባዔው ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪት ነው ኢይቤ ሠናየ ይቤ አብ ኢይቤ ሠናየ ይቤ ወልድ አላ ይቤ፤ ይቤ ሰናየ መንፈስ ቅዱስ በአፈ ሲሳይያስ ነቢይ በዓመተ ሞተ ዖዝያን ንጉሥ ርኢክዎ ለእግዚአብሔር እንዘ ይነብር ዲበ

የአባታችን ሆይ ጸሎት አድምታ ትርጓሜ ፍች አቡነ ዘበሰማያት: ሐዋሪያት ወደ ጌታችን ቀርበው የምንጸልየውን ጸሎት አስተምረን አሉት። ጌታችንም " እናንተስ ስትጸልዩ የሰማይ አባታችን በሉኝ " በማለት
የአባታችን ሆይ ጸሎት አድምታ ትርጓሜ ፍች አቡነ ዘበሰማያት: ሐዋሪያት ወደ ጌታችን ቀርበው የምንጸልየውን ጸሎት አስተምረን አሉት። ጌታችንም " እናንተስ ስትጸልዩ የሰማይ አባታችን በሉኝ " በማለት ማንም ቢሆን ሲቆምና ሲቀመጥ: ሲተኛና ሲነሣ ዘወትር ሊጸልየው የሚችለውን አጭር ጸሎት አስተማረ። ማቴዎስ 6:9-14 ይኸንንም ጸሎት " ኪዳነ ጽድቅ የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል ማብራሪያ " ከሚለው መጽሐፍ ላይ ያገኘሁትን ከታች አቅርቤዋለሁ ያንብቡት። * አባታችን ሆይ :- ጌታችን ከግብርናተ ዲያብሎስ / ከዲያብሎስ ባርነት / ነፃ እንዳወጣን: አጥተነው የነበረውን ልጅነት እንዳገኘን ሲያጠይቅ አቡነ / አባታችን / በሉኝ አለ። ጌታ ሎሌውን: መምህር ደቀመዝሙሩን ምን ቢወደው ያበላዋል: ያጠጣዋል: የልቡናውን ምስጢር ያጫውተዋል እንጂ ርስቱን አያወርሰውም። ርስቱን የሚያወርሰው ለልጁ ነው። እርሱ ግን ጌታችን እና አምላካችን ሲሆን የማታልፍ ርስት መንግሥተ ሰማያትን የሚያወርሰን ስለሆነ ' አቡነ ' በሉኝ አለ። አባት ለወለደው ልጁ እዲራራ የሚራራልን ስለሆነ አቡነ በሉኝ አለ። * በሰማያት የምትኖር :- እንዲህ ማለቱ ራሱን ከምድራዊ አባት ሲለይ ነው። ምድራዊ አባት ሲወልድ በግዙፍ ሲያሳድግ በግዙፍ ነው። ኃላም ሓላፊ ርስቱን ያወርሳል። እርሱ ግን ሲወልደን በረቂቅ: ሲያሳድገን በረቂቅ ነው። ኃላም የማታልፍ ርስቱን መንግሥተ ሰማይን ያወርሰናል። በተጨማሪም ጌታ በሁሉ ምሉዕ ሲሆን ስለ ልዕልናው በሰማይ የምትኖር ይባላል። 1ኛ ጴጥሮስ 1:8-10 ዮሐንስ ራዕይ 21:2-6። *ስምህ ይቀደስ :- ይኸም " ስሜ መሐሪና ይቅር ባይ ነው። " ያልኸው ይጽናልን: መላእክት ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ ብለው ስምህን አመስግነው ቅድስናህን ተሳትፈው እንዲኖሩ: እኛም ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ ብለን አመሰገንህ ቅድስናህን ተሳትፈን እንድንኖር አድርገን በሉ ሲለን ነው። ኢሳያስ 6:3 ዮሐንስ ራዕይ 4:8። *መንግሥትህ ትምጣ :- መንግሥተ ሰማይ ትምጣልን: ልጅነትን ትሰጠን በሉ ሲል ነው። እንዲህም ማለቱ መንግሥተ ሰማይ ከወዲያ ወዲህ የምትመጣ: ከወዲህም ወዲያ የምትሄድ ሆና ሳይሆን ትገለጽልን በሉ ማለቱ ነው። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ፈሪሳውያን ቀርበው " የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች? " ብለው በጠየቁ ጊዜ " የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም: ከዚህ አለች ከዚያ የለችም አትባልም: የእግዚአብሔር መንግሥት እንሆ በመካከላችሁ ናት " ብሏቸዋል። ሉቃስ 10:20-21። *ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁም በምድር ትሁን :- መላእክት ከሰማይ ሲያመሰግኑህ ፈቃድህ እንደ ሆነ እኛም በምድር ያለን ደቂቅ አዳም እናመስግንህ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን። ኃላ ሞተን ተነሥተን እናመስግንህ ዘንድ ፈቃድህ ይሁን በሉ ሲል ነው። እንዲሁም አቤቱ ፈቃደ መዓትህን ትተህ: ፈቃደ ምሕረትህን አድርግልን ብላችሁ ብትለምኑኝ አደርግላችኃለሁ ሲልም ነው። *የዕለት እንጀራችንን ስጠን ዛሬ :- በዚህ ዓለም ሳለን ለዕለት የሚሆነንን ምግብ ስጠን በሉ ሲል ነው። በሰማይ ያሉ መላእክት ስብሐተ እግዚአብሔር ተመግበው / በሰማይ አመስግነውህ ያው ምስጋናቸው ምግብ ሆኗቸው / እንዲኖሩ እኛም በምድር እህል ምግባችንን አትንሣን ብላችሁ ብትለምኑኝ አልነሣችሁም ሲል ነው። *በደላችንን ይቅር በለን: የበደሉንን ይቅር እንደምንል :- ማረን: ይቅር በለን: ኀጢአታችንን አስተስርይልን: በደላችንን ደምስስልን: መተላለፋችንን ሁሉ ይቅር በለን: ይቅርታን እናገኝ ዘንድ እኛም የበደሉንን ሁሉ ይቅር እንላለን ሲል ነው። ለዚህም ነው ጌታ " ከሰዎች ኀጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማይ አባታችሁ ደግሞ ይቅር ይላችኃል: ለሰዎች ግን ኀጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም ኀጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም " ብሏል። ማቴዎስ 6:13-15። እንዲሁም " አበሳ " የዓመት ነው: " ጌጋዬ " / በደል / የዕለት ነው። አበሳ የዓመት ያለውም ነፍስ መግደል: ቋንጃ መቁረጥ: ቤት መስበርና ይኸንን የመሳሰለው ሁሉ ነው። ይኸን ያደረገም ጠላቱን ሲርበው ቢያበላ: ሲጠማው ቢያጠጣው: ሲታረዝ ቢያለብሰው: በደለኛ ሲክሰው ዋስ ጠበቃ ቢሆነው: ንስሓ ቢገባ: ስለክፉ ሥራው ቢያዝን ቢጸጸት ቢያለቅስ ይድናል እንጂ ያለዚያስ አይድንም። ፊያታዊ ዘየማን / በቀኙ የተሰቀለው/ ሲድን: ፊያታዊ ዘጸጋም / በግራ የተሰቀለው / አለመዳኑ ንስሓ ባለመግባቱ ነው። ጌጋየ ዕለት ያለው ደግሞ ሰው ሆኖ በተለያየ ምክንያት መጣላት መጋጨት አይቀርምና: ቂም በቀል ሳይዙ ዕለቱን ስለ እግዚአብሔር ይቅር መባባል ነው። ለዚህም ነው ሐዋርያው " በቁጣችሁ ፀሐይ አይግባ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት " ያለው። ኤፌሶን 4:27 *አቤቱ ወደ ፈተና አታግባን :- ከክፉ አድነን ወደ ኀጢአት: ወደ ክህደት: ወደ መከራ: ወደ ገሃነም አታግባን: ከዚህ ሁሉ አድነን እንጂ በሉኝ ሲል ነው። *መንግሥትህ ያንተ ናትና :- መንግሥተ ሰማያት ያንተ ገንዘብ ናትና በሉኝ ሲል ነው። *ኀይል ምስጋናም ለዘላለሙ :- ከሃሊነት: ጌትነት: ለዘላለሙ ገንዘብህ ናትና አሜን በእውነት በሉኝ ሲል ነው። የእግዚአብሔር ኃይል የባሕርይ በመሆኑም ነው ጻድቁ ኢዮብ " ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደሆንህ አሳብህም ይከለከል ዘንድ እንደማይችል አወቅሁ " በማለት የገለጸው ኢዮብ 42:2 ማጠቃለያ: በዚህ የጸሎት ክፍል ውስጥ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከ 81 አሀዱ መጽሐፍት የተገኙ አምስት ቁም ነገሮችን አስተምሯል እነሱም :- 1. ሃይማኖት 2. ተስፋ 3. ፍቅር 4. ትሕትና 5. ጸሎት ናቸው። ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸሎታችንን ይቀበልልን አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

ተፈጸመ ሱባኤ ሐዋርያት ተፈጸመ ሰዓታት ዘፍልሰታ ለማርያም!!! እግዚአብሔር ያብጽአነ አመ ከመ ዮም!!! አሜን!!! የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅሯ በረከቷ አማላጅነቷ ጣእሟ በእኛ ለዘላለ
ተፈጸመ ሱባኤ ሐዋርያት ተፈጸመ ሰዓታት ዘፍልሰታ ለማርያም!!! እግዚአብሔር ያብጽአነ አመ ከመ ዮም!!! አሜን!!! የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅሯ በረከቷ አማላጅነቷ ጣእሟ በእኛ ለዘላለም ጸንቶ ይደርብን!!! ለአባ ሕርያቆስ ለቅዱስ ኤፍሬም ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለቅዱስ ያሬድ የተለመነች ለእኛም ትለመነን። ሰዓሊ ለነ ቅድስት አእምሮውን ልቡን ሳይብን አሳድሪብን፥ ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን። ለትንሣኤ እና እርገቷ ደግሞ በሰላም ያድርሰን። አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

Repost from N/a
የነሐሴ 14 ምስባክ በድምፅ

✝️ የነሐሴ 14 ግጻዌ (የቀኑ ምንባባት) 📖 መልእክታት የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 1:10 - 19 የሐዋርያው ያዕቆብ መልእክት፦ የያዕቆብ መልእክት 1:12 - 22 የሐዋርያት ሥራ
✝️ የነሐሴ 14 ግጻዌ (የቀኑ ምንባባት) 📖 መልእክታት የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 1:10 - 19 የሐዋርያው ያዕቆብ መልእክት፦ የያዕቆብ መልእክት 1:12 - 22 የሐዋርያት ሥራ፦ ሐዋርያት ሥራ 10:30 - 48 (እስከ ፍጻሜው) 🎼 ምስባክ
መዝሙር 43:4-5 ግዕዝ፦ "ዘአዘዝከ መድኃኒቶ ለያዕቆብ፤" "ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ፤" "ወበስምከ ናኃሥሮሙ ለእለ ቆሙ ላዕሌነ።" ትርጉም፦ "የያዕቆብን ማዳን ያዘዝህ፤" "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፤" "በስምህም በእኛ ላይ የቆሙትን እንጥላቸዋለን።"
☦️ ወንጌልና ቅዳሴ ወንጌል፦ የማቴዎስ ወንጌል 17:14 - 24 ቅዳሴ፦ ቅዳሴ ማርያም
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እና እናት እንዲህ አሉ.... ሼር ይደረግ! አባት እንዲህ አለ "...በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ #እርሱን_ስሙት...።" (ማቴ.17:5) እናት እ
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እና እናት እንዲህ አሉ.... ሼር ይደረግ! አባት እንዲህ አለ "...በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ #እርሱን_ስሙት...።" (ማቴ.17:5) እናት እንዲህ አለች "...የሚላችሁን ሁሉ #አድርጉ አለቻቸው።" (ዮሐ.2:5) አብ ልጄን ስሙት ያለው ጌታችን ኢየሱስ ምን ብሎ ነው ብለን ስንጠይቅ ኢየሱስ እንዲህ አለ.... ሰባቱ እኔ ነኝ 1. የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ----- ዮሐ. 6፡35 2. የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ-------- ዮሐ.8፡12 3. እኔ የበጎች በር ነኝ ------------- ዮሐ.10፡17 4. መልካም እረኛ እኔ ነኝ ----------- ዮሐ.10፡11 5. ትንሣኤ እና ሕይወት እኔ ነኝ ----- ዮሐ.11፡25 6. እኔ እውነት መንገድና ሕይወት ነኝ ---------- ዮሐ.14፡6 7. እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ -------- ዮሐ. 15፡1 ድንግል ማርያም የሚላችሁን አድርጉ ያለችን ኢየሱስ ምን አድርጉ ብሎን ነው ብለን ስንጠይቅ መልሱ ደግሞ... 6ቱ ቃላተ ወንጌል፥ 6ቱ ህግጋተ- ወንጌልና አንቀጸ ብጹዓን ላይ እናገኛለን። +========================+ 👉1ኛ.6ቱ ቃላተ ወንጌል የሚባሉት! ማቴ. 25 1/ለተራበ ማብላት 2/የተጠማ ማጠጣት 3/እንግዳ መቀበል 4 /የታረዘ ማልበስ 5/የታመመን ማየት 6/የታሰረ መጠየቅ 👉2ኛ ስድስቱ ህግጋተ-ወንጌል ማቴዎስ 25 1/በወንድምህ ላይ በከንቱ አትቆጣ 2/ወደ ሴት አትመልከት በልብህም አታመንዝር 3/ሚስትህን ካለ ዝሙት ምክንያት አትፍታ 4/ፈፅመህ አትማል 5/ክፉን በክፉ አትመልስ 6/ጠላትህን ውደድ 👉3ኛ አንቀጸ ብጹዓን ማቴዎስ 5 1፤ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። 2፤ የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። 3፤ የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። 4፤ ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። 5፤ የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና። 6፤ ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። 7፤ የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። 8፤ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። 9፤ ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ