Abu Imran Muhammed Mekonn
ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ 👉 ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ◎ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ ⤵ ↪ እቀበላለሁ ↩ ⤴ ➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Abu Imran Muhammed Mekonn
کانال Abu Imran Muhammed Mekonn (@abuimranaselefy) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 23 956 مشترک است و جایگاه 3 133 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 439 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 23 956 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 05 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -238 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -9 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.39% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.40% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 5 125 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 295 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤
👉 ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤
◎ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤
እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር።
ያለወትን ሀሳብ 💡 ➢ @AbuImranAselefybot በሚለው ያድርሱኝ
⤵
↪ እቀበላለሁ ↩
⤴
➻ በተለይ ስህተት ካዩ በፍጥነት ይጠቁሙኝ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 06 سپتامبر | 0 | |||
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | 0 | |||
| 02 سپتامبر | 0 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
ርዕስ :-"ጠንቋዮች (የሩቁን እናውቃለን ባዮች) እና አደጋወቻቸው "🎙ሸይኽ አቡ ዘር ሐሰን ኮምቦልቻ -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በ ኮምቦልቻ ከተማ ሰላም መስጂድ 🗓 ነሐሴ /𝟐𝟗/ 𝟐𝟎𝟏𝟖 ይደመጥ ! https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha
| 2 | ✅ታላቅ የምስራች ለሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
በመጀመሪያ ለዐለማቱ ጌታ አላህ ምስጋና ይገባው!
በመቀጠልም ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረሳዎች ሲቀሩ የነበሩት ደርሶችና ተጨማሪ አዳዲስ ኪታቦች በአድስ መልኩ ቅዳሜ(ነሀሴ-30) ጀምሮ የሚሰጡ ይሆናል። ጊዜያችንን አመቻችተን በሚቀርበን ቦታ በመገኘት ድናችንን እንገንዘብ!
የአላህ መልዕክተኛ ሲናገሩ፦
من يريد الله به خيرا يفقهه في الدين
"አሏህ መልካም የሻለት ሰው ድኑን ያስገነዝበዋል"
الجهل عار عار
لا يرضى به إلا حمار
ማሳሰቢያ
✅ደርሶቹ የሚሰጡበት ጊዜ👉 ከመጝሪብ-ዒሻ
✅ የሚሰጡበት ቦታ 👉 ዳቶ ፣ ቲቲሲና ተማሪዎች መድረሳ
✅ደርሱን የሚሰጡት፦
↪️ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ደሴ
↪️ኡስታዝ ዐብዱልሀሚድ
👉👉👉ዝርዝር ፕሮግራሙን በፎቶው ላይ ተመልከቱ!
ከሱብሂ በኋላ እንድሁም በቀኑ ክፍል የሚወጡ ፕሮግራሞችን የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ለሌሎች ሰዎች በማድረስ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!!
🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈🔈
https://t.me/hutemariwochchannel | 736 |
| 3 | 👉 ሙሐመድ ሓሚዲን የሰይድ ቁጥብ ጠበቃ !
— የሶሓቦች ደረጃ በነብዩ ሙሐመድ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – ምስክርነት !
አላህ ከሰዎች ነብያቶችን መርጦ ወደ ሰው ልጆች በቃሉ ላካቸው ። በዚህም ነብያቶች በአላህና በሰው ልጆች መካከል አገናኝ ሆኑ ። ከተቀሩት ሰዎች መርጦ ደግሞ ለነብያቶች ሀዋሪያት አደረገ ። የነብዩ ሙሐመድ ባልደረቦች (ሶሓቦች) አላህ ለነብዩ ረዳትነት የመረጣቸው ምርጥ ትውልዶች ነበሩ ። የነብዩን መልእክት ባለበት ተጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ውድ ሕይወታቸውን ፣ ክብራቸውን ፣ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ቤዛ አድርገዋል ። ለዚህ ዲን ሲሉ አንገታቸው ተቀልቷል ፣ ገላቸው ተከታትፏል ። አጥታቸው ተሰብሯል ። በደማቸው የነብዩ ሸሪዓ ለምልሞ ለዓለም ደርሷል ። የአላህ መልእክተኛ ስለነዚህ ባልደረቦቻቸው ከተናገሯቸውና የሰደባቸውንና ክብራቸውን የነካን ምን እንዳሉ በሚቀጥሉት ሐዲሶች እንመልከት : –
عن أبي سعيد رضي الله عنه قال : قال رسول الله – صلى الله عليه وآله وسلم –:
«لَا تَسُبُّوا أَحَدًا مِنْ أَصْحَابِي، فَإِنَّ أَحَدَكُمْ لَوْ أَنْفَقَ مِثْلَ أُحُدٍ ذَهَبًا، مَا أَدْرَكَ مُدَّ أَحَدِهِمْ وَلَا نَصِيفَهُ»
أخرجه البخاري ومسلم .
" ከሶሓቦቼ አንዱንም አትሳደቡ ከናንተ ውስጥ አንዳችሁ የኡሑድ ተራራን የሚያክል ወርቅ በአላህ መንገድ ላይ ወጪ ቢያደርግ (የሶሓቦቼን) የአንዳቸውን እፍኝ ወይም ግማሹ አይደርስም " ።
عن عائشة أم المؤمنين قالت: قال رسول الله – صلى الله عليه وآله وسلم –:
«مَنْ سَبَّ أَصْحَابِي فَعَلَيْهِ لَعْنَةُ اللهِ وَالْمَلَائِكَةِ، وَالنَّاسِ أَجْمَعِينَ» .
وقد رواه الإمام أحمد في "مسنده"، والإمام الترمذي وقال: حسن غريب،
" ሶሓቦቼን የተሳደበ በሱ ላይ የአላህ የመላኢካዎችና የሰዎችም ባጠቃላይ እርግማን ይውረድ "።
عن عبد الله بن مغفل – رضي الله عنه– قال :
قال رسول الله – صلى الله عليه وآله وسلم–:
«اللهَ اللهَ فِى أَصْحَابِي، اللهَ اللهَ فِى أَصْحَابِي، لَا تَتَّخِذُوهُمْ غَرَضًا بَعْدِي، فَمَنْ أَحَبَّهُمْ فَبِحُبِّي أَحَبَّهُمْ، وَمَنْ أَبْغَضَهُمْ فَبِبُغْضِي أَبْغَضَهُمْ، وَمَنْ آذَاهُمْ فَقَدْ آذَانِي، وَمَنْ آذَانِي فَقَدْ آذَى اللهَ، وَمَنْ آذَى اللهَ فَيُوشِكُ أَنْ يَأْخُذَهُ».
" በሶሓቦቼ ጉዳይ አላህን ፍሩ, (እኔ ከሞትኩ በኋላ) ክብራቸውን በመንካትና በመስደብ አዛ በማድረግ ኢላማ አድርጋችሁ አትያዟቸው ( በመጥፎ ነገር ወደነርሱ አታነጣጥሩ) እነርሱን የወደደ እኔን ለመውደዱ ነው የወደዳቸው ። እነርሱን የጠላቸው እኔን ለመጥላቱ ነው የጠላቸው ። እነርሱን አዛ ያደረገ እኔን አዛ አደረገ ! እኔን አዛ ያደረገ አላህን አዛ አደረገ ! አላህን አዛ ያደረገ ሊዘው ይቀርባል " ።
ጮሌ በምልክት ይገባዋል እንደሚሉት የነብዩና የሶሓቦች ወዳጆች ሶሓቦችን ለመውደድና ለማክበር አንድ የቁርኣን አንቀፅ ወይም የነብዩ ሐዲስ ይበቃቸዋል ። እነዚህ ስለሶሓቦች ክብርና እነርሱን መስደብ ወይም አዛ ማድረግ አደጋው ምን እንደሆነና ባለቤቱ ለአላህ እርግማንና ለሱ ቅጣት ራሱን የዳረገ መሆኑን የሚያሳዩ የነብዩ ንግግሮች ናቸው ። ሁሉንም እንዘርዝር ብንል መፅሐፍ ማሳተም ግድ ይለናል ። አላህ ካለ በሚቀጥለው ክፍል የሰለፍ ዑለሞች የሶሓቦችን ክብር የሚነካና የሚተች ሰውን አስመልክተው የሰጧቸውን ብይኖች እናያለን ።
https://t.me/bahruteka | 609 |
| 4 | ልዩ አዲስ ሙሃዶራ
ሱናን አጥብቆ መያዝ እና ግዜን በአግባቡ መጠቀም በሚል ሪእስ የተደረገ
ነሓሴ 27/12/2018
🕌 በአል-ወሰጢያህ መድረሳ እና መርከዝ
🎤በዶ/ር ሸይኽ ሁሰይን ቢን ሙሀመድ አስ-ስልጢይ
https://t.me/AbraribnAwal | 308 |
| 5 | 📢 የአዲስ ሪሳላህ ማስታወቂያ
📚 አዳቡል አውላድ ወነይሉል ሙራድ
📚 (آدَابُ الْأَوْلَادِ وَنَيْلُ الْمُرَادِ)
👉 ለልጆቻችን አደብ፣ ስነ-ምግባር እና ትምህርት እጅግ አስፈላጊ የሆነ ጠቃሚ አዲስ ሪሳላህ ዝግጁ ሆኖ ቀርቧል።
📝 ዝግጅት እና ስብስብ፦
ሸይኻችን አቡ መንሱር ሸይኽ ሙሐመድ ሀያት አል-ወሎውይ
📝 جَمْعُ وَتَرْتِيبُ أَبِي مَنْصُورٍ الشَّيْخ مُحَمَّد حَيَاةَ الْوَلَوِيِّ
📖 ስለ ሪሳላው፦
◈ የልጆችን የዕለት ተዕለት አደብ የሚያስተምር
◦ ለቤተሰብ እና
◦ ለኡስታዞች
◦ ለልጆች ማስተማሪያነት የሚረዳ
● በአጭሩ እና በግልጽ ሁኔታ የተዘጋጀ
✔️ ለበለጠ መረጃ እና ኪታቡን ለማግኘት ቻናላችንን ይከታተሉ!
🔗 ቴሌግራም ቻናል: 👇👇
[https://t.me/kutub_of_pdf]
♻️ ሊንክ መቁረጥ ክልክል ነው። | 967 |
| 6 | 👉 ሙሐመድ ሓሚዲን የሰይድ ቁጥብ ጠበቃ !
ክፍል አንድ
ሶሞኑን ሙሐመድ ሓሚዲን የእውቀት ቅርስ በሚል ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ስለ ሰይድ ቁጥብ የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርቦለት በጣም አሳፋሪ በሆነ ሁኔታ የነብያቶችን ክብር የሚያጎድፈውን የነብዩ ባልደረቦችን የሚያዋርደውንና የሙስሊሙን አለም ማህበረሰብ በግልፅ የሚያከፍረውን የሰይድ ቁጥብን ጥመቶች እንደ ተራ ጥፋት በመቁጠር ስሌት ሰርቶ ሙዋዘና በሚባለው ሸውራራ ሚዛን እየለካ ያ ጥፋት በዚህ ይጣፋል በሚል አይነት አንድምታ ያለው ዑዝር እየሰጠ ሲያልፍ ሰምተናል ። ከዚህ ጎን ለጎን የሰይድ ቁጥብን ስህተቶች በመረጃ በማጋለጥ ለነብያቶችና ለነብዩ ባልደረቦች ክብር ዘብ የቆሙትን ዑለሞች ወሰን አላፊዮች በሚል የንግግር ቃና ወርፏል ።
በዚህ ሳያበቃ ለሸውራራ ፍርዱ ይረዳው ዘንድ ከዘመናችን ዑለሞች ውስጥ ስለግለሰቡ ሳያውቁ በፊት የተናገሯቸውን ንግግሮች በማምጣት ባጢልን ሐቅ ለማስመሰል ሞክሯል ።
እዚህ ጋር አንባቢያን ሊያውቁት የምፈልገው የሰይድ ቁጥብ ስህተቶች ተራ ስህተቶች ሳይሆኑ አንዱ እንኳን ከእስልምና የሚያወጣ አይነት ለተራራ የከበዱ ቅጥፈት የተሞላባቸው ከባባድ ወንጀሎች መሆናቸውን ነው ። ከእነዚህ ውስጥ እንደማሳያ የነብያትን ክብር መንካት ፣ ሶሓቦችን በኒፋቅ መወረፍ የኢስላሙን አለም ማህበረሰብ በግልፅ ማክፈር የሚሉት ይገኙበታል ። እንደነዚህ አይነት ስህተቶች የኢስላም ሊቃውንቶች ዘንድ ያላቸው ብይን ባለቤቱ ይከፍራል ወይስ አይከፍርም የሚል ነው ። በሱና ዑለሞች ዘንድ ፋሲቅና ሙብተዲዕ ለመሆኑ ኺላፍ የለም ። አላህ ካለ ወደፊት በሚመጡ ክፍሎች በዝርዝር በመረጃ የምናያቸው ይሆናል ።
ለዛሬ ለመግቢያ ይሆን ዘንድ ስለነብያትና ሰለሶሓቦች ክብር የተወሰነ እንይ :–
— ነብያቶች በአላህና በፉጡራኖቹ መካከል አገናኝ እንዲሆኑ ፉጡራኖችን ከኩፍር ጨለማ ወደ ኢማን ብርሀን እንዲያሸጋግሩ አላህ መርጦ የላካቸው ምርጥ ባሮቹ ናቸው ። ይህን አስመልክቶ አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል : –
{ وَإِذَا جَاءَتْهُمْ آيَةٌ قَالُوا لَن نُّؤْمِنَ حَتَّىٰ نُؤْتَىٰ مِثْلَ مَا أُوتِيَ رُسُلُ اللَّهِ ۘ اللَّهُ أَعْلَمُ حَيْثُ يَجْعَلُ رِسَالَتَهُ ۗ سَيُصِيبُ الَّذِينَ أَجْرَمُوا صَغَارٌ عِندَ اللَّهِ وَعَذَابٌ شَدِيدٌ بِمَا كَانُوا يَمْكُرُونَ}
الأنعام (124)
" ተዓምርም በመጣቻቸው ጊዜ ፡- «የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ እስክንሰጥ ድረስ በፍጹም አናምንም» አሉ ፡፡ አላህ መልክቱን የሚያደርግበትን ስፍራ ዐዋቂ ነው ፡፡ እነዚያን ያመጹትን ሰዎች ይዶልቱ በነበሩት ነገር አላህ ዘንድ ውርደትና ብርቱ ቅጣት ያገኛቸዋል "፡፡
በዚህ አንቀፅ ላይ እንደምናየው አላህ ለከሀዲያኖች መልስ ሲሰጥ " አላህ መልእክቱን የሚያደርግበትን ስፍራ ዐዋቂ ነው " ይላቸዋል ። መልእክቱንም ከሰዎች ውስጥ ነብያቶችን መርጦ ልባቸውን ለመልእክቱ ማስቀመጫ ስፍራ አደረገው ። እነዚህን አላህ መልእክቱን ሊያስቀምጥባቸው የመረጣቸውን ነብያቶች ክብር መንካት ያከፍራል ። ይህ ሲባል የአንድ ነብይ ክብር መንካት ያጠቃላይ ነብያቶች ክብር መንካት ማለት አይደለም የሚል የሸረሪት ድር አይነት ሹብሀ የሚያነሱ ስለማይጠፉ አላህ ይህን በር በሚቀጥለው አንቀፅ ዘግቶታል : –
{ قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ}
آل عمران (84)
«በአላህ አመንን ፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም (በቁርኣን) ፣ በኢብራሂምና በኢስማዒልም፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው ፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው (አመንን) ፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም ፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» በል ፡፡
በዚህ አንቀፅ ላይ እንደምናየው አላህ ከመልእክተኞች መካከል መለየት እንደማይቻል እንዲህ ብሎ ነገረን " ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም " ። እኛ ለነርሱ ታዛዦች ነን በል " ። ብሎ በሁሉም ነብያቶች ማመን ግዴታ መሆኑ ነግሮናል ። ከዚህ በመነሳት የኢስላም ሊቃውንቶች አላህ ከላካቸው መልእክተኛች ውስጥ የአንዱንም ክብር መንካት የሁሉንም ክብር መንካት እንደሆነ በተለይም ደግሞ ዑሉል ዐዝም የተባሉትን ክብር መንካት የወንጀሉን ክብደት እንዲጨምር እንደሚያደርገው ይስማማሉ ። ለዚህ ነው ከእስልምና መሰረታዊ የኢማን ክፍሎች ( አርካኑል ኢማን) አንዱ በነብያት ማመን የሆነው ። የነብያትን ክብር መንካት በነብያት ማመንን ይፃረራል ። ሰይድ ቁጥብ የሚያቋሽሻቸው ነብዩላሂ ሙሳ ከዚህ ለየት ባለ መልኩ አላህ ለኔ መርጨሃለሁ ያላቸው መሆኑን በሚቀጥለው አንቀፅ እንመልከት : –
{ وَاصْطَنَعْتُكَ لِنَفْسِي}
طه (41)
«ለነፍሴም (በመልእክቴ) መረጥኩህ ፡፡
ይህ ስለነብያቶች ከመጡ መረጃዎች ከባሕር እንደ ጠብታ ሲሆን ለጮሌ ማመላከት ይበቃዋልና ልብ ያለው ልብ ይበል ። እኝህን አላህ መርጦ ያከበራቸውና መልእክተኛው አድርጎ ወደ ሰው ልጆች የላካቸውን የአላህ መልእክተኛን ነው ሰይድ ቁጥብ ክብራቸውን በመንካት የሚያዋርዳቸው ። አላህ ካለ በሚቀጥለው ክፍል ስለ ሶሓቦች ደረጃና ክብር እንዲሁም እነርሱን የመሳደብና ክብራቸውን የመንካት ብይን እናያለን ።
https://t.me/bahruteka | 992 |
| 7 | 👉 ቢዳዓ ከመጠጥ በላይ ያሰክራል !
ኢኽዋኖች መርሐቸው እንደ አየሩ ፀባይ ይቀያየራል ። ወጥ የሆነ መርህ የላቸውም ። መለኮታዊው የህይወት መመሪያ የአላህና የነብዩ ንግግሮችና መመሪያዎች ለእነርሱ መርህ የሚሆኑት ከስሜታቸው ጋር ከገጠሙ ብቻ ነው ። ካልሆነ ቦታ የላቸውም ! እነርሱ የሚጋልቡበት የስሜት ፈረስ ወደ ሚፈልጉት የስልጣን እርከን ካደረሳቸው ሁሉ ነገር ሀላል ነው ። ሁሉ ነገር መስላሓ ነው ። ሁሉ ነገር ለእስልምና ሲባል ነው ። ምናልባት ያ ተግባር የእስልምናን መሰረት የሚንድ ቢሆንም እንኳን !
ለዚህ ነው በተለያየ ጊዜ በሸሪዓ ሚዛን ያልተመዘነ ንግግር የምንሰማውና ሸሪዓን የሚንዱ ተግባራቶችን የምናየው ። ሶሞኑን ጉዞውን ወደ ባሌ ያደረገው የሀገራችን የኢኽዋን መሪዮች ቡድን ትላልቅ ካላቸው መሪዮቹ ውስጥ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ይገኙበታል ። ይኸው ቡድን አብዛኛ ማህበረሰብ የሽርክ መናኻሪያ ያደረገውንና በአሁኑ ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ እየተገነባ ያለውን የሶፍ ዑመርን ዋሻን ፕሮጀክት ከጎበኘ በኋላ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ባደረጉት ንግግር ከነብዩ በኋላ ነብይ ስለማይመጣ ዶ/ር አብይን ወልይ ብንለው ምን ትላላችሁ ሲል የተሰበሰበው ህዝብ በተክቢራ አጅቦ ወልይነቱን አፅድቋል ! ።
ንግግሩን በሚቀጥለው ሊንክ ገብታችሁ አዳምጡ : –
https://drive.google.com/file/d/17fzkqAYx5JvC-V4XvqAi2a70bKEiCGg4/view?usp=drivesdk
ኦሮምኛ የማትችሉ አስተርጉማችሁ ስሙት ። ገርሞ ገርሞ ይገርማል ።
የትኛው ደስታ በዚህ ልክ እንዳሰከራቸው አናውቅም ። መጀመሪያ አካባቢ የማህበረ ቅዱሳን አክቲቪስቶች ዶ/ር አብይ ነብይ ነው ሲሉ ነበር ። እነዚያ አካላት ዛሬ እየተራገሙ ይገኛሉ ። ከእነርሱ ውስጥ የኢኽዋን አክቲቪስቶችም ነበሩበት ። አሁን ደግሞ ኢኽዋኖቹ ደረጃውን ወደ ወልይነት አወረዱት ። ያም ሆነ ይህ ወልይነት ለፈለጉት የሚያለብሱት ካባ ሳይሆን በአላህ ብቸኛ ተመላኪነት በማመንና እሱን በመፍራት የሚገኝ ሲሆን ነብይነት ደግሞ የሚሰጠው በአላህ ምርጫ ነው ። ለማን እንደሚገባና ለማን መሰጠት እንዳለበት የሚያውቀው እሱ ነውና ።
ለማንኛውም መርህ አልባ የሆነ አካል መርሁ ስሜቱ ነውና ብዙም አይገርመንም ። ነገር ግን ሁሉም ማወቅ ያለበት ዱንያ ላይ የሚሰጡ ምስክርነቶች አላህ ፊት የሚያስጠይቁ መሆናቸውን ነው ። ለዚህ ማረጋገጫው የሚከተለው የአላህ ቃል ነው : –
{وَقِفُوهُمْ ۖ إِنَّهُم مَّسْئُولُونَ}
الصافات (24)
«አቁሟቸውም ፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል) ፡፡
አላህ ሐቅን አውቀን የምንከተለውና ባጢልን አውቀን የምንርቀው ያድርገን ።
https://t.me/bahruteka | 2 400 |
| 8 | 🎤 ታላቅ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ጥሪ↩️
⚙ የፕሮግራሙ አዘጋጆች፦
✅ የኢሎስ ሰለፍያ ጀምዓ
🪑የእለቱ ተጋባዥ እንግዳዎቻችን ፦↩️
🎙ሸይኽ አብዱልሀሚድ አል-ለተሚይ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ሸይኽ መህቡብ ከሳንኩራ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ሸሰይፉላህ ከምስራቅ ስልጢ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ኡስታዝ ኢዙዲን ከሁልባራግ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ኡስታዝ ነስሩዲን ከሳንኩራ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ኡስታዝ ኢብራሂም ከወራቤ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ኡስታዝ ስራጅ ከወራቤ -ሐፊዘሁሏህ-
🎙ኡስታዝ በህሩ ከስልጢ ወረዳ -ሐፊዘሁሏህ-
☞ የፕሮግራሙ መሪ :-
↳ አቡ ዒምራን
↳ አቡ ዐማር
↳ አቡ ሑዘይፋህ
↳ አቡ ኑዐይም
⇾ኢንሻአላህ ሌላም ተጋባዥ እንግዳ ይኖራል !!
🗓ፕሮግራሙ የፊታችን ቅዳሜ
ቀን /23/12/2018
በኢትዮ 3:00 በሳኡድ=9:00 ይጀመራል ቀደምብላቹ በመገኘት የፕሮግራሙ ተካፋይ ይሁኑ!!!
✅ፕሮግራሙን ለመከታተል ሊንኩን
በመጫን ይቀላቀሉ።
✍በቻናል እና በግሩፓች ሼር በማድረግ
ሀላፍትናችንን እንወጣ
➷➷➷➷➷➷➷➷➷ https://imo.onelink.me/RAdY?af_dp=imo%3A%2F%2Fuser.voiceroom.join%2Fmy.0s168dngpwesn5dx%3Fentry_type%3Dshare_web_dp=https%3A%2F%2Fimo.im&from=copy_link | 3 200 |
| 9 | 🔹ወሳኝ የጁሙዓህ ኹጥባ (ምክር)
ርዕስ :-" አንደበትን (ምላስን) መጠበቅ "
🎙ሸይኽ አቡ ዘር ሐሰን ኮምቦልቻ -ሐፊዞሁ'ሏህ-
🕌 በ ኮምቦልቻ ከተማ ሰላም መስጂድ
🗓 ነሐሴ / 𝟐𝟐 / 𝟐𝟎𝟏𝟖
ይደመጥ !
✈️https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha | 3 203 |
| 10 | 🟢በማያውቁት ጉዳይ መግባት …🟢
አላህ በጥብቅ የከለከለው ጉዳይ:
قال الله سبحانه
《وَلَا تَقْفُ مَا لَيْسَ لَكَ بِهِ عِلْمٌ ۚ إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا》 الإسراء:(36)
"እውቀት በሌለህ በሆነ ነገር አትከተል።መስሚያ ፣ መመልከቻም ፣ ልብም በእነዚህ ሁሉ (ተግባር) ባለቤታቸው እኮ ተጠያቂ ነው።"
ሰለፎች እውቀት በሌለ ነገር ከመከተል ውስጥ የሚከተሉትን ጠቅሰዋል።
لا تتبع ما لا تعلم وما لا يعنيك
1⃣የማታውቀውንና የማይመለከትህን ጉዳይ አትከተል።
لا تقل ما ليس لك به علم
2⃣ እውቀት በሌለህ ጉዳይ አትናገር።
لا تقل: رأيت ولم تر، وسمعت ولم تسمع
3⃣ ሳታይ አይቻለሁ ፣ ሳትሰማ ሰምቻለሁ አትበል።
قول الزور، وشهادة الزور
4⃣ ከቅጥፈት ንግግርና ከቅጥፈት ምስክርነት ተጠንቀቅ።
التحلم بحُلمٍ كاذب
5⃣ ያላዩትን ህልም እንዳዩ አስመስሎ ወይም አቀነባብሮ ከማውራት ተጠንቀቅ።
الحكم بالظن
6⃣ በግምት ብይን ከመስጠት ተጠንቀቅ።
التقليد الأعمى
7⃣ ከጭፍን ተከታይነት ተጠንቀቅ።
البدعة في الدين
8⃣ በዲን ላይ የአምልኮ ፈጠራን ተጠንቀቅ።
الجرح والتعديل
9⃣በውል ስለማታውቀው አካል ትችትም ሆነ ውዳሴ ተጠንቀቅ።
እነዚህ ባህሪያትና ተግባራት አላህ ዘንድ በጥብቅ ያስጠይቃሉ።
👉ጭራሽ በማያውቁት ጉዳይ ይቅርና በጥርጣሬ (الظن) ላይ ሆኖ መናገር እንኳን ከባድ ስለመሆኑ የቁርኣንና የሀዲስ ጥቅሶች በርካታ ናቸው።
( وَقُلْ رَبِّ زِدْنِي عِلْمًا )
✍ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ)
http://t.me/Abuhemewiya | 3 054 |
| 11 | 🌸🍃
"كلمتُكَ الطيبةُ لها أَثَر؛
اعتذارُكَ له قيمَةٌ؛
تفهمُكَ للآخرينَ أدَبٌ؛
التغاضي عن الأخطاءِ وعيٌ ؛
مراعاةُ المشاعرِ نُبْلٌ ؛
صَوْنُ الوُدِّ وُدٌّ ؛
ما تُقدِّمه لغيركَ عائدٌ إليكَ ؛
لا تبخلْ بالجَمَالِ فتصبح خاليًا منه"
💡መልካም ተግባራቶች
"መልካም ቃላትህ ትልቅ ተፅዕኖ አላቸው
ይቅርታህ ዋጋ አለው
ሌሎችን መረዳትህ ስነ-ምግባር ነው
ስህተቶችን ማለፍና ችላ ማለት ብስለት ነው
የሌሎችን ስሜት መጠበቅ ልግስና/ክብር ነው
ፍቅርን መጠበቅ ራሱ ፍቅር ነው
ለሌሎች የምትሰጠው ነገር ሁሉ ወደ አንተ ተመልሶ ይመጣል
ስለዚህ ውበትን አትስሰት (አትቁጠብ) አሊያ ከእሱ ባዶ ትሆናለህና።
↪️↪️
💬 የፍቅር ቤት ❨ @YeFkrBet_1❩
💬 ለተጨማሪ ነጥቦች ↙️
🌐 https://t.me/YeFkrBet_1
💡 ሀሳብ ካለዎ 👇 ያናግሩን
https://t.me/YeFkrBet_1bot | 2 347 |
| 12 | አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
ውድ ሰለፊዮች እንኳን ደስ ኣላችሁ
ይህቺ አፕ በተሳካ ሁኔታ በplay store ተጭናለች ከዚህም ቦሀላ የምንሰራቸው አፖችን በፕሌይስቶር ስለምንጭን ሰርች ሲደረጉ ከፊት እንዲመጡ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ገብታችሁ አምስት ኮከብ እንድትሰጡ በታለቅ አክብሮት እና ትህትና እያጠየቅን መላው ሰለፊይ የቻናል በልተቤቶች ለሌሎች እንዲደርስ ሼር መድረግን አትርሱ!
Play Store👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.abdulrezak.tuhfetulatfal&utm_source=chatgpt.com
📲 አሁኑኑ አፑን ያውርዱ እና ለሌሎችም ያጋሩ☝☝
🛠 የአፕ ማሰሪያ አገልግሎት ለማግኘት
👉 @JJ_selfy_app_developer
📢 ከ100 በላይ እስላማዊ አፕልኬሽኖችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
https://t.me/jj_app_developer
https://t.me/jj_app_developer
https://t.me/jj_app_developer | 4 536 |
| 13 | 🔊#አዋጅ! #አዋጅ! #አዋጅ! 🔊
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
🔵እነሆ የፊታችን ጁሙዓ ማለትም ነሀሴ 22/2018 አ. ል. {ረቢዓል አወል ١٥/١٤٤٨. هـ } በዓይነቱ ልዮ የሆነ ታላላቅ የሰለፍያ #መሻይኾች የሚሳተፉበት ሀገር አቀፍ #የonline የዳዕዋ ፕሮግራም ተሰናድቶ አርሂቡ ይላቹሀል።
💺ተጋባዥ መሻይኾች
1,ሸይኽ ሀሰን ገላዉ {ከባህር ዳር}
2,ሸይኽ ዐብዱል ሐሚድ አል'ለተሚይ{ከስልጤ}
3,ሸይኽ ዩሱፍ አሕመድ(ከባህርዳር)
4,ዶ/ር ሸይኽ ሑሰይን አስ'ስልጢ
(ከአዲስ አበበ)
5,ሸይኽ ጦሀ ኸድር (ከአዲስ አበባ)
6,ሸይኽ አቡ ዘር ሐሰን (ከኮምቦልቻ)
7,ሸይኽ ሙሐመድ ጀማል(ከኮምቦልቻ)
8,ሸይኽ ሙሀመድ ሀያት {ከሀራ}
9,ሸይኽ ሑሰይን ከረም (ከሀራ)
10,ሸይኽ ሙባረክ (ከወልቅጤ)
✪ሌሎችም እንግዶች ይኖሩናል
🌍የፕሮግራሙ ቦታ
በሀራ ሰለፍዮች የቴሌግራም ግሩፕ
💻የፕሮግራሙ አዘጋጆች
የሀራ ሰለፍያ ጀመዓዋች
🕰የፕሮግራሙ ሰዓት
🇪🇹በኢትዮ. 3:00 pm
🇸🇦በሳዉድ. 9:00 pm
🇦🇪በዱባይ. 4:00 pm
📡ፕሮግራሙን ለመከታተል
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/haraselefi
https://t.me/haraselefi
https://t.me/haraselefi
https://t.me/haraselefi
👆👆👆👆👆👆👆👆
Join ይበሉ!
✅የፕሮግራሙ ቀን እስከሚደርስ #ሸር
ባማድረግ ለብዙ እህት ወንድሞች ተደራሽ እንድሆን የበኩላችንን እንወጣ።
🔵ባረከሏሁ ፊኩም!!!!
💻 ሌሎች መሻይኾቻችንና ዱዓቶቻችን ኢንሻ አሏህ በሌላ ፕሮግራም የምንገናኝ ይሆናል
| 3 123 |
| 14 | #ስለ_መውሊድ_በኡለሞቻችን
➪➩➪➩➪➩➪➩➩➩
✅ በአለም ላይ ታዋቂ የሆኑና በአላህ ፍቃድ ባላቸው እውቀት ከጥመት ባለቤቶች ውጭ ትንሽ ትልቁ፤ ሴት ወንዱ የሚያከብራቸው ውድና የተከበሩ የሱና መሻይኾች በአሁኑ ሰዓት እየተደገሰ ስለሚገኘው መውሊድ የሰጡት የተለያዩ ትምህርት ሲሆን ከታች በሊንክ ቀርቦላችኋል።
ታላላቅ ኡለሞች ስለ
መውሊድ ምን አሉ?
╭─••─═••═─•••─╮
✅ ክፍል ❶ እስከ ⓯
╰─••─═••═─•••─╯
❶ኛ ➦ በታላቁ ዓሊም አንደበት
ስለ #መውሊድ
🎙 سماحة الشيخ عبدالعزيز بن باز رحمه الله
🎙 በሸይኽ አብዱል አዚዝ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3911
➋ኛ መውሊድ ቢድዓ ስለመሆኑ ስለ አጀማመሩም
↩️ هل الإحتفال بالمولد بدعةٌ أو سُنّةٌ؟ومتىٰ عُرف هذا الإحتفال، ومتىٰ بدأ؟
🎙 فضيلة الشيخ العلامة محمدأمان بن علي الجامي رحمه الله تعالى
🎙 በሸይኽ ሙሐመድ አማን ቢን አልይ አልጃሚ ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3920
➌ኛ ለነብዩ መውሊድ መሰባሰብ ይቻላልን?
↩️ هل يجوز أن نحتفل بالمولد النبوي؟
🎙 فضيلة الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله
🎙 በሸይኽ ሱለይማን አሩሃይሊ ሀፊዘሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3924
➍ኛ ነብዩ ﷺ ረቢዕ 12 ቀን ተወልደዋልን?
↩️ هل ولد النبي ﷺ يوم ١٢ ربيع الأول؟
🎙 فضيلة الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله
🎙 በሸይኽ ሱለይማን አሩሃይሊይ ሀፊዘሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3938
❺ኛ አጠር መጠን ባል ገለፃ የቀረብ ወሳኝ ነጥብ መውሊድ ቢድዓ ለመሆኑ
🎙الشيخ الدكتور عبد العزيز الريس حفظه الله
🎙 በሸይኽ አብዱልአዚዝ አረይስ ሀፊዘሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3943
❻ኛ በዲናችን ላይ የፈለሰፈ በሚለው ሀዲስ ላይ ተዕሊቅ በዛውም ለመውሊድ ምላሽ ተሰጥቶበታል።
↩️ تعليق مهم على حديث "من أحدث في أمرنا" وفيه الرد على بدعة المولد
🎙 الشيخ محمد بن علي بن آدم الإتيوبي الولوي
🎙 በታላቁ ኢትዮጵያዊ ዓሊም ሙሐዲስ አሽ‐ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ ብን አደም ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3946
❼ኛ መውሊድ ቢድዓ ሊሆን እንዴት ቻለ?
➺ መውሊድን የጀመሩት እነማን ነበሩ?
➺ ሶሃቦችስ መውሊድን አክብረዋልን?
🎙 الإمام الفقيه العلامة محمد بن آمان بن علي الجامي رحمه الله تعالى
🎙 በታላቁ ኢማም ሙሀመድ ቢን አማን አልጃሚ ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3951
➑ኛ በመውሊድ ዙሪያ ጥሩ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ወሳኝ ሙሐደራ ነው።
➽ በምርጥ አገላለፅ አቅርበውልናል።
🎙 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى
🎙 በሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3953
❾ኛ ለመውሊድ የአቡ ለሃብን መናም መረጃ ለሚያደርጉ ምላሽ
↩️ الرد على من يستدل بمنام أبي لهب في جواز الاحتفال بالمولد
🎙 الشيخ محمد بن علي بن آدم الإتيوبي الولوي
🎙 በታላቁ ኢትዮጵያዊ ዓሊም ሙሐዲስ አሽ‐ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ ብን አደም ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3955
❿ኛ ጥሩ ቢድዓ አለን? ለመውሊድ መሰባሰብስ ፍርዱ ምንድን ነው?
↩️ هل هناك بدعة حسنة؟ وحكم الإحتفال بالمولد؟
🎙 الشيخ العلامة الإمام عبد العزيز بن عبد الله بن باز رحمه الله تعالى
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3958
⓫ኛ ስለ መውሊድ ሁክም በተለያዩ ታላላቅ ዓሊሞች
↩️ حكم الإحتفال بالمولد النبوي
✅ لمجموعة من العلماء الأكابر:
🎙 الإمام مقبل الوادعي
🎙 الإمام ابن عثيمين
🎙 الإمام الألباني
🎙 الإمام ابن باز
رحمهم الله جميعًا
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3960
⓬ኛ እጅግ በጣም #ማራኪ አገላለፅ በመውሊድ ዙሪያ
🎙 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى
🎙 በሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን ረሂመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3966
⓭ኛ የነብዩ ﷺ መውሊድ በሚከበርበት ቦታ መገኝት ፍርዱ ምን ይሁን?
🎙 العلامة الإمام : مقبل بن هادي الوادعي ـ رحمه الله تعالى
🎙️ በሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አል-ዋዲዒ ረሒመሁሏህ
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3970
⓮ኛ ነብያችን ከመውሊድና መውሊድ ላይ ከሚፈፀመው ጥፋት የጠሩ ናቸው።
➡️ ሰኢድ አልኩመልይ ለተባለው ሱፍይ የተሰጠ መልስ
🎙 العلامة الإمام : صالح بن فوزان الفوزن حفظه الله
🎙️ ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን ሐፊዘሁሏህ።
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3973
⓯ኛ መውሊድ ሲደርስ ስለ ረሱላችን ﷺ የሕይወት ታሪክ፣ ባህሪያት ማውራት ይቻላል?
🎙 العلامة الإمام : صالح بن فوزان الفوزن حفظه الله
🎙️ ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን ሐፊዘሁሏህ።
በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3977 | 8 524 |
| 15 | 🚫 የሰለፍዮች የዳዕዋ ነፃነት በመጅሊስ አመራሮች መልካም ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ አይደለም !
ኢትዮዽያዊያን የፈለጉትን አስተሳሰብም ሆነ እምነት የማራመድ መብታቸው በማያሻማ ሁኔታ እንደ ጠዋት ፀሀይ ፍንትው ብሎ በሚታይ መልኩ ህገ – መንግስቱ ያስቀምጣል ። በመሆኑም እኛ ኢትዮዽያዊያን ሰለፍዮች ህገ – መንግስቱ ለዜጎች የሰጠውን መብታችን በመጠቀም በሀገራችን ላይ የመረጥነውን የሰለፍያ መዝሀብ የመከተልና ሌሎችንም ወደዚሁ የመጥራት መብት አለን ።
ህገ – መንግስቱ ለዜጎች እምነታቸውን በነፃነት የማራመድ መብታቸው ካረጋገጠባቸው አንቀፆች ውስጥ የሚከተለውን እንይ : –
በኢፊድሪ ህገ – መንግስት አንቀፅ 27(1) እንዲህ ይላል : –
" ማንኛውም ሰው የመረጠውን እምነት የመያዝ ፣ የማክበር ፣ የማራመድ ሙሉ ነፃነት አለው " ።
ይህ ሀገራችን የምትመራበት ህገመንግስት ለሁሉም ዜጎች በእኩልነት የሰጠው መብት ነው ። የትኛውም አካል ማንንም ከኔ ስር ካልሆንክ ብሎ የማስገደድም ሆነ የማዘዝ መብት እንደሌለው ያረጋግጣል ። በሌላ በኩል ይኸው ህገመንግስት ለዜጎት ያልተገደበ የእምነት ነፃነት የሰጠና ማንም ይህን ነፃነት የመገደብና የማስገደድ መብት እንደሌለው ያስቀምጣል ። ይህም በሚከተለው የህገመንግስት አንቀፅ እናገኘዋለን : –
– በኢፊድሪ ህገ– መንግስት አንቀፅ 27(3) እንዲህ ይላል : –
" ማንኛውም ሰው የሚፈልገውን እምነት ለመያዝ ያለውን ነፃነት በሀይል ወይም በሌላ ሁኔታ በማስገደድ መገደብ ወይም መከልከል አይችልም "።
ህገመንግስቱ በዚህ መልኩ ለዜጎች ያልተገደበ የፈለጉት እምነት በነፃነት የማራመድ መብት መጅሊሱ አላይም አልሰማም ብሎ ከኔ ስር ካልሆንክ ብሎ ዜጎችን እያሳሰረና ከመስጂድና ከመድረሳ እያስባረረ ይገኛል ። ይህ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮዽያ የምትከተለው የብዝሀነት ፖሊሲ እንዲሁም በእነዚህ አንቀፆች ስር የተቀመጠውን ህገመንግስታዊ መመሪያ የጣሰ ነው ። በተጨማሪም መጅሊሱ የሚያራምደው በኔ ስር ካልሆንክ የሚለው የረጋጭነት አካሄድ ከብዝሀነት መርሁ ጋር ፍፁም ተቃራኒ ከመሆኑም በላይ የዜጎችን ህገመንግስታዊ መብት ነጥቆ ረግጬ ልግዛህ ባይነት ነው ።
እኛ ኢትዮዽያዊያን ሰለፍዮች ሀገራችን የምትመራው በህገመንግስቱና ረጋጭነትን በሚዋጋ ብዝሀነትን መሰረት ባደረገ መርህ መሆኑን ጠንቅቀን እናውቃለን ። በመሆኑም ሀገራችንን እያስተዳደረ ያለው ብልፅግና ፓርቲ የህገመንግስቱን የበላይነት አስጠብቆ የብዝሀነትን መርሁን እውን አድርጎ መብታችንን ሳይቆራረስ እንዲያስከብርልን እንጠይቃለን ።
ከዚህ ጎን ለጎን የብልፅግና ፓርቲ እንዲያውቅልን የምንፈልገው የሀገሪቱን ህገመንግስታዊ መመሪያ ተከትለው ህዝብን በእኩልነት እንዲያገለግሉ የህዝብ አደራ ተጥሎባቸው በመንግስት የስልጣን ወንበር ላይ የተቀመጡ አንዳንድ ባለስልጣናትና እንዲሁም አንዳንድ የፖሊስና የሰላምና ፀጥታ አካላት ያስቀመጣቸው የገዢው ፓርቲ ሳይሆን መጅሊሱ ረግጬ ልግዛህ የሚለውን አላማው ሊያስፈፅሙለት ደሞዝ የሚከፍላቸው የሚመስሉ መሆኑን ነው ።
ይህ በኢፊድሪ ህገ – መንግስት አንቀፅ 11 መሰረት መንግስት በሀይማኖት ጣልቃ እንደማይገባና ሀይማኖትም በመንግስት ጣልቃ እንደማይገባ የተቀመጠውን መርህ የሚጥስ ነው ። እነዚህ አካላት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዮች በእምነት ጣልቃ ገብተው አንተ እገሌን ተከተል ከእገሌ ስር ሁን እያሉ የፈለጉትን እያሰሩ የሰለፍዮችን ተቋማት ( መድረሳና መስጂዶችን እያሸጉና አስለቅቀው ለመጅሊስ እያስረከቡ ይገኛሉ ። በመሆኑም እኛ ኢትዮዽያዊ ሰለፍዮች የዚህ አይነቱ ፀረ ህገመንግስታዊና ፀረ የፓርቲው መርህ አካሄድና ጭቆና በአስቸኳይ እንዲቆምልን እንጠይቃለን ።
በጣም የሚገርመው የዚህ አይነቱ ግፍና ጭቆና አሁን አብዛኛው ኢትዮዽያዊ በጉጉት የሚጠብቀው ሀገራዊ ምክክር እየተካሄደ ባለበት ወቅትም ጭምር እየተፈፀመ መሆኑ ነው ።
ሌላው ሁሉም ሰለፍይ ሊያውቀው የሚገባው መጅሊሱ ሰኔ 28/2012 በአዋጅ ሲቋቋም አንቀፅ 6 ንኡስ አንቀፅ 3 ላይ
" የዚህ ምክር ቤት መቋቋም የሀገሪቷ ሙስሊሞች በክልልም ሆነ በፌዴራል ደረጃ የመሰረትዋቸውን በሀይማኖት የተደራጁ ተቋማት መብትም ሆነ ለወደፊት የመደራጀትና የመመዝገብ መብታቸውን አይከለክልም "
በማለት በግልፅ ማስቀመጡን ነው ። ይህ ማለት በተቋም ለመደራጀትና ለመመዝገብ ከፈለጉ ይችላሉ ማለት እንጂ ካልተደራጁ እምነታቸውን በነፃነት ማራመድ አይችሉም ማለት አለመሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ከላይ በአንቀፅ 27(3) ያየነውን መብት የሚያጠናክር ነው ።
ውድ ሰለፍዮች ሆይ ዐቂዳችሁን በግል ቤታችሁም ይሁን ቤት ተከራይታችሁ ወይም ገዝታችሁ የማስተማርና በነፃነት ዳዕዋ የማድረግ መብታችሁ ህገ – መንግስቱ ያረጋገጠላችሁ የዜግነት መብት እንጂ ማንም በምፅዋትነት የለገሳችሁ ስላልሆነ መብትና ግዴታችሁን አውቃችሁ ወደፊት ቀጥሉ ።
አንዳንድ የመንግስትና ህዝብን አደራ ወደ ጎን በማድረግ የግል አመለካከታቸውን በስልጣን ለማስፈፀም የሚሄዱና እንዲሁም የተጣለባቸውን ህዝባዊ አደራ በጥቅም የሸጡ አካላት የሚያደርሱባችሁን ግፍ ተጋፍጣችሁ ለአላማችሁ ፅኑ ። እንደነዚህ አይነት አካላትን እስከመጨረሻ በመታገል ማንነታቸው ለፍትሕ የቆሙ የመንግስት አካላት እንዲያውቁዋቸው ለማድረግ ጥረት አድርጉ ። ምክንያቱም በሁሉም አካባቢ የተሰጣቸውን የህዝብ አደራ ለመወጣት ቆርጠው የቆሙ አሉና መፍትሄ ታገኛላችሁ ።
አላህ ቁርኣንና ሐዲስን በሰለፎች ግንዛቤ የበላይ ያድርግልን ።
http://t.me/bahruteka | 2 535 |
| 16 | ቂርአቱ የሚጀመረው ነሃሴ 20//2018 ነው።
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱሏህ
ውድ ተማሪዎች ከዚህ በፊት ይጀመራል ያልናችሁ ቋሚ የደርስ ፕሮግራም ከቀናት በኋላ ይጀመራል።
ፕሮግራሙ
➊ኛ የአረብኛ ቋንቋ ትምህርት
=> ፅሁፍ ለጀማሪዎች
=> የነህው ትምህርት
=> የሶርፍ ትምህርት
❷ኛ አጫጭር ኪታቦች
=> የአቂዳ ኪታቦች
=> የመንሃጅ ኪታቦች
=> የፊቅህ ኪታቦች
❸ የቁርኣን ትምህርት
👉 በዚህ ፕሮግራም ስር እህቶች በእህቶቻቸው ብቻ የሚማሩ ይሆናል። ይህም የተለያዩ ደረጃዎች ላይ ላሉ ሁሉ የተመቻቸ ነው።
=> የቃኢደቱ-ኑራንያህ
=> የቁርኣን ነዞር
=> የተጅዊድ ህግጋት
✅ በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ እቅዱ ያላችሁ በሚከተለው አድራሻ ፈጥናችሁ ተመዝገቡ!
👇👇👇
@Medresaa_bot
🌐 ስለ ደርሱ ተጨማሪ ማብራሪያዎችን ለማግኘት እና ሀሳብ ለመስጠት የሚከተለውን ግሩፕ ተቀላቀሉ!
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/arabic_grammer_m | 11 854 |
| 17 | #መውሊድን_ከተለያዩ_ሸሪዓዊ
ምክንያቶች አንጻር አላከብርም!
ከብዙው በጥቂቱ 20 (ሀያ)
ምክንያቶችን ልጥቀስ።
➚➚➚➚➚➚➚
❶ኛ, #መውሊድ በሸሪዓችን #መሠረት የሌሌለው ማለትም #ቁርኣንና_ሐዲሥ ላይ ያልተደነገገ አዲስ #መጤ ፈጠራ ስለሆነ፣
❷ኛ, #መውሊድ መከበር ያለበት ጠቃሚ #ኢስላማዊ በዓል ሁኖ በነበር፤
ከእኛ #በፊት ያሉ ደጋግ የነቢዩ ﷺ
➼ ባለቤቶች፣
➼ ባልደረቦች (ሶሐቦች)፤
➼ ታቢዒዮችና
➼ አትባዑ ታቢዒዮች #ባከበሩት ነበር።
#ስለዚህ ያኔ ለነርሱ #ዲን ያልነበረው፤
ዛሬ ለእኛ #ዲን አይሆንምና አላከብርም!
❸ኛ, ከነዚህ #ትውልዶች በኋላ የመጡ #ታላላቅ የኢስላም #ሊቃውንቶችና #ሙሐዲሦች ስላላከበሩት፣
❹ኛ, #መውሊድን የጀመሩት ሶሐቦችን #በመሳደብ በግንባር ቀደምትነት የሚታወቁት #ሺዓዎች የሆኑት ፋጢሚዶች ስለሆኑ፣
❺ኛ, አንድ ነገር በራሱ #መልካም ከሆነና የተጀመረበት #አላማ ለመልካም ከሆነ፤ ምንም እንኳን #ጀማሪዎቹ መጥፎ ቢሆኑም ነገሩ #ያልተፈቀደ ላይሆን ይችላል። #መውሊድን እነዚህ የፋጢሚይያህ #ሺዓዎች የጀመሩበት ዐብይ ምክንያት ግን፤ #በዋናነት የራሳቸውን #ብልሹ እምነት በሌላው ላይ ለመጫን #መሸጋገሪያ ድልድይ ይሆናቸው ዘንድ እና ከሱንናው #ማኅበረሰብ ጋር ያለውን #ልዩነት አጥብበው በፖለቲካው ዘርፍም የስልጣን #አድማሳቸውን ለማስፋት ነበር። ስለዚህ ለዚህ እኩይ #የሺዓ አላማ የተጀመረን #መውሊድ አላከብርም!
❻ኛ, #መውሊድ በሸሪዓችን #መሠረት የሌለው #በዓል ስለሆነ፤ ከፊሉ #ሙስሊም አከብራለሁ ሲል፣ ከፊሉ ደግሞ አላከብርም ሲል፤ #አንድ መሆን የሚገባውን #ሙስሊም በዚህ ክፍተት ብቻ #እንዲከፋፈል ጉልህ ሚና የተጫወተ #መጤ በዓል ነው።
#መልካም ነገር ቢሆን ኑሮ፤ #ሙስሊሙን አንድ ያደርጋል እንጅ አይከፋፍልም ነበር!
❼ኛ, #እስልምናዬ ሙሉ መሆኑ ተነግሮኛል። #ስለሆነም በውስጡ ያልተደነገገን ነገር በራሴ እሳቤ #አልጨምርም!
❽ኛ, #መውሊድ ጠቃሚ በነበር #አላህና መልዕክተኛው ﷺ በነገሩን ነበር። እነርሱ ለእኛ ከእኛ ይልቅ #ይበልጥ ጠቃሚውን ያውቃሉና!
❾ኛ, #ከመልዕክተኛው ሱንና ውጭ የሆነን #ነገር መፈጸም፤ እርሳቸው #ባላዘዙበት ነገር ወደ ርሳቸው #ለመቃረብ መሞከር፤ #እርሳቸውን መውደድ ሳይሆን #መቃረን ስለሆነ፣
❿ኛ, #በሸሪዓው ውስጥ የሌለን #መውሊድን ማክበር፤ #ሸሪዓውን ጉድለት #ያለበት ስለሚያስመስል፣
⓫ኛ, #በእስልምናችን ውስጥ የተደነገጉ ሁላችንንም መላውን #ሙስሊም አንድ የሚያደርጉን ሁለት እውቅ #አመታዊ ዒዶች ስላሉን፣
⓬ኛ, #መውሊድ በራሱ ቢድዓ ከመሆኑም #ባሻገር፤ በሚከበርበት እለት ደግሞ ከርሱ የባሱ #ቢድዓዎች ይፈጸማሉ።
⓭ኛ, #በመውሊድ እለት ከራሱ ተጨማሪ ከሚታከሉ #ቢድዓዎች ባሻገር፤ #ከእስልምና ሊያስወጡ የሚችሉ #ሽርኮች መፈጸሚያ #ማዕከል በመሆኑ፣
⓮ኛ, መልዕክተኛውን ﷺ #መውደድ ማለት ሱናቸውን #በቀንጣጤ አጥብቆ መያዝና ትዕዛዛቸውን #መፈጸም እንጅ፤ ልደታቸውን #ማክበር ባለመሆኑ፣
⓯ኛ, የርሳቸውን #ልደት ማክበር፤ #አላዋቂዎች ደግሞ የሚወዱትን ሰው #ልደት እንዲያከብሩ በር #ከፋች በመሆኑ፣
⓰ኛ, እፁብ #ድንቅ የሆኑ #በሸሪዓችን የተደነገጉ ብዙ ኢስላማዊ #እሴቶች እያሉን፤ ቅንጣት #መሠረት የሌለውን በዓል መሠረት ያለውን #አስመስለን ስናከብር፤ #ሙስሊም ላልሆኑ ወገኖች መተላለፍ ያለበትን #መልዕክት ወደ ጎን በመተው #መተላለፍ የሌለበትን መልዕክት #እያስተላለፍንላቸው በመሆኑ፣
⓱ኛ, #መውሊድ የሚከበርበት ረቢዑል አወል 12፤ #ትክክለኛው የልደት ቀናቸው ባለመሆኑ #እንዳውም ይህ ቀን በትክክል #የሞቱበት ቀን ነበር። ስለዚህ #ልደታቸውን ነው ወይስ #ሞታቸውን እያከበርን ያለነው?! #የሚከበርበት ቀን ራሱ የተገደበና በውል #የታወቀ አለመሆኑ በራሱ፤ #መውሊድ በሸሪዓችን #መሠረት የሌለው አዲስ #መጤ ቢድዓ ለመሆኑ #አመላካች ነው። #ሁሉም ሸሪዓዊ ትዕዛዛት #የአፈጻጸም ህግና ደንብ አላቸው። እርሱ (መውሊድ)ግን የለውም፣ #ምክንያቱም ሰዋዊ ስለሆነ!!!
⓲ኛ, #በመውሊድ ምክንያት ሙስሊሙ ማኅበረሰብ #ሲከፋፈል የሚያይ፤ በቂ #እውቀት የሌለው #ሙስሊም ማኅበረሰብ #በእስልምናው እንዲጠራጠር #ሰበብ ስለሚሆን።
⓳ኛ, #ሙስሊሞች በሸሪዓቸው ባልተደነገገው #የመውሊድ በዓል ሳቢያ ሲጨቃጨቁ፤ #አልፎም ለድብደባና ለሰፊ ልዩነት ሲዳረጉ የሚያይ፤ #እስልምናን ለመቀበል ጉጉት የነበረው #ሙስሊም ያልሆነ ወገን፤ #እስልምናን እንዲጠላና እንዲርቅ፣ እንዲሁም #ሙስሊሞችን በመጥፎ ምስል እንዲስል #ሰበብ ስለሚሆን፣
⓴ኛ, #እስልምና እንድንተገብራቸው ያዘዘን ብዙ በጎ #ተግባራት አሉ። እንኳን አዲስ #ተጨማሪ ነገር ልፈጥር ይቅርና፤ እነዚያን #መሠረት ያላቸውን የታዘዝኳቸውን ሰናይ #ተግባራት አሟልቼ የማልፈጽም ስለሆንኩ እንኳን ፈጽሜ #የማልጨርሳቸውን ብጨርሳቸው እንኳን፤ እነርሱኑ #በተደጋጋሚ እፈጽማለሁ እንጅ ሌላ አዲስ #ፈሊጥ አላመጣም። ይህን የማደርገው #መልዕክተኛውን ﷺ ስለምወድ #እንጅ ስለምጠላ አይደለም።
𝓬𝓸𝓹𝔂
<===/====/====/====/===>
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
<\\\> | 17 447 |
| 18 | በአሁኑ ሰዓት
አብዛኛው ሰው አላህን ፍራ
ከምትለው...
ካሜራ አለ ተጠነቀቅ ብትለው
ይበልጥ ይጠነቀቃል‼
ሱብሀነላህ!!
https://t.me/aaussj
https://t.me/aaussj | 3 394 |
| 19 | የ ቃዒደቱ አንኑራኒየህ ደርስ..
~
ተ
ጀ
መ
ረ
🎙በወንድም አቡ ጃቢር ዓሊይ ብን ዐብዱላህ አላህ ይጠብቀው!
☞ የስርጭት ሊንክ
📱👇👇👇👇
https://t.me/Quraanuunaa?videochat=fe5ab2f402423c3653 | 234 |
| 20 | የጁምዓ ኹጥባ(ምክር)
የቢድአ አደገኝነት
እና
እና የመውሊድ ቢድአነት
ኡስታዝ አቡ ሙስ0ብ ሰዕድ አብዱለጢፍ (ሀፊዘሁሏህ)
ነሀሴ 8 - 2018
ባህርዳር ቡኻሪ መስጂድ
የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ
https://t.me/alateriqilhaq | 4 544 |
