cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Ethiopian Orthodoxs Daily

በቤተ ክርስቲያናችን በየቀኑ የሚታሰብ ቅዱሳን፤ የመፅሐፍ ቅዱስ ምንባባት ፤ ብሂለ አበው እና አስተማሪ የሆኑ መንፈሳዊ ፅሁፎች ያገኙበታል::Share https://t.me/ethiopianorthodoxs //like page on facebook fb.me/ethiopianorthodxs ለሀሳብ አስተያየትዎ @Yakob520

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
6 375
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
+230 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ዳግም ትንሣኤ፦ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሤኤው ሳምንት ለሐዋርያው ቶማስ ተገለጠለት:: የዛሬው ቀን እንደ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አጠራር ዳግም ትንሣኤ ይባላል። በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ በዛሬው ዕለት የክርስቶስን ዳግም ትንሣኤ በማየታችን የእግዚአብሔር ልጅ የመባልን ክብር ያገኘንበት ቀን ነውና በቤተ ክርስቲያን ተገኝተን ልንከብር ያስፈልጋል። አባት ሆይ! ከአባቶቻችን ምስጋናን እንደ ተማርን ስለ ምሥጢረ ሥላሴ በዳግም ትንሣኤ አወቅን ተረዳን፤ እንዲሁም እናምናለን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ሒዱ አሕዛብን ሁሉ አስተምሩ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው እንዳለ የምናምንባት ሃይማኖት ይህች ናት ከእርስዋ በቀር ለዘላለሙ ሌላ አንሻም። ካህናት ሆይ እንኳን ደስ አለችሁ! በዛሬው ዕለት አምላካችሁ እኛን የማጥመቅ፣ የማሰርና የመፍታት ሥልጣን፣ ክህነት የመስጠትን ሥልጣን፣ የመባረክን ሥልጣን፣ የመሾም የመሻር ሥልጣን፣ የመቀደስ የመፈወስ ሥልጣን የተሰጣችሁ ቀን በዛሬዋ ዳግም ትንሣኤ ናት እና ኑ በቤተ መቅደስ ተሰባስበን ደስታ እናድርግባት። ምእመናን ሆይ! ሀብተ ወልድ እና ስመ ክርስትና የምናገኝበትን የምሥራች ጌታ ለሐዋርያት የሰጠበት ቀን በዳግም ትንሣኤ ነውና ኑ በመቅደሱ ተሰባስበን በደስታ በሐሴት እናመስግን። ሌላም በዛሬው ዕለት ለሐዋርያው ቶማስ በእጆቹና በእግሮቹ ውስጥ የችንካሮቹን ምልክት አሳየው የቶማስንም እጅ ይዞ በመለኮታዊ ጎኑ ውስጥ አኖረውና በጦር የተወጋበትን ቦታ አሳየው ቶማስም ጌታዬና ፈጣሪዬ መነሣትህን አመነኩ አለ:: ጌታችንም ብታየኝ አመንክብኝ የሚመሰገንስ ሳያየኝ የሚአምንብኝ ነው ብሎ መለሰለት:: በትርጓሜ ወንጌል እንዲህ ይላል ቶማስ በመድኃኒታችን ጎን ውስጥ እጁን በአስገባ ጊዜ እጁ በመለኮት እሳት ተቃጠለ በመለኮቱም ደግሞ በታመነ ጊዜ እጁ ከመቃጠል ዳነች:: ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በሐዋርያቶች ጸሎት በታጋዮች ጻድቃንም በድል አድራጊዎች ሰማዕታት ጸሎት ይልቁንም አምላክን በወለደች  በክብርት ድንግል ማርያም በአማላጅነቷ ይምረን ዘንድ ወደርሱ እንለምን ለዘላለሙ አሜን:: መልካም ዕለተ ሰንበት። 🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸       🌸 የምሥራች 🌸 ⛪️ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን 🙏በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን ⛪️አሰሮ ለሰይጣን 🙏አግኣዞ ለአዳም ⛪️ሰላም 🙏እምይእዜሰ ⛪️ኮነ 🙏ፍሥሐ ወሰላም 🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️
نمایش همه...
ግንቦት አንድ በዚህችም ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች:: እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት:: ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ:: ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ በዚያ ወራት የመካኖችን መባዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበር:: እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኀዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር:: ሰውን የሚወድ እግዚአብሔር ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ኀሳባቸውን ተመለከተ:: ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው:: በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት:: ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት:: የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርግ ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች:: ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች ስሟንም ማርያም ብላ ሰየመቻት ትርጓሜውም እመቤት ማለት ነው:: ደግሞም ሀብትና ሥጦታ ማለት ነው:: በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ናት:: ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነት ያገኘንባት:: እንግዲህ እዚህ ጋር ልብ ይሏል:: በዚህ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ የኛ ልጅነት የኛ የመዳንችንን መንገድ እግዚአብሔር እንዴት እንዳከናወነልን እንረዳለን:: እግዚአብሔር ሰውን ሲያድን ማዳኑን የፈጸመው እጅግ በጣም ልዩ በሆነ ሁኔታ ነው:: ይህም ገናናነቱን ከእኛ ታናሽነት ጋር አዋሕዶ፤ ከሃሊነቱን ከእኛ ነፃነት ጋር አስማምቶ በመሆኑ ነው:: ይህ ማለት ምን ማለት ነው? ሊያድነን ሲነሣ እንዲሁ በማንኛውም መንገድ ቢያድነን ታላቅ ቸርነትና ደግነት ሆኖ ሳለ እርሱ ግን ከዚያም በላይ በሆነ መንገድ እኛን አሳትፎ ፈቃዳችንን ተቀበሎ አስፈቅዶ አስወድዶ ያዳነን:: እርሱ ሁሉን ማድረግ ስለሚችል ብቻ ያለ እኛ ፈቃድ ሱታፌ እንዲሁ አፍአዊ በሆነ ሁኔታ እና ያለ ፈቃዳቸው አላዳነንም:: ባሕርያችንን ሲዋሐድም ያለ እኛው ፈቃድና ሱታፌ አላደረገውም:: የሚጠቅመንን የመዳናችንን ነገር ሲፈጽም እኛን አስወድዶና አሳትፎ ነው:: አካላዊ የእግዚአብሔር ቃል እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት ሲወርድ መከራ ተቀብሎ እኛን የሚያድንበትን መሣሪያ የወሰደው ከእኛው መዳኑ ከሚያስፈልገንና ከሚደረግልን ከሰዎች ነበር:: ይህ እንዲሆን ደግሞ ሰዎችን የሚወክልና እኛን ሁሉ ወክሎ የሚሳተፍ አንድ ሰው ያስፈልግ ነበር:: በዚህም ያ የሚያስፈልግ አንድ ሰው በዛሬዋ ቀን የተወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት:: በእወነት ምስጋና ይድረሳትና። ከዚህ በኋላ ነው እንግዲ የነቢያት ትንቢታቸው ከተፈጻሚነት የደረሰው:: ታዲያ የዛሬውን በዓል ስናከብርና ተድላ ደስታ ስናደርግ ከመንፈሳዊነት ሳንወጣ ልንጠነቀቅ ይገባል:: ይህን በዓል ስናከብርም ሌሊት በቤተ ክርስቲያን በማኅሌት÷ በዝማሬ÷ ጠዋት በኪዳንና በቅዳሴ÷ ታምሯን በመስማት÷ ወንግል በመማር ነው:: ክርስቲያኖች ከዚህ የወጣ ባዓል የላቸውም:: ብዙዎች የእኛን መንፈሳዊ በዓል ይዘው የራሳቸውንና የቤታቸውን ጣጣ ይዘውና አስታከው መንፈሳዊ በዓላ ላይ ለጥፈው ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንም ከመንፈሳዊነታችን ጋርም የሚፃረር ነገር ሲፈጽሙ ይታያል ይህ አግባብ አይደለም:: የበግና የፍየል ከለር እየመረጡ÷ ቄጣና ፈንዲሻ እየረጩ÷ የቡና አተላ እየገለበጡ የሚከበር መንፈሳዊ በዓል የለም:: አስፀያፊም የተወገዘም ግብር ነው። እስኪ አንድ በዓለም ያለ ሰው ልደቱን ሲያከብር ወይ ሲደግስ የበግ ከለር መርጦ የሚያርድ ማን አለ? ወይ ቡና እያንቃረረ ቂጣና ፈንዲሻ በየጥጋ ጥጉ የሚጥል ማን አለ? ታዲያ እንደዚህ ያለን ኮተታ ኮተት ከየት የመጣ ነው:: የኛ አይደለም እንዲህ ያለ ነገር እንዲህ የሚያደርጉ ካሉ ፈጥነው ንሰሐ ሊገቡና ከክርስቲያኖች ማኅበር ሊገቡ ይገባል:: የእመቤታችንን የልደቷን በዓል ግን የምናከብረው በዝማሬ÷ በማኅሌት÷ በኪዳን÷ በቅዳሴ ጊዜ ሥጋወ ደሙ እየተቀበልን÷ ወንጌልን እየተማርን÷ የተራበ እያበላንና የታረዘ እያለበስን እየዘመርን ነው:: ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን። 🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️
نمایش همه...
"እንግዲህ ሰው በመሆኑ ተሰቀለ፤አምላክ በመሆኑ ተነሣ፤ እኛም በመነሣቱ እግዚአብሔር የእግዚአብሔርም የባሕርይ ልጅ በእውነት እንደሆነ እናምናለን።" (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቄርሎስ) መልካም የትንሣኤ በዓል
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
በሰሙነ ህማማት ወቅት የምንሰማቸው እንግዳ ቃላትና ትርጉማቸው በግብረ ሕማማት ውስጥ በግዕዝም ሆነ በኋላ በአማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የእብራይስጥ፣ የቅብጥና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ። የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፦ #ኪራላይሶን፦ ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ < ኪርዬ ኤሌይሶን> ነው። #ኪሪያ ማለት እግዝእትነ / እመቤታችን" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ / ጌታ ሆይ / አቤቱ" ማለት ነዉ፡፡ "ኤሌይሶን" ማለት ደግሞ "ማረን / ይቅር በለን" ማለት ነዉ ፡፡ ትርጉሙም "አቤቱ ማረን" ማለት ነዉ፡፡ "ኪራላይሶን" የምንለዉ በተለምዶ ነዉ፡፡ ይኸዉም "ኪርዬ" ከሚለዉ "ዬ" ኤሌይሶን" ከሚለዉ ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸዉ በአማርኛ "ያ"ን ፈጥረዉ ነዉ፡፡ #ናይናን፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሐረነ፤ማረን" ማለት ነው። #እብኖዲ ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "አምላክ" ማለት ነው። "እብኖዲ ናይናን" ሲልም " አምላክ ሆይ ማረን" ማለቱ ነው። #ታኦስ ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ጌታ፣አምላክ" ማለት ነው። #ማስያስ ፦ የእብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሲህ" ማለት ነው። #ትስቡጣ ፦ "ዴስፓታ" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም "ደግ ገዥ" ማለት ነው። #አምነስቲቲ_ሙኪርያቱ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግስትከ- አቤቱ በመንግስትህ አስበኝ" ማለት ነው። #አምነስቲቲ_ሙዓግያ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ " ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግስትከ -ቅዱስ ሆይ በመንግስትህ አስበን" ማለት ነው። #አምነስቲቲ_ሙዳሱጣ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ " ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግስትከ -የሁሉ በላይ የሆንክ ሆይ በመንግስትህ አስበን " ማለት ነው።
نمایش همه...
04:03
Video unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
03:06
Video unavailableShow in Telegram
ሚያዝያን ለመቄዶንያ! ወራችንን በመልካም ስራ እንጀምር
نمایش همه...