fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 322 مشترک است و جایگاه 6 154 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 360 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 322 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 22 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 507 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 11 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 49.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.09% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 0 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 875 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 23 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 322
مشترکین
+1124 ساعت
+1077 روز
+50730 روز
آرشیو پست ها
"አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ።" ሉቃ 1፡28 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድ
"አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ።" ሉቃ 1፡28 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

“ተቀጸል  ጽጌ” (አበባን  ተቀዳጅ)  በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመከበር ላይ ይገኛል። በዐፄ  ዳዊት ዘመን  ኢየሱስ  ክርስቶስ  የተሰቀለበት ግማደ  መስቀሉ  ወደ ኢትዮጵያ የገባበት   “ተቀጸል  ጽጌ” (አበባን  ተቀዳጅ)  በዓል  መስከረም ፲ ቀን በየዓመቱ   ይከበራል፡፡  በዘንድሮው ዓመትም በዓሉ ሲከበር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት  ጽ/ቤት   ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ  ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ  ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሐላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ካህናት ምእመናን የሰንበት ትምሕርት ቤት ዘማርያን  ተገኝተዋል። በክብረ በዓሉ ያሬዳዊ ዜማ በአጫብር በሊቃውንት ቀርቧል። የየረር ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ዘማርያንም የአጫብር ወረብ አቅርበዋል።  “ተቀጸል  ጽጌ” (አበባን ተቀዳጀ) የሚለውን መዝሙር የዜማን የቅኔ መሥራች የሆነው ኢትዮጵያዊው ቅዱስ  ያሬድ  ነው። የተመሠረተውም  በ፮ኛው መ/ክ/ዘ መጀመሪያ በዐፄ  ገብረ  መስቀል  ዘመነ መንግሥት ነው።  በዚሁ መሠረት የክረምቱና የልምላሜው ጊዜ አልፎ የአበባውና የፍሬው ጊዜ በሚተካበት በመስከረም ፳፭ ቀን ቅዱስ ያሬደ ውደ ንጉሡ ዙፋን ቀረቦ “ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ዐጼጌ” በማለት ዘምሯል፡፡ ዐፄ  ገብረ  መስቀል  ክረምቱ  አልፎልሃልና  አበባን  ተቀዳጅ፣  አበባን  ተላበስ  እያለ  ያወድሰው  የነበረው  በዓላዊ  ትውፊት  እየተቀባበለ  እስከ  ፲፭ኛው  ምዕት ዓመት ደርሶ ነበር፡፡ በኋላም ዐፄ  ዳዊት   የጌታችን  ግማደ  መስቀል ከኢየሩሳሌም አስመጥቶ   መስከረም ፲ ቀን  ወደ ኢትዮጵያ  በመድረሱ  ግማዱም  በንጉሡ  ምክንያት  በመምጣቱ  “ዐፄ  መስቀል” እየተባለ  መከበር  ሲጀምር፣  የ፳፭ኛው  ቀን  የአበባው  በዓልም  በ፲፭  ቀን  ወደ ኋላ  በማፈግፈግ   በአንድነት የዐፄ መስቀልና ተቀጸል ጽጌ  እንዲከበር ተወስኖ   እስካሁን ድረስ በታላቅ ሥነ ሥርዐት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ©eotc tv

በዚህች ቀን ከእመቤታችን ስዕል ተአምር ተገለጠ! ጼደንያ ማርያም! እንኳን አደረሳችሁ! https://www.tiktok.com/@eotc_gssu/video/7416622754000063775

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 የ2017 ዓ.ም የመስቀል በዓል ጥናት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

የተማሪዎች የምረቃ መርሐግብር በማዕከላዊ ጎንደር (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) መስከረም 06/01/2017 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት በደብረ ሣኅል ቅዱስ ሩፋኤል ወአቡነ ሐራ ድንግል ቤ
+4
የተማሪዎች የምረቃ መርሐግብር በማዕከላዊ ጎንደር (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) መስከረም 06/01/2017 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት በደብረ ሣኅል ቅዱስ ሩፋኤል ወአቡነ ሐራ ድንግል ቤ/ክ ውሰጥ የሚገኘው የውሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት በ2016 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ሥርዓተ ት/ት መሰረት የ1ኛ እና የ2ኛ ክፍል ትምህርት የተማሩ ልጆችን አስመረቀ። በመርሐ ግብሩ ከማዕከላዊ ወደ ትልቆች ክፍል ያለፉ ልጆችን የምስክር ወረቀት የመስጠት መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን በጉባኤው የማዕ/ጎ/ዞ/ሃ/ስ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ ሊቀ አዕላፍ ብርሃኑ ፍትሕአምላክ: የማዕ/ጎ/ዞ/ሃ/ስ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ ዲያቆን አንዳርጋቸው እንዳለው :የደብሩ ሰ/ጉ/አባላትና ካህናት አገልጋዮች እንዲሁም የአካባቢው ምዕመናን በተገኙበት በቀን 05/01/2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ተከናውኗል:: በዚሁም ዕለት በዓለማዊ ት/ት ደረጃ ለያዙ: የ12ኛ ክፍል መግቢያ ፈተና ላለፉ እንዲሁም ሰ/ት/ቤቱን በሐሳብ እና በገንዘብ ላገዙ ባለ ድርሻ አካላት ሰንበት ት/ቤቱ እውቅና ሰጥቷል:: የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ይከታተሉ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 05/0
+4
በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተከናወነ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 05/01/2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2016 ዓ.ም የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ መርሐ ግብር የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል አባ ተስፋዬ እማምሰው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ዋና ክፍል ኀላፊ መጋቤ ኅሩያን ቀሲስ ሐዲስ ኪዳነ ማርያም በትምህርታቸው የደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በተገኙበት በዛሬው ዕለት በኆኅተ ሰማይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ ተከናውኗል።         በዕለቱም ከየአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለወጡ ተማሪዎች የካርድ እና የምስክር ወረቀት የመስጠት መርሐ ግብር እንደ አጠቃላይ ደረጃ ለወጡት ተማሪዎች እና በንቃት ሲያገለግሉ ለነበሩ አገልጋዮች ደግሞ ሽልማት እና እውቅና የመስጠት መርሐ ግብር እንደተከናወነም ተገልጿል።                    በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል አባ ተስፋዬ ከ1ኛ-4ኛ ክፍል የታተሙ መጻሕፍትን ለሰ/ት/ቤቶች ያስረከቡ ሲሆን የሥርዓተ ትምህርቱን አተገባበር በማድነቅ በቀጣይ ለሚሰራውም ትውልድን የመቅረጽ ስራ ሀገረ ስብከቱ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ በመግለጽ መርሐ ግብሩን በፀሎት ዘግተዋል።    መረጃው የአንድነቱ ትምህርት ክፍል ነው። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ የሥርዓተ ትምህርት የግንዛቤ መስጫ መርሐ ግብር ተከናወነ። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት (መስከረም 5/2017 ዓ.ም) በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
+4
በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ  የሥርዓተ ትምህርት የግንዛቤ መስጫ መርሐ ግብር ተከናወነ። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት (መስከረም 5/2017  ዓ.ም) በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ መንበረ ጵጵስና እየተከናወነ የሚገኘው ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር  በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተዘጋጀውንና በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ ትግበራ ላይ በሚገኘውን ሥርዓተ ትምህርት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በሥልጠናው የሀገረ ስብከቱ ማደራጃ መምሪያ መ/ሰ አክሊሉ  የሀገረ ስብከቱ  የሰንበት ት/ቤት አንድነት  ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ መምህር መኮንን  የአድባራት አስተዳዳሪዋች የሰበካ ጉባዬ አባላት  የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮችና የተለያዩ ማኅበራት የተሳተፉበት ነው። ሥልጠናው የተሰጠው በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አዘጋጅነት በ2016 ዓ.ም በክረምት ሥልጠና ሀገረ ስብከቱን ወክለው በተሳተፉ መምህራን ሲሆን የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ለ2017 ዓ.ም የትምህርት  ዓመት እንዲረዳ የመማርያ መጻሕፍት ግዥ በመፈፀም በሥርጭት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በደሴ ከተማ ለሚገኙ ከሁሉም አድባራት ለተወጣጡ የሰ/ት/ቤት መምህራን እንዲሁም የስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች እና የመጻሕፍት መምህራን አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክ
+3
በደሴ ከተማ ለሚገኙ ከሁሉም አድባራት ለተወጣጡ የሰ/ት/ቤት መምህራን እንዲሁም የስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች እና የመጻሕፍት መምህራን አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክህነት ለ20ቀናት ሥልጠና በወሰዱ መምህራን ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሥልጠና በደሴ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አማካኝነት በደሴ ቅዱስ ገብርኤል ካቴደራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ መስጠት ተጀምሯል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 04/01/2017 ዓ.ም በሥልጠናው የተገኙ የወረዳው የሰ/ት/ቤቶች ክፍል ሐላፊ ፣ የስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች እና የመጻሕፍት መምህራን ፣ የሰ/ት/ቤት መምህራን እና የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አመራሮች ተገኝተዋል። በመጀመሪያ ቀን የግማሽ ቀን ውሎ በሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ ዙሪያ እንዲሁም በስልጠናው ለተገኙ አካላቶች መልእክት በዲ/ን ሀብታሙ ለማ የደቡብ ወሎ ሃ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ተሰጥቶ በወ/ም ሚኪያስ አወቀ ለሰልጣኞች የአራት ቀን ውሎ አጠቃላይ ገለጻ ተሰጥቶ በወ/ም መስፍን አበባው እና በወ/ም ኢዩኤል ሞገስ አጠቃላይ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሥልጠና ተሰጥቷል። ከሻይ እረፍት በኋላ በወ/ም ሚኪያስ ዘነበ እና በእህት ቃልኪዳን ሰይድ የመሠረተ ሃይማኖት(ዶግማ) ክፍለ ትምህርት ለሰልጣኞች ተሰጥቶ የግማሽ ቀን ሥልጠናው ተጠናቋል። ሥልጠናው ለ 4 ቀን የሚቆይ ይሆናል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረ
+3
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተከናወነ።

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 እንኳን ለዘመነ ማቴዎስ በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዘመናትን ታቀዳጃለህ።" መዝ 64(65):11 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 እንኳን ለዘመነ ማቴዎስ በሰላም አደረሳችሁ! "በቸርነትህ ዘመናትን ታቀዳጃለህ።" መዝ 64(65):11 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! መልካም አዲስ ዓመት! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

በመጨረሻም አዲሱ ዘመን በሃይማኖት መንፈስ ግጭትን በውይይት፤ መለያየትን በአንድነት፤ አለመግባባትን በዕርቅ ፈትተን በመታደስ ማማ ላይ የቆመ ማኅበረ ሰብን ለመገንባት ሁላችንም ጥረት እንድናደርግ በእግዚአብሔር ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ አዲሱ ዓመት የሰላም የዕርቅ የእኩልነትና የአንድነት ያድርግልን፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!! አሜን:: አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ