የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 628 مشتركاً، محتلاً المرتبة 5 948 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 308 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 628 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 556، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 21، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 27.33%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.34% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 993 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 510 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 14.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 08 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 628
المشتركون
+2124 ساعات
+1317 أيام
+55630 أيام
أرشيف المشاركات
+2
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ተገኝተው ከምዕራብ ክፍለ ከተማ ገዳማትና አድባራት ተዋጣጥተው ለመስቀል ደመራ በዓል በዝግጅት ላይ ለሚገኙት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት መልእክትና አባታዊ ቡራኬ አስተላለፉ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 14/01/2016 ዓ.ም
በመልእክታቸውም ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እግዚአብሔር ለአገልግሎት ጠርቶ ስላከበራችሁ ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን እንኳን ደስ አላችሁ ብለው ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት ልጆቿ ተከብራ በልዩ ጣዕመ ዜማ ታጀባ በማንኛውም ክብረ በዓል ላይ እግዚአብሔር ሲመሰገን ማየት እጅግ ደስ ያሰኛልና በዓሉ የሰላም በዓል የድኅነት በዓል እንደመሆኑ ለሰላም ትልቅ ትኩረት በመስጠት ከሚመለከታቸው ክፍሎችም ጋር በጋራ በመስራት ሁላችን ዐይን እና ጆሮ ሆነን በስማችን ክፉ ሥራን በመስራት የቤተክርስቲያንን ስም የሚያጠለሽ እንዳይኖር እየዘመርንም ተግቶ ሥራ መሥራት ይገባል ብለዋል። የአደባባይ በዓል በመሆኑም የሚመጣውም ሁሉ የሚማርበት እንዲሆን የአደራ መልእክታቸውንም አክለዋል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
“ተቀጸል ጽጌ” (አበባን ተቀዳጅ) በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመከበር ላይ ይገኛል።
በዐፄ ዳዊት ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት “ተቀጸል ጽጌ” (አበባን ተቀዳጅ) በዓል መስከረም ፲ ቀን በየዓመቱ ይከበራል፡፡ በዘንድሮው ዓመትም በዓሉ ሲከበር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሐላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ካህናት ምእመናን የሰንበት ትምሕርት ቤት ዘማርያን ተገኝተዋል።
በክብረ በዓሉ ያሬዳዊ ዜማ በአጫብር በሊቃውንት ቀርቧል። የየረር ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ዘማርያንም የአጫብር ወረብ አቅርበዋል። “ተቀጸል ጽጌ” (አበባን ተቀዳጀ) የሚለውን መዝሙር የዜማን የቅኔ መሥራች የሆነው ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ነው። የተመሠረተውም በ፮ኛው መ/ክ/ዘ መጀመሪያ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት ነው። በዚሁ መሠረት የክረምቱና የልምላሜው ጊዜ አልፎ የአበባውና የፍሬው ጊዜ በሚተካበት በመስከረም ፳፭ ቀን ቅዱስ ያሬደ ውደ ንጉሡ ዙፋን ቀረቦ “ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ዐጼጌ” በማለት ዘምሯል፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል ክረምቱ አልፎልሃልና አበባን ተቀዳጅ፣ አበባን ተላበስ እያለ ያወድሰው የነበረው በዓላዊ ትውፊት እየተቀባበለ እስከ ፲፭ኛው ምዕት ዓመት ደርሶ ነበር፡፡ በኋላም ዐፄ ዳዊት የጌታችን ግማደ መስቀል ከኢየሩሳሌም አስመጥቶ መስከረም ፲ ቀን ወደ ኢትዮጵያ በመድረሱ ግማዱም በንጉሡ ምክንያት በመምጣቱ “ዐፄ መስቀል” እየተባለ መከበር ሲጀምር፣ የ፳፭ኛው ቀን የአበባው በዓልም በ፲፭ ቀን ወደ ኋላ በማፈግፈግ በአንድነት የዐፄ መስቀልና ተቀጸል ጽጌ እንዲከበር ተወስኖ እስካሁን ድረስ በታላቅ ሥነ ሥርዐት በመከበር ላይ ይገኛል፡፡
©eotc tv
በዚህች ቀን ከእመቤታችን ስዕል ተአምር ተገለጠ!
ጼደንያ ማርያም! እንኳን አደረሳችሁ!
https://www.tiktok.com/@eotc_gssu/video/7416622754000063775
+4
የተማሪዎች የምረቃ መርሐግብር በማዕከላዊ ጎንደር
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) መስከረም 06/01/2017 ዓ.ም
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት በደብረ ሣኅል ቅዱስ ሩፋኤል ወአቡነ ሐራ ድንግል ቤ/ክ ውሰጥ የሚገኘው የውሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት በ2016 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ሥርዓተ ት/ት መሰረት የ1ኛ እና የ2ኛ ክፍል ትምህርት የተማሩ ልጆችን አስመረቀ።
በመርሐ ግብሩ ከማዕከላዊ ወደ ትልቆች ክፍል ያለፉ ልጆችን የምስክር ወረቀት የመስጠት መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን በጉባኤው የማዕ/ጎ/ዞ/ሃ/ስ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ ሊቀ አዕላፍ ብርሃኑ ፍትሕአምላክ: የማዕ/ጎ/ዞ/ሃ/ስ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ም/ሰብሳቢ ዲያቆን አንዳርጋቸው እንዳለው :የደብሩ ሰ/ጉ/አባላትና ካህናት አገልጋዮች እንዲሁም የአካባቢው ምዕመናን በተገኙበት በቀን 05/01/2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ተከናውኗል::
በዚሁም ዕለት በዓለማዊ ት/ት ደረጃ ለያዙ: የ12ኛ ክፍል መግቢያ ፈተና ላለፉ እንዲሁም ሰ/ት/ቤቱን በሐሳብ እና በገንዘብ ላገዙ ባለ ድርሻ አካላት ሰንበት ት/ቤቱ እውቅና ሰጥቷል::
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ይከታተሉ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+4
በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተከናወነ።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 05/01/2017 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2016 ዓ.ም የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ መርሐ ግብር የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል አባ ተስፋዬ እማምሰው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ዋና ክፍል ኀላፊ መጋቤ ኅሩያን ቀሲስ ሐዲስ ኪዳነ ማርያም በትምህርታቸው የደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በተገኙበት በዛሬው ዕለት በኆኅተ ሰማይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ ተከናውኗል።
በዕለቱም ከየአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለወጡ ተማሪዎች የካርድ እና የምስክር ወረቀት የመስጠት መርሐ ግብር እንደ አጠቃላይ ደረጃ ለወጡት ተማሪዎች እና በንቃት ሲያገለግሉ ለነበሩ አገልጋዮች ደግሞ ሽልማት እና እውቅና የመስጠት መርሐ ግብር እንደተከናወነም ተገልጿል።
በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል አባ ተስፋዬ ከ1ኛ-4ኛ ክፍል የታተሙ መጻሕፍትን ለሰ/ት/ቤቶች ያስረከቡ ሲሆን የሥርዓተ ትምህርቱን አተገባበር በማድነቅ በቀጣይ ለሚሰራውም ትውልድን የመቅረጽ ስራ ሀገረ ስብከቱ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ በመግለጽ መርሐ ግብሩን በፀሎት ዘግተዋል።
መረጃው የአንድነቱ ትምህርት ክፍል ነው።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+4
በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ የሥርዓተ ትምህርት የግንዛቤ መስጫ መርሐ ግብር ተከናወነ።
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት (መስከረም 5/2017 ዓ.ም)
በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ መንበረ ጵጵስና እየተከናወነ የሚገኘው ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተዘጋጀውንና በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ ትግበራ ላይ በሚገኘውን ሥርዓተ ትምህርት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
በሥልጠናው የሀገረ ስብከቱ ማደራጃ መምሪያ መ/ሰ አክሊሉ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ መምህር መኮንን የአድባራት አስተዳዳሪዋች የሰበካ ጉባዬ አባላት የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮችና የተለያዩ ማኅበራት የተሳተፉበት ነው።
ሥልጠናው የተሰጠው በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አዘጋጅነት በ2016 ዓ.ም በክረምት ሥልጠና ሀገረ ስብከቱን ወክለው በተሳተፉ መምህራን ሲሆን የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ለ2017 ዓ.ም የትምህርት ዓመት እንዲረዳ የመማርያ መጻሕፍት ግዥ በመፈፀም በሥርጭት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+3
በደሴ ከተማ ለሚገኙ ከሁሉም አድባራት ለተወጣጡ የሰ/ት/ቤት መምህራን እንዲሁም የስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች እና የመጻሕፍት መምህራን አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክህነት ለ20ቀናት ሥልጠና በወሰዱ መምህራን ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሥልጠና በደሴ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት አማካኝነት በደሴ ቅዱስ ገብርኤል ካቴደራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ መስጠት ተጀምሯል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መስከረም 04/01/2017 ዓ.ም
በሥልጠናው የተገኙ የወረዳው የሰ/ት/ቤቶች ክፍል ሐላፊ ፣ የስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች እና የመጻሕፍት መምህራን ፣ የሰ/ት/ቤት መምህራን እና የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አመራሮች ተገኝተዋል። በመጀመሪያ ቀን የግማሽ ቀን ውሎ በሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ ዙሪያ እንዲሁም በስልጠናው ለተገኙ አካላቶች መልእክት በዲ/ን ሀብታሙ ለማ የደቡብ ወሎ ሃ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ተሰጥቶ በወ/ም ሚኪያስ አወቀ ለሰልጣኞች የአራት ቀን ውሎ አጠቃላይ ገለጻ ተሰጥቶ በወ/ም መስፍን አበባው እና በወ/ም ኢዩኤል ሞገስ አጠቃላይ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሥልጠና ተሰጥቷል። ከሻይ እረፍት በኋላ በወ/ም ሚኪያስ ዘነበ እና በእህት ቃልኪዳን ሰይድ የመሠረተ ሃይማኖት(ዶግማ) ክፍለ ትምህርት ለሰልጣኞች ተሰጥቶ የግማሽ ቀን ሥልጠናው ተጠናቋል። ሥልጠናው ለ 4 ቀን የሚቆይ ይሆናል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
