ch
Feedback
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

前往频道在 Telegram

✨Philosophy For Higher Consciousness✨

显示更多

📈 Telegram 频道 ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ 的分析概览

频道 ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ (@zephilosophy) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 31 568 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 2 177,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 086

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 31 568 名订阅者。

根据 01 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 360,过去 24 小时变化为 25,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 19.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.27% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 6 041 次浏览,首日通常累积 1 978 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 62

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
✨Philosophy For Higher Consciousness✨

凭借高频更新(最新数据采集于 02 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

31 568
订阅者
+2524 小时
+1027
+36030
帖子存档
"የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር መቃቃር የጀመረው  ራሱን ከተፈጥሮ ሁሉ የበላይ አድርጎ መመልከት ሲጀመር ነው።ለዚህም መነሻ ምክንያት የክርስትና አስተምህሮ ነው።" ብሩህ አለምነህ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ሰፊ ዘመናትን የያዙት የባርያ ንግድ፣ ቅኝ ግዛት፣ የተለያዩ ዓይነት ባርነቶችና የሴቶች ጭቆናዎች ሁሉ መንስኤያቸው የሰው ልጅ መቆጣጠርንና ጥቅምን ዓላማው ባደረገ አስተሳሰብ መመራቱ ነው፡፡ አንድን ነገር “መቆጣጠር” ካሰብክ ራስህን የዚያ ነገር አካል አድርገህ ማሰብህን አቁመሃል፡፡ “መቆጣጠር” የሚለው ሀሳብ የሚመጣው ራስህን ከዚያ ነገር ለይተህ ስታየው ነው፡፡ እናም አውሮፓውያን በዚህ መንገድ ተጉዘው ራሳቸውን ከተፈጥሮ ገነጠሉ፤ ራሳቸውን ከተፈጥሮ መገንጠል ብቻ ሳይሆን ተፈጥሮን ለሰው ልጅ መጠቀሚያ ብቻ የተፈጠረ አድርገው እንዲቆጥሩት አድርጓቸዋል፡፡ በዚህ አስተሳሰብ ላይ ተመስርተውም የፈጠሩት ሃይማኖት (ክርስትና)፣ የካፒታሊዝም ስልተ ምርት፣ ፍልስፍናና ሳይንስም ተፈጥሮን ይበልጥ እንደመጠቀሚያ እና ሜካኒካል በሆኑ ክስተቶች የተሞላ አድርገው እንዲያስቡት አድርጓቸዋል፡፡ ለምሳሌ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሄር ምድርን የሠራት፣ እንስሳትንና እጽዋትንም የፈጠራቸው ለሰው መጠቀሚያነት እንደሆነ ይናገራል፤
“እግዚአብሄርም አለ፡- ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር፤ የባሕር አሣዎችንና የሰማይ ወፎችን፤ እንሳሳትንና ምድርን ሁሉ፤ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ፤” (ዘፍ 1፥ 26)
​"አላህ በሰማያትና በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ ያስገዛላችሁ፤ ግልጽና ድብቅ የሆኑትንም ጸጋዎቹን በፊታችሁ ላይ ያፈሰሰላችሁ መሆኑን አታዩምን?" (ቁርአን 31፥20)
እንደዚህ አይነት መንፈሳዊ አስተምህሮ እንደ ታሪክ ምሁሩ Lynn White, Jri አመለካከት፣ "የሰውን ልጅ ራሱን ከተፈጥሮ የተገነጠለና የተለየ፤ የፍጥረታት ሁሉ ማዕከልና የሁሉም የበላይ አድርጎ እንዲመለከት በማድረግ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡ " በሃይማኖታዊ አስተምህሮው ከተፈጥሮ ራሱን የገነጠለው አውሮፓ “ተፈጥሮን መቆጣጠርና ማስገበር ” በሚል መርህ ወደሚመራው ካፒታሊስታዊ ስልተምርት ተሸጋገረ፡፡ ካፒታሊዝምም የገበያ ውድድርን በማፋፋምና ከፍላጎት በላይ የሚጠቀም ማህበረሰብን በመፍጠር ተፈጥሮ ላይ የመጨከኑና ከመጠን በላይ የመበዝበዙን መንገድ አጠናክሮ ገፋበት፡፡ እንደ አዲሶቹ ማርክሲስቶች አመለካከት ግን የካፒታሊዝም ጦስ የሰውን ልጅ ከተፈጥሮ በመገንጠል ብቻ አያበቃም፤ "ካፒታሊዝም የሰውን ልጅ ከተፈጥሮ ብቻ ሳይሆን ከራሱ ሰውነትም ገንጥሎታል፡፡ ካፒታሊዝም የሰውን ልጅ ሃይል በገበያ ብዙ ትርፍ ሊያመጣ እንደሚችል ኢንቨስትመንት በመቁጠር ሰውነትን ወደ ሸቀጥነት ቀይሮታል፡፡" እናም ወደ ሸቀጥነት የተቀየረው ሰው ለተፈጥሮ የሚያዝንበት ህሊና አጣ፡፡ የጥንቱና የምዕራብያውያን ፍልስፍና ዋነኛ ትኩረቱ ሰው ከሚኖርበት አካባቢና ከዲበ አካላዊው (ከሰማያዊው) ዓለም ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያስስ ነበር፡፡ እውነትንና እውቀትን፤ ውበትንና የሕይወት ትርጉምን ሁሉ በዚህ ሂደት ውስጥ ለማግኘት ይሞክር ነበር፡፡ ይሄም ሂደት  ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን ጥብቅ ቁርኝት የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ የጥንቱ አውሮፓዊነት ከተፈጥሮ ጋር መቃቃር የጀመረው ግን ራሱን ከተፈጥሮ ሁሉ የበላይ አድርጎ መመልከት ሲጀመር ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ትምክህታዊ አመለካከት እንዲይዝ ካደረጉት አስተምህሮቶች ውስጥ ዋነኛው ደግሞ ክርስትና ነው፡፡ " የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።" መዝሙረ ዳዊት 115፥16 ክርስትና (እና እስልምና) እግዚአብሄር ምድርን ለሰው ልጅ መጠቀሚያ እንደፈጠረ በማስተማር የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን ህብረትና ጓደኝነት ቆረጡት፡፡ አውሮፓዊነትም በዚህ የክርስትና አስተምህሮ ተጠልፎ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ግንኙነት ከሁለንተናዊ ህብርነት ወደ ገዥና ተገዥ፣ ጨቋኝና ተጨቋኝ፣ መለኮታዊና አለማዊ ወደሆነ “ቁጥጥር እና ጥቅም”ን ታሳቢ ወዳደረገ የሁለትዮሽ ግንኙነት ተቀየረ፡፡ የኒውተን ሜካኒክስ እንዲሁም የሆብስ፣ የላሜትሪ እና የዴካርት ፍልስፍናዎች መሰረታቸው ይሄው በሰውና በተፈጥሮ መካከል ያለው የበላይነትና የበታችነት የሁለትዮሽ ግንኙነት ነው፡፡ እነሱ የሚመኩበት “የምክንያታዊነት” እና “ተፈጥሮን በመቆጣጠር የማስገበር” አካሄድ መጨረሻ ላይ የምድራችንንና አጠቃላይ የሰውን ልጅ ህልውና የከፋ አደጋ ላይ ጣለው፡፡ አውሮፓዊነት ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን የስሜት ቁርኝት ትቶ የተጓዘበት መንገድ መጨረሻው ተፈጥሮን በማምከን የሰውን ልጅ ለከፋ አደጋ ዳረገው፡፡ 📖ፍልስፍና -2 ✍️ ብሩህ አለምነህ @zephilosophy

ድንቅ ሀሳቦችና አባባሎች 1.የሰው ዘር ጠቅላላ ፍለጎት ማቆሚያ የሌለው እና ፋታ የማይሰጥ የስልጣን ወይም የክብር ጥማት ነው።መደምደሚያውም ሞት ብቻ ነው።" ቶማስ ሆብስ 2."ሰው ነፃ ሆኖ ቢወለድም በሄደበት ቦታ ሁሉ በሰንሰለት ተጠፍንጓል።አንዳንዱ ራሱን የሌሎች አለቃ አድርጎ ያስባል።ሆኖም ከእነሱ በባሰ ባርነት ውስጥ ነው።ይህ ለውጥ እንደምን መጣ አላውቅም። ምን ጉዳይ ህጋዊነቱን ያፀድቅለታል ? እርሱን መመለስ እንደምችል አሰባለሁ።" ዣን ዣክ ሩሶ 3."ሰዎች ዲሞክራሲያዊውን መሪ ሁልጊዜም የፍላጎታቸው ወኪል አድርገው ወደ ታላቅነት ምኩራብ ተንከባክበው ያወጡታል።ይህ እንግዲህ የአምባገነንነት ዛፍ የሚያጎናቁልበት ግልፅ ስር ነው።" አፍላጦን 4.«ከሰዎች መሃል የሚበዙቱ ስለራሳቸውን ብቻ ሲያስቡ ፤ የሚመሩባቸው ፍላጐቶችም በአንድ ምልከታ በቀላሉ የሚገመቱ እና በወቅቱ ባሉበት ሁኔታ ዙርያ የሚሽከረከሩ ናቸው።" ጆን ስትዋርት ሚል 5"በህይወት ያለ ነገር ሁሉ ለአንድ ነገር ሊታዘዝ ግድ ነው! እናም ለራስህ መታዘዝ ካልቻልክ ሌላው  ሰው ያዝሀል። ኃያላን ራሳቸውን ይታዘዛሉ .. ሌሎችንም  ያዛሉ! እነዚያ ለራሳቸው የታዘዙት ደካማ የሆኑትን እንዲያዝዙ ግድ ይሆናል።" ፍሬድሬክ ኒቼ 6."ሰዎች በተፈጥሯቸው ነፃ፣ እኩል እና ራሳቸውን የቻሉ በመሆናቸው ማንም ከራሱ ፍቃድ ውጭ መብቱ ተነጥቆ በሌላው ፖለቲካዊ ሉዓላዊ ስልጣን ስር ሊውል አይገባውም።" ጆን ሉክ 7."አንድ ነገር መረዳት ማለት ከባህሪይ እና ከውስጣዊ ማንነቱ ጋር መተዋወቅ ነው።" ጀርም ቤንታም 8."የአገር መልካምነት (በምግባር ልዕልና መላቅ) በመንግስት ስርዓቷ የሚሳተፉ ዜጎቿ መልካምነት ድምር ውጤት ነው።" አሪስጣጢሎስ 9."መልካም አርበኛ እና እውነተኛ ፖለቲከኛ በአገሩ ያለውን እሴት እንዴት አሟጦ እንደሚጠቀም ያሰላስላል።" ኢድመንድ በርክ 10."ብዙውን ጊዜ መንግስታት የዛሬውን እውነታ ለመጋፈጥ ሲደፍሩ አይስተዋልም። ከዚህም የተነሳ ለሚመጣው ዝግጁ አይደሉም።ለዜጎቻቸው የሚያቀርቡትም የማይጨበጥ ምናባዊ ደስታን ይመስላል።" ጀርም ቤንታም 11. "ታላላቆቹ የፖለቲካ እሰጥ አገባዎች እና ግጭቶች በሀይማኖት ፣በብሄር ፣በመብት ፣በነፃነት ስም የሚደረጉ ይመስላሉ።ሀቁ ከዚህ ይለያል።ከውብ መፈክሮች ጀርባ ድብቅ የግል ጥቅምን የማስጠበቅ እኩይ ጠባያት አሉ።" ኢድመንድ በርክ የትኛውን አባባል የበለጠ ወደዳችሁት? @zephilosophy

«የዓለም ታሪክ ነፃነት ለማወቅ ከሚደረግ ሒደት ውጭ ምንም አይደለም።» ፍሬድሪክ ሄግል ታላቁ ጀርመናዊ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ሔግል "philosophy of history" በተሰኘው መፅሀፍ ላይ የዓለም ታሪክ አጋጣሚ ያከታተላቸው ኹነቶች ትርዒት ሳይሆን በተቃራኒው ምክንያታዊ እና የታሰበበት ዕቅድ ውጤት ነው ይለናል። ይህ ቅጥ አምባር በየትኛውም ቦታ እና ጊዜ ቁልጭ ብሎ ይታያል። የፖለቲካ ጥናትም የተሟላ የሚሆነው ተቋማት እና ሰብዕናዎች በትልቅ ዓላማ ያነገበ የታሪክ እድገት ማዕቀፍ ውስጥ ከተከወነ ብቻ ይሆናል፡፡  ለዚህ ሒደት ወይም ቅጥ አምባር (ፓተርን) ሔግል ስያሜ አውጥቶለታል። ታላቁ ኃሳብ ወይም ፍፁማዊ እውቀት (The ldea) ሲል ይጠራዋል። ሔግል በፖለቲካ ሒደት ውስጥ ኃሳብ ላለው ትልቅ ፋይዳ አፅንኦት ስለሚሰጠው ስያሜው የተገባ ይመስላል። ቁሳዊው የሰዎች እና የተቋማት ዓለም ለሔግል ብዙም ጉዳዩ አይደለም። ይልቁን ለቁሳዊው ዓለም አቅጣጫ እና ግብ የሚሰጠው መንፈስ ወይም ኃሳብ ላይ ማተኮርን ይመርጣል። ታላቁ ኃሳብ በማህበረሰብ ውስጥ አስፈላጊ የሆኑ እንደ ፍትህ ፤ ነፃነት ያሉ ረቂቅ እሳቤዎችን ሁሉ ጠቅልሎ የሚይዝ ማዕቀፍ ነው። «ነፃነት ይላል ሔግል በሰዎች ተግባር ውስጥ ሳይሆን በሰዎች ግንዛቤ ውስጥ ይገኛል። ፖለቲካን ለመረዳትም ማጥናት ያለብን የሰዎችን ድርጊት አይደለም፡፡ ድርጊታቸውን እንዲፈፅሙ የሚገፋፋቸውን መንፈስ እንጅ። የሰው ዘር ታሪክ በንቃት የተተለመ የሆነ ግብ ይዞ አልተጀመረም። ማህበራዊ ደመ ነብስ ንቁ የሆነ ለህይወት እና ለንብረት ደህንነት መሻትን ያመላክታል። እናም ማህበረሰብ በሚቋቋምበት ጊዜ ይህ ዓላማ ይበልጥ ጠቅላይ ሆኗል። የዓለም ታሪክ የሚጀምረው ጠቅላይ ግብን በመረዳት ነው። የመንፈስ ኃሳብ በስውር  ቅርፁ ንቁ ደመነብስ ይሆናል።» ይለናል። በታሪክ ማዕከል ውስጥ ከህቡዕ ልቦና ወደ ንቁ ልቦና ወይንም ካለመንቃት ወደ ንቃት የተደረገው ሽግግር አለ። ይህም ወደ ፍልስፍናዊ ነፃነት የሚያደርሰው ሒደት ነው። አስተያየቱን ሲቀጥልም፦ «የነፃነት ዋና ተፈጥሮ ራሱን ወደማወቅ መምጣቱ ነው። በዚህም ህልውናውን ይገነዘባል።ሰዎች ከታላቁ ኃሳብ ጋር መኖርን ማወቅ አለባቸው። ሊያመልጡት አይቻላቸውምና። ሰዎች እና ተቋማት ነፃነትን ለማወቅ ከፈለጉ በትልቁ የታሪክ ሒደት ውስጥ ትክክለኛ ቦታቸውን ለማወቅ ጥረት ማድረግ አለባቸው፡፡ ታሪክ በእርሱ አመለካከት መሠረት በነፃነት አቅጣጫ የሚደረግ ተቋማዊ የለውጥ ሒደት ነው። ሰዎች ነፃነትን እንዲጨብጡ የህልውናቸውን ምክንያት ወደማወቅ ከፍታ ማንሰራራት አለባቸው፡፡ ስለዚህ ነፃነት ከእውቀት ወይም ንቃተ ልቦና (consciousness) ተለይቶ ሊታይ አይችልም። ነፃ የሆነ ሰው ለድርጊቱ እና ለባህርዩ የክልከላ አጥር ያልተበጀለት ሰው ሳይሆን በታሪክ መስክ ላይ ትክክለኛ እና ልዩ ስፍራውን ጠንቅቆ ያወቀ ነው፡፡ ይህንን ነፃነት የሚያጐናፅፈው ታላቁ ኃሳብ ብቻ ነው።" በፖለቲካ ንፍቀ ክበብ ውስጥ ብዙ ሰዎች ፍዝ ናቸው። የመረዳትም የመሳተፍም ንቃት የላቸውም፡፡ እጣ ፈንታቸውን ያለ ተቃውሞ እና ያለ አመፃ ይቀበላሉ። እነዚህ ሰዎች ሳያውቁት በጦርነት ይፈጃሉ ፤ በረሃብ ያልቃሉ ፤ በአምባገነን ጭቆና ይቆረቁዛሉ። በእያንዳንዱ ዘመን አልፎ አልፎ ግን ብቅ የሚሉ ልዩ ሰብዕናን የታደሉ ፤ የነቁ እና አብዮተኛ ግለሰቦች አይጠፉም። የአንድ መደብ አባላት አይደሉም። ልዩ መብት የታደሉ ወይንም የተነፈጉም አይደሉም። ከየትኛውም አቅጣጫ ሊወጡ የሚችሉ ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ - ይላል ሔግል የፖለቲካዊ ተግባር ሰዎች ናቸዉ። የራሳቸውን ግብ እና ፍላጐት ሰንቀው በአንድ ኃሳብ ይጓዛሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች የዲያሌክቲካዊው ሒደት ዋነኛ መሳርያ ናቸው። በግልፅ ባይታወቃቸውም የተቃርኖ (አንቲቴሲስ) ኃሳብን በመድረስ ነባሩን ስርዓት ይሞግታሉ። አብዮትን በመለኰስ ታሪክን ይፅፋሉ። ሔግል የእነዚህ ሰዎች ወዳጅ ነው። ለሰው ዘር እድገት ያበረከቱትን አስተዋፅኦ ማክበር ይገባናል"  ይለናል @zephilosophy

ስለጊዜ ሳስብ ገደል አፋፍ ላይ ሆነው የለቀቋት እፉዬ ገላን አስታውሳለሁ። ከዓይን እስከምትሰወር ድረስ ብቻ የምንከተላት። ከአለፈች በኋላ ምስሏ ብቻ በአዕምሯችን መዝገብ ሳይ የሚሰፍር። በ "ጊዜ" ውስጥ ቁጥር አይደለም ያለው። ጊዜ ስንል ሰዓት ፣ደቂቃ ሰከንድ እያልን አይደለም። ጊዜ ሰኞና ሀሙስ አልያም ጥቅምትና ሰኔ አይደሉም። ትላንትና ብለን ዛሬ ከዛሬም ደግሞ ነገ ተከታዩ አይደሉም የጊዜ መስፈሪያዎች...እኛው ነን!! ጊዜ የሚሰፈረው በእኛ ነው።  በስጋና በነፍሳችን ውስጥ ነው ጊዜ የሚሽከረከረው። በሽክርክሪቱ መሀል የምንቆጠረው እኛ ነን።24 ሰዓታት የምንላቸው ፍካሬያቸው ከውልደት እስከ ሞት ድረስ ያለው ህልውናችንን ለመወከል ነው። እያንዳንዷ የገላችን ክፍል ጊዜ ነው። ህዋሳቶቻችን እንደ ኑግ ክምር ከስጋዎቻችን ላይ ሰፍረዋል። በየሰከንድ ውስጥ ከዚህ ክምር ቅንጣት ህዋስ ትንሸራተታለች።ጊዜ ቁጥር አይደለም። ጊዜ ስጋችን ነው ታሪካችን ነው...ህይወታችን ነው ጊዜ እኛው ነን። 📖📖📖📖📖📖 ይህ የኛ ጊዜ ግን መከረኛ ትውልድ ተገልጦበታል።ዘመኑ የመከራ ክርታስ ሆኗል። በዚህ ክርታስ ውስጥ ሞት... ስደት.... ጦርነት... ድህነት... የተባሉ ጥሬ ሀቆች ታጭቀውበታል። ይህንንም የክርታስ ቋጠሮ በእያንዳንዱ የትውልዴ አንገት ላይ እንደ ሜዳሊያ ተንጠልጥሏል።ለዚያም ነው ሁሉም የጎበጠው። ለዚህም ነው የድባቴ አየር ብቻ የሚነፍሰው። ይህ ትውልድ በ "ጊዜው ላይ ተሸንፏል። ቢያኮርፍ እንኳ የሚያባብለው የለም። ታላላቆቹ ጥይት በማንጣጣት ተጠምደዋል ለረሀቡ ዳቦ ለእንባው ደሞ መሀረብ የሚያቀብለው ታላቅ የለውም። የኑሮ ትርምስና ውጣ ውረድ ሽባ አድርጎታል። ለመሳለም ጎንበስ ሲሉለት ኩርኩም አናቱን ያቀምሱታል። ለመማር ከእግራቸው ስር ቢደፋ ከንፅህና የራቀ እግራቸው ይሰነፍጠዋል። ይህ እግራቸው መዋል በሌለባቸው ስፍራ ስለመገኘታቸው እንደ ምልክት ሆኖ ይጮሀል። ትውልዱ ባክኗል! ታላላቆቹ ለሚጫወቱት ቁማር ማስያዣ ሆኗል። ህይወቱ የራሱ አይደለችም። በአራጣ ተይዛለች...... አህመድ ሁስ 📖ጥሪ ወደ ሞት @zephilosophy

የእግዜር አሽሙር ምድርን በዘረጋው፣ ሰማይን ባቆመው           ጥበበኛ እጁ ተጨንቆ ቢሰራን፤ እኛ ግን ከንቱ ነን! ከእርግብ መደብ ተክሎን            የእባብ ነፍስ አፈራን። ፍርድ ያውቅበት የለ? የሕይወትን ትርጉም – በአሽሙሩ ሲያራራው፧ ለሞቱ ያልመጠነን- “ኗሪ!' ብሎ ጠራው። ባባ ጣሂር 📖የመንፈስ ከፍታ @zephilosophy

"ፍትህ የሌለው ሉአላዊ ስልጣን የተደራጀ ዝርፊያ እንጂ ሌላ ምንድን ነው?" አውግስቲን @zephilisophy
"ፍትህ የሌለው ሉአላዊ ስልጣን የተደራጀ ዝርፊያ እንጂ ሌላ ምንድን ነው?" አውግስቲን @zephilisophy

The Republic The Republic የአፍላጦን ዋነኛ ተጠቃሽ ስራው ነው። የመጀመሪያው ብስል የፖለቲካዊ ፍልስፍና ስራም ነው። ስለመንግስት አስተዳደር ያለውን አስተያየት ጠቅልሎ አካቶበታል። ከፍተኛ ስነ ፁሁፋዊ ለዛ ያረፈበትን ይህን ታላቅ ዲያሎጉን (በውይይት መልኩ የሚቀርብ ሀተታ) የፃፈው ድርሰትን በሚገባ በተካነበት እና ኃሳብን የመግለፅ ጥበብን አሳምሮ ባወቀ! ወቅት በመሆኑ በፍልስፍናው አበክሮ የሚያወጣ የሚያወርዳቸውን ጉዳዮች በሚደንቅ ህብር አስሮ ለማቅረብ እስችሎታል። ፍፁም ነው የሚለውን ሐሳባዊ የጋራ ብልፅግና ሲተነትን (ይህም በስነፅሁፍ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ዩቶፒያ-- እንከን አልባ ምናባዊ ዓለም-- ተደርጎ ይቆጠራል።) በህይወቱ  ያተኮረበትን ተግባራዊ ፖለቲካ ያስዳስሳል። በሳል የህይወት ተሞክሮውን እና እውቀቱን ተጠቅሞ ለዓይነተ ብዙ ችግሮች (ከስነ ፅሁፍና ሙዚቃ ግልጋሎት እስከ የሴቶች እኩልነት፤ ከጋራ መኖሪያዎች እስከ የህዝብን ዕድገት በመቆጣጠር ምርጥ ዘር የመፍጠር ሳይንስ ወይም ኢዩጄኒክስ ድረስ) አስተያየቱን ለግሷል። በትምህርት እና በመንግስት መካከል ያለውን የጠለቀ ግንኙነት ካስተዋሉት የመጀመሪያዎቹ ጠቢባን መሃልም አንዱ ነው። ወጣቶችን ስለማስተማር፤ ስለማነፅ እና ስለማሰልጠን የሰጠው አፅንኦት በበርካቶች በአድናቆት ታይቷል። ዣን ዣክ ሩሶ «በዓለም ላይ በትምህርት ላይ የተሰራው እጅግ ምርጡ የምርምር ፅሁፍ » ሲል The Republicን ማወደሱን ልብ ይሏል። በአስር ቅፆች (መፅሃፍት) የተደራጀ ስራ ነው The Republic። በመጀመርያው ቅፅ ፍትህ የሰው ልጆች ነብስ በትክክል ስራዋን እንድትከውን የሚያስችል ጠበል ነው ይለናል። ህይወትን በአግባቡ የሚኖር ሰው የተባረከ እና ደስተኛ ነው ሲል ያክላል። በሁለተኛው ቅፁ መግቢያ ላይም ፍትህ ለራሱ ሲባል (መልካም እሴት ስለሆነ) እንዲሁም የሚያስገኘው ውጤት በጎ ስለሆነ ልንተገብረው እንደሚገባ ይመክረናል። በአራተኛው ቅፅ ደግሞ ፍትህን የሚተገብር ግለሰብ ሌሎቹን የምግባር እሶቹን በሙሉ እያስተባበረ እንደሆነ ያስረዳል። ፍትህን የማይተገብር ሰው በአንፃሩ ደፋርም አይደለም፡፡ ብልህም አይደለም። ትክክለኛም አይደለም፡፡ ከላይ ከላይ ሲያዩት የዲያሎጉ ዓላማ «ፍትህ ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ መመለስ ቢመስልም ፍትህ (juctice) የሚለውን አቻ ትርጓሜ የሚያስገኝልን የግሪክ ቃል ከፖለቲካዊ እና ህጋዊ እኩልነት የዘለለ ፍቺ በውስጡ ያመቀ በመሆኑ ጉዳዩን አስፍተን እንድንመለከተው ይጋብዘናል። የምግባር ልዕልናን (virtue) የመፈንጠቅ ትክክለኛነት የሚል ትርጉምም አለው፡፡ አፍላጦን ይባትል የነበረው ትክከለኛውን ህይወት (ሰዎች እና አገራት ሰናይ ተፈጥሯቸውን አሟጠው እንዲያወጡ የሚያደርጉ መርሆችን) ፍለጋ ነው። The Republic በወቅቱ በነበረው ስርዓተ ፖለቲካ ላይ የቀረበ ኂስም ክስም ነው። አፍላጦን ከሰው ልጆች ተሞክሮ የሚልቅ ዘላለማዊ ህልውና አለ ብሎ ያምን ስለነበር ግብረ ገብ እና መልካሙ ህይወት የዚህ ህልውና መገለጫዎች ናቸው። መንግስታት እነኝህን እሴቶች ማበረታታት አለባቸው ይላል። ይህ አመለካከቱን ለማሳየት ባጠናቀረው አንድ ተረክ ላይ ሰዎች ዋሻ ውስጥ ፊቶቻቸውን ወደ ግድግዳ አዙረው በሰንሰለት ተጠፍንገዋል። ለብርሃኑ ጀርባቸውን ሰጥተዋል። ስለዚህ ያተኮሩበት ግድግዳ ላይ የሚታያቸው ትዕይንት ከጀርባቸው የሚከወነው እውነታ ነፀብራቅ ወይንም ጥላው ብቻ ነው። ለአፍላጦን ተራ ተርታው የዕለት ተዕለት ህይወት አታላይ ቅዠት ነው። በፖለቲካ ውስጥ የሚያቆጠቁጡት ክፋቶችም አውሬያዊ ደመ ነብስን የመከተል ውጤቶች ናቸው። ስለሆነም ከዚህ ክፉ ደመ ነብሳዊ ጥሪ ነፃ የወጡ ፈላስፎች የንግስናን መንበር ካልተቆናጠጡ ወይንም ነገስታቱ በቅንነት ሃቀኛ ፈላስፎች ሊሆኑ ካለቆረጡ በቀር ከክፋት መላቀቅ የለም። ፈላስፋ-ፖለቲከኛ ብቻ ነው ዜጎቹን ከታሰሩበት ፈትቶ ፊታቸውን ወደ ብርሃን ሊመራ የሚችለው ፤ ከዋሻውም አውጥቶ አምሳያውን ሳይሆን ትክክለኛውን እውነት የማሳየት ብቃት የታደለው። @zephilisophy

The Republic - Plato

የገዢ ኪሳራ ይህ ሰፊ ገበያ በመንፈስ ተሞልቶ በፍቅር ሲጣራ፤ ሸማች የሚጋፋው ቅራቅንቦ ተራ፡፡ “ያ ስንት ነው? ይላል፣ “ይሄኛውስ?” ይላል፤ የብልጭልጭ አይነት ያነሳል ይጥላል። ከመንፈስ ገበያ የውበት ጥሬ እቃ ሞልቶ ተትረፍርፏል፤ ሸማች ግን ልብ የለው ለኮልኮሌ ፍቅር ማልዶ ተሰልፏል። “ወዴት ነህ?” አይባል -                  “ወዴትም!” ነው መልሱ፤ “ምን በላህ?” ይሉታል -                   “ምንም!” ልትል ነፍሱ፡፡ እንዲያውም ካሰኘው! ምን እንደሚፈልግ ፈፅሞ ይዘነጋና፤ “ፀሃይ ስጡኝ!” ብሎ ብቅ ይበል ማምሻውን፤ ሰልፈኛ ነውና ' ከጨረቃ ቆርሶ '                     ይወስዳል ድርሻውን፡፡ የሸማች ሕሊናን መምሰል ከሸፈነው፤ ገበያ መታየት ከመግዛት እኩል ነው። የጠየቀም ገዝቶ፣የክፈለም ገዝቶ፣        የተላከም ገዝቶ፣ የላከም ሸምቶ፤ እዚያው ይሞታታል! ያልሞላ ቅርጫቱን ለአምሳዮቹ ትቶ ። ይኸው መጨረሻው ! ሸማቹ ለገላው እየተጨነቀ፣ ገዢው ለብልጭልጭ እየተደነቀ፤ የመንፈስ ከፍታ ተሸርሽሮ አለቀ፡፡ ገጣሚ- ሩሚ መፅሀፍ-የመንፈስ ከፍታ @zephilosophy

የሰው ልጆች የሚተዳደሩት በውሸት አንቀልባ ታዝለው ነው። ውሸት ሂዱ ከእኔ ራቁ ብትላቸው መግቢያ ቀዳዳ የላቸውም። በውሸት ውስጥ ስናልፍ ከነነፍሷ በድመት መንጋጋ ውስጥ እንደገባች አይጥ አይነት ህይወት እንኖራለን። በድመቷ ጥርሶች ተቆንጥጣ የተንጠለጠለችው አይጥ እስከምትሰለቀጥ ድረስ በህይወት መኖሯን እንደፀጋ ትቆጥራለች። መላመጥና መውዋጧ ግን አይቀርም። በውሸት እቅፍ ውስጥ መደላደልም እንዲህ ነው። እቅፏ አባብሎ እስከሚያፍነን የመተንፈሻ እድል የተሰጠን ይመስለናል። የባከኑ ሰከንዶች ያክል እንኖራለን። በተቃራኒው እውነት ምንጊዜም ገፊ ሀይል ናት። እንደወርቅ በእሳቱ ሳትፈትሸን የራሷ አታደርገንም። በግዛቷ ላይ ከሰፈርን በኋላም መፈናፈኛ የለንም። የማርያም መንገድ አትሰጠንም። እውነት በእኛ ዙሪያ የምታጥረው ክልል እጅግ ውዱ መከለልን ነው። ስለዚህም እንደፈለግን የምንፈነጭባትን የውሸት ዓለም ፈጠርን። በእሷም ጥላ ስር ተጠለልን። እኔ ግን የራሴን የእውነት ዓለም ልገነባ ነው.... መፅሀፍ-ጥሪ ወደ ሞት ደራሲ-አህመድ ሁስ @zephilosophy

"እውነታው የሰው ልጅ የሰውን ልጅ መጠበቅ አለበት ይላል። ቅዠት ግን ሌላ አካል ከሰማይ እስኪወርድ ይጠብቃል።" "ያለ ሰላም፣ ስለ ብልጽግና የሚደረግ  ንግግር በመቃብር ላይ የሚተወን ትያትር ነው።" ✍️ዮናታን አቢስ በሀገራችን ሟቾችን ቶሎ ነው የምንቀብረው። ሀዘናችን አጥሮ ሳይሆን ሞት የተለመደ የዕለት ተዕለት ኑሯችን ስለሆነ። ሌላ ጭF:ጨFa። ሌላ የቤተ ክርስቲያን ቃ:*ጠሎ። በፍርሃት ባዶዋን የቀረች ሌላ መንደር። የሟ*ቾ*ች ዝርዝር ውስጥ ስም እስኪወጣ የሚጠብቁ ሌላ ቤተሰቦች። ሌላ ዙር መግለጫዎች፣ ውግዘቶች፣ ጸሎቶች እና ቃል ኪዳኖች። ከዚያም ዝምታ፤ እስከ ቀጣዩ ጭF:ጨFa ድረስ። በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ምሥራቅ አርሲ ተደጋጋሚ የጥ**ቃት መድረክ ሆናለች። ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ንጹሐን ተገdl:ዋል፣ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ኢላማ ተደርገዋል፣ አብያተ ክርስቲያናት ተጠktዋል፣ ቤተሰቦች ተፈናklዋል፣ እንዲሁም ማኅበረሰቦች ከታጠቁ ሰዎች ለማምለጥ ወደየአቅጣጫው ለመሰ*ደድ ተገደዋል። ቁጥሮቹ እንደ ምንጩ ይለያያሉ። ዘጠኝ ሟ*ቾ*ች። ሠላሳ ሟ*ቾ*ች። አርባ ሟ*ቾ*ች። ከዚያም በላይ። ወይም ያነሰ። ማንም ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ የሆነ አይመስልም። ሁሉም የሚስማማበት አንድ ሀቅ ግን ሰዎች እየሞtu መሆናቸውን እና ለረዥም ጊዜም ሲሞtu እንደነበር ነው። ምርመራው ከመጀመሩ በፊት ደ*ሙ ደርቋል። መንግሥት መግለጫዎችን ያወጣል። አብያተ ክርስቲያናት ደወል ይደውላሉ። ፖለቲከኞች ስሌት ያሰላሉ። ሟ*ቾ*ች ግን እንደሞtu ቀርተዋል። አርሲም ቀጣዩን የቀብር ሥነ-ሥርዓት እየጠበቀች ነው። የሥልጣን ጠበቆች ሁልጊዜም ማብራሪያ አላቸው። ግጭቱ ውስብስብ ነው። የጸጥታው ሁኔታ አስቸጋሪ ነው። ገዳ*ዮቹ አይታወቁም። ምርመራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። እነዚህ ተመሳሳይ ሰበቦች ደጋግመው ከመነገራቸው የተነሳ፣ ከማብራሪያነት ይልቅ እንደ ኑዛዜ መሰማት ጀምረዋል። መንግሥት ሕይወትን ለመጠበቅ ከተቋቋመ ተቋምነት ባለፈ ሌላ ምንድን ነው? አንድ መንግሥት በኢኮኖሚ ዕድገት ላይሳካለት ይችላል። በመሠረተ ልማት ላይሳካለት ይችላል። በትምህርት ላይሳካለት ይችላል። ነገር ግን ዜጎቹን ደጋግሞ ከግ*ድያ መታደግ ከተሳነው፣ ከተመሰረተበት መሠረታዊ ዓላማ መውጣት ይጀምራል። የአንድ መንግሥት ቀዳሚ ኃላፊነት ልማት አይደለም። ጥበቃ (ደህንነት ማረጋገጥ) ነው። ያለ ሰላም፣ ስለ ብልጽግና የሚደረግ ማንኛውም ንግግር በመቃብር ላይ የሚተወን ትያትር ነው። የአርሲ አሳዛኝ ክስተት ሰዎች መሞtaቸው ብቻ አይደለም። ትልቁ አሳዛኝ ነገር ብዙዎች መሞtaቸው እንደሚቀጥል አምነው መቀበላቸው ነው። ጭfጨfaዎች ወቅታዊ ሆነዋል። እንደ ዝናብ። እንደ መኸር። እንደ ድርቅ። የሚጠበቁ። የሚገመቱ። የተለመዱ። ነገር ግን ከዚህ ሁሉ በስተጀርባ የተደበቀ ሌላ አሳዛኝ ነገር አለ። ከእያንዳንዱ ጥ*ቃት በኋላ የሚሰማውን ቋንቋ በጥሞና ያዳምጡ። "ኦርቶዶክሶች ተገ*ደሉ።" "አማራዎች ተገ*ደሉ።" "ኦሮሞዎች ተገ*ደሉ።" "ሙስሊሞች ተገ*ደሉ።" እያንዳንዱ ቡድን የራሱን ሟች ይቆጥራል። እያንዳንዱ ቡድን በራሱ ድንበር ውስጥ ብቻ ያዝናል። አስከሬኖች አስቀድመው በምድብ ተለይተው ይመጣሉ። ብሔር በመጀመሪያ። ሃይማኖት በሁለተኛ ደረጃ። ሰብዓዊነት በመጨረሻ። በጥ*ይ'ት የተገdለ ሕጻን የኦርቶዶክስ ደ*ም ወይም የሙስሊም ደ*ም አይደለም የሚደማው። የሚፈሰው የሰው ደ*ም ነው። መቃብር ስለ ብሔር ግድ የለውም። ቤት የሚያ*ወድም እሳት ሰለባዎቹ የትኛውን ቋንቋ እንደሚናገሩ አይጠይቅም። ሞት የጎጠኝነት ትልቁ ጠላት ነው፣ ምክንያቱም ሁሉም ርዕዮተ ዓለሞች ዕድሜ ልካቸውን ሊደብቁት የሚሞክሩትን ሀቅ፣ ከማንኛውም ማንነት ስር ሰው የሚባል ተመሳሳይ ምስኪን ፍጡር እንዳለ ያጋልጣል። ሆኖም በዚህ አስከፊ ሁኔታ ውስጥም ቢሆን ሌላ ነገር ይጀምራል። ጸሎት። አጥብቃችሁ ጸልዩ። አብዝታችሁ ጸልዩ። ተግታችሁ ጊዜ ጸልዩ። በአንድነት ጸልዩ። ለምህረት ጸልዩ። ለሰላም ጸልዩ። ለፍትህ ጸልዩ። ጸልዩ። ጸልዩ። ጸልዩ። ሰዎች እየጸለዩ አብያተ ክርስቲያናት ተቃ*ጥለ*ዋል። ሰዎች እየጸለዩ መንደሮች ባዶ ቀርተዋል። ሰዎች እየጸለዩ ገዳ*ዮቹ ተመልሰዋል። ሰዎች እየጸለዩ የቀብር ሥነ-ሥርዓቶች ቀጥለዋል። መደጋገም እምነት መሆኑ አብቅቶ እውነታን መካድ መሆን የሚጀምረው የትኛው ነጥብ ላይ ነው? አማኞች አምላክ ፍጥረቱን ይጠብቃል ይሉናል። ፍጥረቶቹ ግን በጥ*ይ*ት አልቀዋል። አምላክ ቤቱን ይጠብቃል ይሉናል። ቤቱ ግን በእሳት አመድ ሆኗል። አምላክ ምዕመናኑን ይጠብቃል ይሉናል። ምዕመናኑ ግን ዛሬም ልጆቻቸውን እየቀበሩ ነው። ከዚያም የተለመደው መከላከያቸው ይመጣል። የፈጣሪ መንገድ አይመረመርም፤ የሚሰራው በሚስጥር ነው። ግን ሚስጥር ማለት ማብራሪያ ሲያልቅ የሚቀር መጽናኛ ነው። ዓይናችን እያየ እየሆነ ያለውን እንግዳ የሆነ የተገላቢጦሽ ሁኔታ አስተውሉ። ሃይማኖት የሰው ልጅ በፈጣሪ ላይ እንደሚደገፍ ያስተምራል። እውነታው ግን የሚያሳየው ፈጣሪ በሰው ልጅ ላይ እንደተደገፈ ነው። ሰዎች የአምልኮ ስፍራዎችን ይገነባሉ። ይጠብቃሉ። ሲወድምም መልሰው ይገነባሉ። መልሰው ይከላከላሉ። እሱን ለመጠበቅ ይሞ*ታሉ። የሰው ልጅ እጁን ቢሰበስብ፣ እያንዳንዱ ስፍራ ፍርስራሽ ይሆናል። እያንዳንዱ ቅዱስ መጽሐፍ አቧራ ይለብሳል። እያንዳንዱ ተቋም ይወድቃል። በግልጽ እንደሚታየው ፈጣሪ አማኞችን ከሚጠብቀው ይልቅ፣ አማኞች ናቸው ፈጣሪን የሚጠብቁት። ሁሉን አድራጊ የሆነው አምላክ የራሱን መቅደስ እንዳይፈርስ መከላከል ካልቻለ፣ በአርሶ አደር ላይ የተተኮሰችን ጥ*ይ*ት ይመክታል ብሎ መጠበቅ ምን ዓይነት አመክንዮ ነው? መንደሮች ሲቃጠሉ አምላክ ዝም ካለ፣ ኃላፊነቱ ከጅምሩም የሱ አልነበረም ማለት ነው። ኃላፊነቱ ሁልጊዜም የኛው ነው። ይህ የሰዎችን ነጻነት የሚቃወም ሙግት አይደለም። ይልቁንም ቅዠትን የሚቃወም ሙግት ነው። ምክንያቱም ቅዠት ተግባርን ሲተካ አደገኛ ነውና። በተሰበረ ድልድይ የሚተማመን ሰው፣ ሲሻገር ሊሞት ይችላል። በተዓምራዊ ጥበቃ የሚያምን ማኅበረሰብ፣ ሰብዓዊ ጥበቃን ቸል ሊል ይችላል። እናም ብጥብጥ ሲመጣ፣ እውነታው ዕዳውን ይሰበስባል። የአርሲ ትምህርት ሥነ-መለኮታዊ አይደለም። ሰብዓዊ ነው። ምንም መልአክ አልመጣም። ምንም ተዓምር ጣልቃ አልገባም። ምንም መለኮታዊ ጋሻ ከዳመና አልወረደም። ሰዎች ከተርፉ፣ የተረፉት ሌሎች ሰዎች እንዲተርፉ ስለረዷቸው ነው። ማኅበረሰቦች ከጸኑ፣ የጸኑት የሰው ልጆች እርስ በርሳቸው ስለተጠባበቁ ነው። የቆሰሉትን የተሸከሙት እጆች የሰው ልጅ እጆች ናቸው። ለሟቾች የፈሰሰው እንባ የሰው ልጆች እንባ ነው። ፍትሕ የጠየቁት ድምጾች የሰው ልጆች ድምጾች ናቸው። እና ምናልባትም ከሁሉም መራራው እውነት ሁሉም መረጃዎች ወደ ሰው ልጅ ራሱ እየጠቆሙ ሳለ፣ እኛ ከሰው ልጅ በላይ የሆነ መዳኛን መፈለጋችንን ቀጥለናል። አርሲ በሃይማኖቶች መካከል የሚደረግ የጦር ሜዳ አይደለችም። በብሔሮች መካከል የሚደረግ የጦር ሜዳም አይደለችም። በአማልክት መካከል የሚደረግ የጦር ሜዳም አይደለችም። ይልቁንም በእውነታና በቅዠት መካከል ያለች የጦር ሜዳ ናት። እውነታው የሰው ልጅ የሰውን ልጅ መጠበቅ አለበት ይላል። ቅዠት ግን ሌላ አካል ከሰማይ እስኪወርድ ይጠብቃል። የአርሲ መቃብሮች ለጊዜው የትኛው ወገን እያሸነፈ እንደሆነ እየነገሩን ነው። ፍትሕ ለሰብዓዊነት!! ፍትሕ ለእውነት!! ፍትሕ ለአርሲ!! @zephillosophy

4. አብዛኛው ስሜታዊ ህመም ተቃውሞ እንጂ እውነታው አይደለም። ይህ ማለት ስቃይ ምናባዊ ነው ማለት ሳይሆን ብዙ ስቃይ የሚመጣው እውነታው ከሆነው የተለየ እንዲሆን ከመፈለግ ነው ማለት ነው። ስቶይኮች ይህንን በጥልቀት ተረድተውታል፡ ህመም የማይቀር ነው፤ ስነ-ልቦናዊ ስቃይ ግን ብዙ ጊዜ ትርጓሜ ነው። ማርጀት ያማል፣ ማጣት ያማል፣ መገለል ያማል፣ ሞት ያማል፤ ነገር ግን አእምሮ ህመሙን በተቃውሞ ያባዛዋል፦ "ይህ መሆን አልነበረበትም"፣ "ይህ ማንነቴን ያፈርሰዋል"፣ "ከዚህ መትረፍ አልችልም"፣ "ህይወት ዘላቂነት ሊሰጠኝ ይገባ ነበር"። ቡድሂዝም ሙሉ ፍልስፍናውን በዚህ ግንዛቤ ላይ ገንብቷል፡ መጣበቅ ስቃይን ይፈጥራል፣ ምክንያቱም እውነታው ራሱ በየጊዜው የሚለዋወጥ ነውና። አሁን ላይ neuroscience እንደሚያሳየው፣ ስሜታዊ ስቃይ በአእምሮ ተደጋጋሚ የሃሳብ ዑደቶች አማካኝነት ይባባሳል — አእምሮ ድርጊቱ ካለፈ ከረጅም ጊዜ በኋላም ህመሙን ደጋግሞ ይለማመደዋል እንዲሁም ይተረጉመዋል። የሰው ልጅ ከአካል ጉዳቱ ከሚድንበት ፍጥነት ይልቅ ከውስጣዊ ትረካው የሚድንበት ፍጥነት ይዘገያል። ነፃነት የሚመጣው ህልውናን በመቆጣጠር አይደለም፤ ይልቁንም በህልውና ላይ የሚደረገን አላስፈላጊ ስነ-ልቦናዊ ፍጭት በመቀነስ ነው። የሚታጠፍ ዛፍ ማዕበሉን ተቋቁሞ ያልፋል፤ ደረቁ ቅርንጫፍ ግን ይሰበራል። 5. ራሳችሁን በንቃት ካልገነባችሁ፣ ማህበረሰቡ በአጋጣሚ ይገነባቹሃል። ይህ ምናልባት ከሁሉም የበለጠ አደገኛው እውነት ሊሆን ይችላል። የሰው ልጅ እጅግ በቀላሉ ሊቀረጽ የሚችል ፍጡር ነው። ፍላጎቶቻችን፣ ፍርሃቶቻችን፣ ምኞቶቻችን፣ የፖለቲካ እምነቶቻችን፣ የውበት መመዘኛዎቻችን፣ የትኩረት አቅማችን፣ ስነ-ምግባራችን እና ስብዕናችን እንኳ 'ego' ሊቀበለው ከሚችለው በላይ በአካባቢያችን የሚቀረጹ ናቸው። ከወላጆቻችሁ፣ ከአልጎሪዝም፣ ከባህል፣ ከሃይማኖት፣ ከጓደኞቻችሁ፣ ከደረሰባችሁ ጉዳት፣ ከብሄራዊ ተረቶች፣ ከማህበራዊ ሚዲያ፣ ከማስታወቂያ እና ከምትኖሩበት ዘመን ሁልጊዜ ሞዴሎችን እየቀዳችሁ ነው። አብዛኛው ሰው በውስጡ የተጫነለትን "ስክሪፕት" እየተወነ እንጂ ህይወቱን እየመረጠ አይደለም። ዩንግ እንዲህ ሲል አስጠንቅቋል፡ "unconscious የሆነውን ነገር ወደ conscious እስካላመጣኸው ድረስ፣ ህይወትህን ይመራዋል፤ እናም ዕጣ ፈንታ ብለህ ትጠራዋለህ።" ዘመናዊው ስነ-ልቦና ይህንን "conditioning" ይለዋል፤ neuroscience "neuroplasticity" ይለዋል፤ ጥንታዊ ፍልስፍና ደግሞ "unconscious slavery" ይለዋል። አስፈሪው ነገር ይህ ነው፡ አንድ ሰው "በውስጤ እውን እየተናገረ ያለው ማነው?" ብሎ ሳይጠይቅ ሙሉ ህይወቱን ሊኖር ይችላል። እናንተ ናችሁ? ፍርሃታችሁ ነው? ጎሳችሁ ነው? ጉዳታችሁ? ባዮሎጂያችሁ ነው? ባህላችሁ ነው? ወይስ የተቀባይነት ጥማታችሁ? ማነው እየተናገረ ያለው? የባከነ ህይወት ማለት ብዙ ጊዜ አስደንጋጭ ጥፋት ማለት አይደለም። ለአስርተ ዓመታት የተዘረጋ፣ ሳያውቁት፣ ሳይረዱት መተወን፣ መምሰል ነው። እናም ምናልባት በሁሉም ፍልስፍናዎች ውስጥ ያለው ጥልቅ ጥበብ ይህ ነው፡ የሰው ልጅ በራሱ ላይ የተጫነበትን ማንነት በዝምታ ከመቀበል ተላቆ ራሱን በንቃት መፍጠር ሲጀምር አደገኛ እና ህያው ይሆናል። ንቁ!! እንንቃ!! @zephilisophy

ከመጽሃፍት እና በትንሿ እድሜዬ ከሕይወት የተረዳሁትን አምስት ከባድ እውነቶች ልንገራችሁ። ይጠቅማችሁ ይሆናልና ልብ ብላችሁ አንብቡት። ፀሀፊ- ዮናስ በጋሻው 1. አእምሯችን እውነትን አይፈልግም፤ የሚፈልገው ስነ-ልቦናዊ ህልውናውን ማስጠበቅ ነው። የሰው ልጅ ራሱን የሚያየው እውነታን እንደሚሻ ምክንያታዊ ፍጡር ነው። ግን አብዛኛውን ጊዜ አእምሮ "እውነቱ ምንድነው?" ብሎ አይጠይቅም። ይልቁንም የሚጠይቀው፡ "ማንነቴን ምን ይጠብቅልኛል?" "ተቀባይነት እንዲኖረኝ የሚያደርገኝ ምንድነው?" "በሰላም እንድተኛ የሚፈቅድልኝ ምንድነው?" የሚሉትን ጥያቄዎች ነው። ሰዎች የሚጎዷቸው ግንኙነቶች ላይ የሚጣበቁት፣ በሞቱ ሃይማኖቶች ላይ ሙጭጭ የሚሉት፣ ርዕዮተ-ዓለሞችን የሚያመልኩት፣ በሚጠሉት የሥራ መስክ ውስጥ የሚቆዩት እና ለብዙ አሥርተ ዓመታት እራሳቸውን የሚገድል ልማዶችን የሚደጋግሙት ለዚህ ነው። Ego ተቃርኖን የህልውና ስጋት አድርጎ ነው የሚቆጥረው። ጥንታዊያን ስቶይኮች ይህንን በ "attachment" ውስጥ አይተውታል። ቡድሂዝም በ "desire" እና "illusion" ውስጥ ተመልክቶታል። ካርል ዩንግ ደግሞ እራሳችንን ላለመጋፈጥ በምንገነባቸው "shadows" እና "masks" ውስጥ አይቶታል። ዘመናዊው neuroscience ደግሞ "predictive processing" ውስጥ እየተመለከተው ነው፡ አእምሮ ከትክክለኛ patterኖች ይልቅ የታወቁ (የተለመዱ) patterኖችን ይመርጣል፤ ምክንያቱም መረጋጋት ከለውጥ ይልቅ በሃይል አጠቃቀም ረገድ ርካሽ ነውና። ሰዎች መንቃት ማለት አዳዲስ ሀሳቦችን ማግኘት ይመስላቸዋል። አብዛኛውን ጊዜ ግን መንቃት ማለት ስሜታችሁን አደንዝዘው የያዙትን ውሸቶች መጣል ነው። አብዛኛው ሰው ነፃ የማይወጣው ምቾትን ከእውነት ጋር ስለሚያምታታ ነው። 2. እኛ አንድ ሰው አይደለንም፤ ተፋላሚ ማንነቶች የሚጋደሉበት የጦር ሜዳ ነን። በውስጣችን የበላይነትን ለማግኘት የሚፋለሙ ጥንታዊ የዝግመተ-ለውጥ ስርዓቶች አሉ፡ ደስታን የሚፈልገው እንስሳ፣ ደህንነትን የሚፈልገው ህጻን፣ ደረጃን የሚፈልገው ego፣ ትርጉምን የሚፈልገው ነፍስ፣ መታየትን የሚፈልገው ጥላ እና ሰላምን የሚፈልገው ህሊና። የሰው ልጅ ወጥ ያልሆነው ለዚህ ነው። አንድን ሰው በአንድ ጊዜ እየወደዳችሁዕ ልትጠሉት ትችላላችሁ። ስኬትን እየተመኛችሁ የራሳችሁ እንቅፋት ልትሆኑ ትችላላችሁ። ታላቅነትን እየፈለጋችሁ መታየትን ልትፈሩ ትችላላችሁ። "ራስን መፈለግ" የሚለው ዘመናዊ ቅዠት ስነ-ልቦናዊ ሞኝነት ነው። እንደተቀበረ ሀብት ተቆፍሮ የሚወጣ አንድ ወጥ የሆነ እኔነት የለም። ያለው በሃይሎች መካከል የሚደረግ ድርድር ብቻ ነው። ሲግመንድ ፍሮይድ "ego, id, super ego" ብሎታል። ዩንግ "archetypal conflict" ሲለው፣ ቡድሂዝም "non-self" ይለዋል። neuroscience እንደሚያሳየው ንቃተ-ህሊና ራሱ አንድ ወጥ ገዥ ሳይሆን፣ ከተለያዩ የነርቭ ሥርዓቶች የተገነባና በየጊዜው እንደገና የሚታደስ ሂደት ነው። ውስጣዊ ዘላቂነትን በጠበቃችሁ ቁጥር ስቃያችሁ ይጨምራል። ጥበብ የሚጀምረው "የኔ እውነተኛ ማንነት የትኛው ነው?" ብላችሁ መጠየቅ ስታቆሙ እና "የትኛውን ማንነቴን ነው መመገብ ያለብኝ?" ብላችሁ መጠየቅ ስትጀምሩ ነው። 3. አዕምሮ የመዘናጊያዎች ሱሰኛ ነው ምክንያቱም ዝምታ ሟችነትን ያስታውሳል። ሰዎች የትኩረት መከፋፈልን እንደ ስንፍና ይቆጥሩታል። ግን ስንፍና አይደለም፤ የትኩረት መከፋፈል ህልውናዊ ማደንዘዣ ነው። ሰዎች ለምን ያለ ማቋረጥ ስልካቸውን ይነካካሉ፣ ወሬ ያወራሉ፣ በቁጣ ይሞላሉ፣ ተቀባይነትን ይፈልጋሉ፣ ስራ ያበዛሉ፣ በመዝናኛ ይተበተባሉ፣ ወይም ሁልጊዜ ማነቃቂያ ይፈልጋሉ? ምክንያቱም ስክነት አደገኛ ነው። በዝምታ ውስጥ፣ አእምሮ በህይወት ዘመኑ ሁሉ ሲሸሻቸው የኖረውን ነገሮች መስማት ይጀምራል፡ ሞት፣ ብቸኝነት፣ ጸጸት፣ ባዶነት፣ ነፃነት፣ የጊዜ መክነፍ፣ ትርጉም አልባነት እና የህልውና አስፈሪ ሃላፊነት። ብሌዝ ፓስካል ከክፍለ ዘመናት በፊት እንደጻፈው፣ "የሰው ልጅ ችግሮች የሚመነጩት በአንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው በጸጥታ መቀመጥ ባለመቻሉ ነው።" ዘመናዊው neuroscience የሚያስደነግጥ እውነት አረጋግጧል፡ በእረፍት እና በself-reflection ጊዜ ንቁ የሚሆነው የአዕምሯችን ክፍል ብዙ ጊዜ ወደ ራስ-ተኮር አስተሳሰብ፣ ጭንቀት፣ ማብሰልሰል እና የትረካ ማንነት ግንባታ ያመራል። አማካዩ ሰው እራሱን በቀጥታ ከመጋፈጥ ይልቅ የትኩረት አቅሙ ቢጠፋ ይመርጣል። meditation ከመፈወሱ በፊት የማይቻል የሚመስለው ለዚህ ነው። በዝምታ ውስጥ ትኩረት ከሚሰርቁ ነገሮች ጋር ብቻ አይደለም የምትታገሉት፤ የህልውና ፍርሃታችሁን አርክቴክቸር ነው የምትጋፈጡት። ይቀጥላል @zephilosophy

📝 የፖለቲካ ንቃተ ህሊናውን ያላዳበረ ማህበረሰብ  የፖለቲካ አመራሩን እርካብ ያለአገባብ በሚቆናጠጡ ኃይሎች ላይ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅሙ ደካማ ነው። ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማለት ማህበረሰብ ስለ መብቶቹ፣ ኃላፊነቶቹ እና በዙሪያው ባሉ የስልጣን አወቃቀሮች ላይ ያለው ግንዛቤ እና ንቁ ተሳትፎው ነው። ወይም በአጭሩ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማለት ህዝብ መብቱን፣ ግዴታውን እና መንግስታዊ አወቃቀሮችን በግልጽ ማወቅ ማለት ነው። ንቃተ ህሊናውን ያላዳበረ ማህበረሰብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴው ውስን፣ ደካማ ወይም በቀጥታ በቁጥጥር ሥር የዋለ ሊሆን ይችላል። እንዲህ ያለው ማህበረሰብ የፖለቲካ እንቅስቃሴውን ፍትሃዊ ወይም ሚዛናዊ ባልሆነ ሁኔታ በሚቆጣጠሩ ኃይሎች ላይ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅሙ ደካማ ስለሆነ፣ የሚከተሉትን ችግሮች ያስከትላል፦ 🔴 ሃብት እና ስልጣን በጥቂቶች እጅ ይከማቻል፤ 🔴 መንግሥታዊ ተጠያቂነት ይዳከማል፤ 🔴 የምርጫ ሂደት ሲከናወን፣ ዜጎች ችላ ይባላሉ፤ 🔴 ማህበረሰቡ ከማህበራዊ ፍትሕ እና ከፖለቲካዊ እርካብ ይርቃል። ስለዚህ ዘላቂ ዴሞክራሲ ለመገንባት የፖለቲካ ትምህርት እና ንቃተ ህሊና ማስፋፋት መሠረታዊ ጉዳይ ነው። ንቁ ዜጋ ብቻ ነው ሥርዓተ ፖለቲካውን የሚቀርጽ እና የራሱን እጣ ፈንታ የሚወስን ኃይል የሚሆነው። በመሆኑም የፖለቲካ ንቃተ ህሊና እጦት እና ጥቂት ተሳትፎ ያለው ማህበረሰብ የህዝባዊ አመራር ይዘት በሌላቸው የፖለቲካ ኃይሎች ላይ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅሙ ደካማ ነው። ማንኛውም ማህበረሰብ በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በማህበራዊ ዕድገት እንዲገሰግስ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ከፍተኛ ሚና አለው። ምክንያቱም ጥልቅ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ያላቸው ዜጎች ስለ መብታቸው፣ ስለ ግዴታቸው፣ ስለ መንግሥት አሠራር እና ስለ ህዝብ ተሳትፎ ፍትሃዊ ግንዛቤ ስለሚኖራቸው ነው። ይህ ግንዛቤ በማህበረሰቡ ውስጥ በበለጠ ሲያድግ ህዝቡ በራሱ ዕጣ ፈንታ ላይ ተጽእኖ ማሳረፍ ይችላል። የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ያላዳበረ ማህበረሰብ ግን በፖለቲካ ተሳትፎ ደካማ ይሆናል። እንዲህ ያለ ማህበረሰብ በምርጫ ጊዜ ብቻ የሚነቃ ሲሆን፣ ከዚያ ውጭ በሀገር ጉዳይ ላይ አስተያየት ለመስጠት ወይም ተጠያቂነት ለመጠየቅ ፍላጎቱ እና ችሎታው ዝቅተኛ ይሆናል። ይህም የፖለቲካ ኃይሎች ወይም የሥልጣን ባለቤቶች ያለ ቁጥጥር እንዲንቀሳቀሱ እድል ይፈጥራል። ንቃተ ህሊና የሌለው ማህበረሰብ ብዙ ጊዜ በወሬ፣ በፕሮፓጋንዳ ወይም በጊዜያዊ ስሜት ይመራል። እውነታን በመመርመር ፋንታ የሚነገረውን ብቻ ይቀበላል። ይህ ደግሞ ለፖለቲካ ማታለያ፣ ለክፍፍል እና ለግጭት በር ይከፍታል። አንድ ህዝብ መብቱን ካላወቀ መብቱን ማስከበር አይችልም፤ ተጠያቂነትንም ከመንግሥት መጠየቅ ይከብደዋል። በሌላ በኩል የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ያደገበት ማህበረሰብ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ንቁ ተሳታፊ ይሆናል። ዜጎች የራሳቸውን ድምጽ ያሰማሉ፣ ፍትሕን ይጠይቃሉ፣ መንግሥትንም በህግ እና በሥርዓት ውስጥ እንዲሠራ ግፊት ያደርጋሉ። ይህ የተሻለ ዴሞክራሲ፣ ፍትሕ እና ሀገራዊ መረጋጋት እንዲገነባ ያግዛል። ስለዚህ የፖለቲካ ንቃተ ህሊናን ማሳደግ የመንግሥት፣ የትምህርት ተቋማት፣ የሚዲያ እና የሲቪል ማህበራት የጋራ ኃላፊነት ነው። ንቁ እና አስተዋይ ማህበረሰብ ብቻ በፖለቲካው ላይ ተጽእኖ ማሳረፍ ይችላል፤ የራሱንም ዕጣ ፈንታ በራሱ እጅ ማስቀመጥ ይችላል። ፀሀፊ-አንበሴ ደበበ @zephilo

ዓለም በ“አሜን” ባዮች ስለተከበበች በየጊዜው መንታ መንገዶች ላይ ቆማ ወደ ፊት ለመራመድ ታመነታለች። በድንቁርና ውስጥ መጠፋፋትን ማለም ዕጣ ፈንታዋ ይሆናል።አዲስ አሻራና ታሪክን የሚያሳርፍ አይገኝም። አይደለም ሰዎች ከተማዎች በዚያ ዓይነት ድብታ ውስጥ ያንቀላፋሉ። ትውልድ እየመጣ ትውልድ ይሄዳል። ነገር ግን የተለየ አብዮት አይከሰትም። ሁሉም “አሜን” እያለ ያደገድጋል። የቀረበለትን ያነግሣል። “ጠላትህ ነው” ተብሎ የተነገረውን ይጠላል። “ወዳጅህ ነው” ተብሎ የተነገረውን ይወድዳል። ምክንያትን አይጠይቅም። ሲደሰትም፣ ሲቆጣም፣ ሲለግምም፣ ሲያብርም… በስሜት ላይ እንጂ በተረጋገጠ ገዢ እውነታ ላይ ተመሥርቶ አይደለም። ከዚህ ውስጥ ‘ለምን?’ ብሎ የሚጠይቅ ሰው ይዘን የመጣናቸውን ፍሬዎች በነሲብ ከመብላታችን በፊት በጥንቃቄ እንድንመዝናቸው ያነቃናል። ምክንያቱም ሁሉም የሐሳብ ፍሬ አይበላም። የተበላሹ ፍሬዎች ሊያጋጥሙን ይችላሉ። በመዳፋችን የያዝናቸውን መልካም በረከቶችና ክፉ መርገሞችን እናነጻጽራለን። እጃችን ላይ ያለው ምንድን ነው? ምንስ እናድርግበት? አንድ ማኅበረሰብ የመጣበትን መንገድ ቆም ብሎ እንዲፈትሽ የሚያደርጉት እንቢተኞች ናቸው። አልገባኝም ደራሲ -ዮናስ ዘውዴ @zephilosophy

ጎህ እንደቀደደ፤ በሚጣፍጥ ዜማ መላክ ከሰማይ ላይ፤ እንዲህ ሲል ተሰማ ቶሎ ቶሎ ውደድ የድሜህ ጀንበር ሳይጠልቅ፤ ሳይውጥህ ጨለማ በህይወት መስከር ነው፤በፍቅር መመርቀን የፊት የፊቱን ኑር፤ ምንድነው ሰቀቀን ህያው ፍጥረት ሁሉ ያከትማል አንድ ቀን። ኡመር ሀያም @zephilsophy