fa
Feedback
ሰሌዳ | Seleda

ሰሌዳ | Seleda

رفتن به کانال در Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ሰሌዳ | Seleda

کانال ሰሌዳ | Seleda (@seledadotio) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 52 968 مشترک است و جایگاه 4 908 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 591 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 52 968 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 27 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -129 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -13 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 18.68% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.45% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 9 898 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 8 187 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 66 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 28 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

52 968
مشترکین
-1324 ساعت
-347 روز
-12930 روز
آرشیو پست ها
የአሜሪካና ኢራን ጥቃት‼️ አዳሩን አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ ዳርቻ ላይ በሚገኘው የኢራን ቴሌኮሙኒኬሽን ተቋምና እና ሌሎች ወታደራዊ ማዕከላት ላይ ጥቃት መፈፀሟን ተከትሎ ኢራን በባህሬን እና በኩዬት በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም ከባድ ጉዳት አድርሳለች። ትራምፕ ኢራንን ከምድረገፅ አጠፋታለሁ የሚል ፅሁፍ ያሰፈሩ ሲሆን የኑክሌር ቦንብ ሊጠቀሙ ይሆን? የሚል ስጋት ደቅኗል።

የሆሳዕናው የውሻ ግድያ 2 ህጻናት ተማሪዎች በእብድ ውሻ በሽታ መሞታቸውን ተከቶሎ የተፈፀመ ነው‼️ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በራቢስ (የእብድ ውሻ) በሽታ ምክንያት ከአንድ ቤት የ6ኛ
የሆሳዕናው የውሻ ግድያ 2 ህጻናት ተማሪዎች በእብድ ውሻ በሽታ መሞታቸውን ተከቶሎ የተፈፀመ ነው‼️ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በራቢስ (የእብድ ውሻ) በሽታ ምክንያት ከአንድ ቤት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ጨምሮ የሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ፣ በነዋሪዎችና በእድር አማካኝነት ሰፊ የውሻ ግድያ ዘመቻ መጀመሩ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል። በከተማዋ አስተዳደር ግብርና ጽሕፈት ቤት መረጃ መሠረት በሆሳዕና ከተማ ውስጥ በአጠቃላይ ከ 10,500 በላይ ውሾች የሚገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 7,500 የሚሆኑት ባለቤት ያላቸው ሲሆኑ 7,200 ያህሉ የተከተቡ ናቸው። ይሁን እንጂ ቀሪዎቹ 3,000 የሚጠጉት ውሾች ባለቤት የሌላቸውና በየአደባባዩ የሚገኙ በመሆናቸው ለበሽታው መስፋፋትና ለሕዝብ ስጋት ዋነኛ ምክንያት መሆናቸው ተገልጿል። የሰው ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ በተፈጠረ ድንጋጤ ነዋሪዎች ጤነኛ የሆኑና የተከተቡ የቤት ውሾችን ጭምር በገመድ በማነቅና በተለያዩ መሣሪያዎች በጭካኔ እየገደሉ መሆኑን የገለጹት የከተማው ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ለፋሞ፣ ይህ ዓይነቱ ድርጊት የእንስሳትን ጤናና ደህንነት ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1376/2017 የሚጻረርና በሕግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ ድርጊቱን የማስቆም ሥራ እየተሠራ መሆኑንና ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ጥፋተኞችን ለመለየት መረጃ እየተሰበሰበ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

“ኢራን ከዚህ በኋላ አትኖርም” ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነቱ አደጋ ውስጥ ከገባ በኃላ ኢራን ዳግም አትኖርም ሲሉ መዛታቸው ተሰምቷል፡፡ ኢራ
“ኢራን ከዚህ በኋላ አትኖርም” ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነቱ አደጋ ውስጥ ከገባ በኃላ ኢራን ዳግም አትኖርም ሲሉ መዛታቸው ተሰምቷል፡፡ ኢራንና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነትን በመጣስ እርስ በእርሳቸው ጥቃት መሰንዘራቸውን ተከትሎ፤ መወቃቀሳቸውን ቀጥለዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አገራቱ ስምምነቱን ከፈጸሙ ከጥቂት ቀናት በኋላ የአሜሪካ ማዕከላዊ ኮማንድ በቴህራን በርካታ ኢላማዎችን መመታቸውን አስታውቀዋል። ጥቃቱን ለመሰንዘሩ ኢራን ስምምነቱን የሚጥስ ተግባር በመፈጽሟ ነው ብለዋል፡፡ ትራምፕ በቱርዝ ሶሻል ሚዲያ ባጋሩት መልዕክት ኢራን በጭራሽ መማር የማትችል ናት ብለዋል፡፡ ቴህራን የሰላም ስምምነቱን መጣስ ካላቆመች ከዚህ በኃል አትኖርም ሲሉ ዝተዋል፡፡ ኢራን በበኩሏ ፤አሜሪካ ስምምነቱን በመጣሷ በዮርዳኖስ፣ ባህሬን እና ኩዌት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት መሰንዘሯን አስታውቃለች፡፡

ኢትዮጵያ፣ አውሮፓ ኅብረት ወደ አገራቸው ሊባረሩ የማይችሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለመላክ ከመረጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሂውማን ራይትስ ዎች ገለጠ። ተቋሙ፣ ኅብረቱ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሦስተኛ አገራት ለመላክ አዲስ ስልቶችን እየቀየሠ ይገኛል በማለት ወቅሷል። ጀርመን፣ ኦስትሪያ፣ ዴንማርክ፣ ግሪክ እና ኔዘርላንድስ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለመላክ ከመረጧቸው አገራት መካከል፣ ኢትዮጵያ፣ ኡጋንዳ፣ ሩዋንዳ፣ ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ሊቢያ እና ሞሪቴኒያ እንደሚገኙበት ተቋሙ ጠቅሷል። ተቋሙ፣ ተቀባይ አገራት የጥገኝነት ጠያቂዎቹን ሰብዓዊ መብት ያከብሩ፣ ወደ ትውልድ አገራቸው ይመልሷቸው ወይም ያስሯቸው እንደኾነ ግልጽ አይደለም ሲል ስጋቱን ገልጧል። የኅብረቱ አገራት ይህንኑ እቅድ እንዲተውት ያሳሰበው ተቋሙ፣ ይህ ካልሆነ ግን እቅዱ ተግባራዊ ከመኾኑ በፊት ኅብረቱ ቢያንስ በተቀባይ አገራት የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ጥብቅ ግምገማ እንዲያደርግ እቅዱን የሚቃወሙት የፈረንሳይና ስፔን መሪዎች ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል። @Seledadotio @Seledadotio

ትራምፕ በምስላቸው ያጌጠ አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረጉ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የሀገሪቱን 250ኛ የነጻነት በዓል ለማዘከር የተዘጋጀ ልዩና ውስን የፓስፖርት ዲዛይን ይፋ አድርገዋል።
ትራምፕ በምስላቸው ያጌጠ አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረጉ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የሀገሪቱን 250ኛ የነጻነት በዓል ለማዘከር የተዘጋጀ ልዩና ውስን የፓስፖርት ዲዛይን ይፋ አድርገዋል። “አርበኛዊ ባዊ ፓስፖርት” (Patriotic Passport) የተሰኘው ይህ ፓስፖርት፣ በትራምፕ የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ የቀረበ ሲሆን የፕሬዝዳንቱን ምስል እና ፊርማ አካትቷል። ​በጀርባው ላይ ደግሞ የ1776ቱ የነጻነት አዋጅ ፊርማ ስነ-ስርዓት ምስል እና “Welcome, but be good!” (እንኳን ደህና መጡ፣ ግን መልካም ሁኑ!) የሚል መልዕክት ተጽፎበታል። ​ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በትራምፕ የታሪፍ ዛቻ ዙሪያ ከአውሮፓ ህብረት ጠንከር ያለ ምላሽ ተሰጥቷል። ህብረቱ ትራምፕ ታሪፍ ከጣሉ ፈጣንና ወሳኝ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል። @Seledadotio @Seledadotio

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች:- ✅ ከጠዋቱ 4፡00-ቀኑ 9፡30 👉 ሜክስኮ፣ ብሔራዊ ፣ ሰንጋተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፣ ኩባ ፓርክ፣ ተ/ሃይማኖት፣ በርበሬ በረንዳ፣ ዲአፍሪካ  እና አካባቢያቸው ፣ ✅ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 👉ጎፋ ካምፕ፣ ጀርመን አደባባይ፣መከኒሳ አረቄ  ፋብሪካ፣ላፍቶ፣ ቄራ፣ቆሼ፣ ዘነበወርቅ፣ጎፋ እና አካባቢያቸው ፣ ✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30 👉ሸገር ዳቦ፣  ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ለገ ጣፎ ከተማ ፣ የካሰዴ፣የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ወሰን ግሮሰሪ፣ ሲኤምሲ ሚካኤል፣ ካራሎ፣ለገጣፎ፣ ሲዲሲ ፣ ኮሰሮ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲሬ ጎዩ፣ የካ ሰዴ፣ድሬ ሰኩር  እና አካባቢያቸው፣ 👉 ጁኒፐር ግላስ፣ ደጋ ውሃ፣ ቻንግልዶንግራን፣ ፊበላ፣ ቦልት ማልት፣ ሃዋ ትሬዲንግ፣ ብራውን ፉድ ፣ ማማ ዱኬት ፋብሪካዎች እና አካባቢያቸው ፣ ✅ ከለሊቱ 6፡00-ቀኑ 6፡00 👉 ድሬደዋ ውሃ፣ ፓይነር ሲሚንቶ፣ ቱሬ ሲሚንቶ፣ ሀረር ውሃ፣ ማረሚያ፣ ኩርቱ፣ በለዋ፣ ቃልቻ፣ ቢሻን በሄ፣ ሃሎብሳ፣ ለጎዳ፣ አሳሊሶ፣ ኢንዱስትሪ ኮንዶሚኒየም፣ ሻሎም ኢንጂነሪንግ፣ መልካ፣የኢንዱስትሪ እና አካባቢያቸው፣ ✅ ከጠዋቱ 1፡30-5፡00 👉አዳማ ከወንጂ ቀበሌ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢያቸው ፣ ✅   ከጠዋት 12፡00-12፡00 👉በአሰላ፣ አዳሚቱሉ፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ እና አካባቢው ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ውድ ደንበኞቻችን፤ የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች:- ✅ ከጠዋቱ 4፡00-ቀኑ 9፡30 👉 ሜክስኮ፣ ብሔራዊ ፣ ሰንጋተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፣ ኩባ ፓርክ፣ ተ/ሃይማኖት፣ በርበሬ በረንዳ፣ ዲአፍሪካ  እና አካባቢያቸው ፣ ✅ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 👉ጎፋ ካምፕ፣ ጀርመን አደባባይ፣መከኒሳ አረቄ  ፋብሪካ፣ላፍቶ፣ ቄራ፣ቆሼ፣ ዘነበወርቅ፣ጎፋ እና አካባቢያቸው ፣ ✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30 👉ሸገር ዳቦ፣  ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ለገ ጣፎ ከተማ ፣ የካሰዴ፣የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ወሰን ግሮሰሪ፣ ሲኤምሲ ሚካኤል፣ ካራሎ፣ለገጣፎ፣ ሲዲሲ ፣ ኮሰሮ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲሬ ጎዩ፣ የካ ሰዴ፣ድሬ ሰኩር  እና አካባቢያቸው፣ 👉 ጁኒፐር ግላስ፣ ደጋ ውሃ፣ ቻንግልዶንግራን፣ ፊበላ፣ ቦልት ማልት፣ ሃዋ ትሬዲንግ፣ ብራውን ፉድ ፣ ማማ ዱኬት ፋብሪካዎች እና አካባቢያቸው ፣ ✅ ከለሊቱ 6፡00-ቀኑ 6፡00 👉 ድሬደዋ ውሃ፣ ፓይነር ሲሚንቶ፣ ቱሬ ሲሚንቶ፣ ሀረር ውሃ፣ ማረሚያ፣ ኩርቱ፣ በለዋ፣ ቃልቻ፣ ቢሻን በሄ፣ ሃሎብሳ፣ ለጎዳ፣ አሳሊሶ፣ ኢንዱስትሪ ኮንዶሚኒየም፣ ሻሎም ኢንጂነሪንግ፣ መልካ፣የኢንዱስትሪ እና አካባቢያቸው፣ ✅ ከጠዋቱ 1፡30-5፡00 👉አዳማ ከወንጂ ቀበሌ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢያቸው ፣ ✅   ከጠዋት 12፡00-12፡00 👉በአሰላ፣ አዳሚቱሉ፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ እና አካባቢው ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ውድ ደንበኞቻችን፤ የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

''ወላጅ እናቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ታዳጊ በቁጥጥር ስር ዋለ'' ደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ ​ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ፣ አየር ጤና ቀበሌ ውስጥ ወላጅ እናቱን
''ወላጅ እናቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ታዳጊ በቁጥጥር ስር ዋለ'' ደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ ​ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ፣ አየር ጤና ቀበሌ ውስጥ ወላጅ እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረው ወጣት ዮሴፍ ከበደ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ። ​የክፍለ ከተማው ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ሟች ወ/ሮ ፍሬህይወት ገብረሚካኤል ተከራይታ ትኖርበት የነበረውን የተቆለፈ ቤት በር ሰብሮ በመግባት ባደረገው ፍተሻ፤ ሟች አንገቷ በቢላ ተቆርጦና ለብቻው በማዳበሪያ ተቋጥሮ መገኘቱን አስታውቋል። በፖሊስ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣራት ግድያው የተፈፀመው ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ.ም አካባቢ ሲሆን፣ የቤቱ የውጭ በርም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ተቆልፎ ሰንብቷል። ​ፖሊስ አስከሬኑን ካነሳ በኋላ ባደረገው ፈጣን ክትትል፣ ወንጀሉን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ የሸሸውና የ"666" አባል እንደሆነ የተነገረለት የሟች ልጅ ዮሴፍ ከበደ፤ ተመልሶ አክስቱ ቤት ተደብቆ ሳለ ወንጀሉን ከፈፀመበት ቢላ ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል። ​የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን እየተመኘ ይህ አሰቃቂ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ሌት ተቀን በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጧል። Via:- ደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ

በአንዳንድ ክፍለከተሞች በቤት ኪራይ ዉል ላይ የተቀመጠዉ የዋጋ ተመን እና ቤቱ የማይጣጣም እንደሆነ እየታወቀ እንኳን ጭማሪዉ በዉሉ መሠረት እንዲሆን ተደርጓል ሲል የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ገለፀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ እንደገለፁት፥ "የ11.5 በመቶ የዋጋ ጭማሪ የተደረገዉ ዉሉ ላይ በተቀመጠዉ እንጂ በደበቃችሁት ላይ አይደለም "ሲሉ  ከአከራይ ተከራይ ተወካዮች ጋር በተደረገ ዉይይት ላይ ተናግረዋል። ሰኔ 30 ጀምሮ የሚተገበረዉ የቤት ኪራይ ዋጋን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ አመታዊ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናት በትናንትናው ዕለት ለዉይይት ቀርቧል። ስለጥናቱ ገለፃ ያደረጉት በአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ተመራማሪዉ አቶ ኑርአሁን አንዳርጌ፥በዚህ ጥናት የዋጋ ትመና ለማድረግ የተለያዩ መስፈርቶች መካተታቸውን ገልፀዋል። የዋጋ ግሽበት፣ የቤቱ መገኛ እና የቤት ስፋት እንዲሁም ከመንገድ ያለ ርቀት ያሉ ከግምት ማስገባቱ ተገልጿል። ተመራማሪዉ ጥናቱን ለማድረግ በከተማዋ ያለዉን የህዝብ ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ እንደነበር በመግለጽ የህዝቡ ቁጥር መብዛት የፍላጎት እና አቅርቦት አለመመጣጠን ፈጥሯል ብለዋል። እስከአሁን ወጥ የሆነ አሰራር ባለመኖሩ ምክንያት 28 በመቶ አከራዮች በየጊዜው በዘፈቀደ የዋጋ ማሻሻያ ያደርጉ እንደነበር በመድረኩ ተገልጿል። በጥናቱ የተሳተፉት ተመራማሪዉ እንዳስረዱት አከራይ እንደፈለገ ዋጋ ቢጨምር አብዛኛውን ሰዉ በረንዳ ይወጣል ፤ ይህ መንግስት ጣልቃ እንዲገባ የሚያስገድድበት አሰራር ሆኖል ብለዋል። በአለምአቀፍ ደረጃ አንድ ሰዉ ከገቢዉ ለቤት ኪራይ 30 በመቶ መክፈል ያለበት ቢሆንም በኢትዮጵያ አሁን ላይ በተገኘዉ ጥናት አንድ ሰዉ ከገቢ ላይ የቤት ኪራይ ወጪዉ ከ50 እስከ 80 በመቶ እንደሚደርስ ተጠቁሟል። በትናንትናው የዉይይት መድረክ የተካፈሉ የአከራይ እና ተከራይ ተወካዮች በዋጋ ጭማሪዉ ዙሪያ ለአስተዳደሩ ጥያቄዎችን አንስተዋል። ከአራዳ ክፍለከተማ እንደመጡ የተናገሩት ተሳታፊ ሀሳባቸውን ሲገልፁ፥"አከራዩም ሆነ ተከራዩ የችግሩ አካል ነዉ፤ በዚህ ላይ የጋራ መግባባት ያስፈልጋል"ይላሉ። የ11.5 በመቶ የዋጋ ጭማሪዉ ለአከራዩም ሆነ ለተከራዩ የዋጋ ተመኑ ሚዛናዊነት ላይ ጥያቄ አንስተዋል።  ሌላኛዉ ከኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ እንደመጡ የገለፁ ተሳታፊ በቤት ኪራይ ዙሪያ በአከራይ እና በተከራይ በኩል የመደባበቅ ሂደቶች አሉ ፤ ይሄንን ግልፅ ማድረግ ካልተቻለ ፍትሀዊ የአከፋፈል ስርአት ማምጣት እንደማይቻል አንስተዋል። በመድረኩ የ11.5 በመቶ ዋጋ ጭማሪ በመሀል ከተማ እና በማስፋፊያ አካባቢዎች ለምን እኩል ይጨመራል? ይህን ጭማሪ አሁንስ ተከራዩ ጨምሮ መክፈል ይችላል ወይ? የሚሉ ሀሳቦች ተነስተዋል። ለተነሱ ሀሳብ እና ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የቢሮዉ ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ፥ በዉሉ መሠረት የተቀመጠዉን ዋጋ መነሻዉ ተንተርሶ በጥናቱ መሠረት ጭማሪ  መደረጉን ገልፀዋል። በአንዳንድ ክፍለከተሞች በቤት ኪራይ ዉል ላይ የተቀመጠዉ የዋጋ ተመን እና ቤቱ የማይጣጣም እና የማይገጣጠም እንደሆነ እየታወቀ እንኳን ዉሉ ህጋዊ አድርገን ጭማሪዉ ተደርጓል ሲሉ ተናግረዋል። የ11.5 በመቶ የዋጋ ጭማሪ የተደረገዉ ዉሉ ላይ በተቀመጠዉ እንጂ በደበቃችሁት ላይ አይደለም በማለትም ገልፀዋል። "ዋጋ ሲጨመር ዉሉ ላይ ባለዉ ነዉ የተጨመረዉ መጀመሪያ ስታከራዩ በማስፋፊያ እና በመሀል ከተማ በልዩነት እንዳከራያችሁ ሁሉ አሁን የተጠናዉ ጭማሪ በዉሉ መሠረት የሚጨምር ነዉ፤ ለማስፋፊያ አካባቢ ዝቅ ያለ ለመሀል ከተማ ከፍ ያለ ጥናት አልተጠናም "ሲሉ አስረድተዋል። በመጪዉ አመት 11.5 በመቶ ጭማሪ የተደረገበትን አግባብ ያስረዱት ሀላፊዋ፥"ጭማሪዉ በጣም ከፍ ያለ ነዉ ብለን እኛ አልወሰድንም ቢያንስ የፌዴራል ጥናትን እንኳን ወስደን ተግባራዊ ብናደርግ  እንደ ከተማ አስተዳደር  ጥናት ዉስጥ ስናስገባዉ ትንሽ ነዉ የጋሸበዉ ፤ ይሄን ተከራዩ መክፈል ይችላል ብለን ነዉ  የወሰድነዉ" ሲሉ አስረድተዋል። በከተማዋ ከ50 ሺህ በላይ የኪራይ ቤቶች ተመዝግበዉ ወደ ሲስተም እንደገቡ ተገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio

በአዶላ ከተማ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ወርቅ ለማግኘት መሬቱን እየቆፈረ ነው።" በማህበራዊ ሚዲያ እጅግ መነጋገሪ ከሆኑት እንድ የሆነው የአዶላ ህዝብ በመናኽሪያ ጭምር እና በየቦታው ወርቅ ና ማዕድን ፍለ
+5
በአዶላ ከተማ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ወርቅ ለማግኘት መሬቱን እየቆፈረ ነው።" በማህበራዊ ሚዲያ እጅግ መነጋገሪ ከሆኑት እንድ የሆነው የአዶላ ህዝብ በመናኽሪያ ጭምር እና በየቦታው ወርቅ ና ማዕድን ፍለግ መሬቱን እየቆፈ ነው፡፡ በኦሮሚያ ክልል አዶላ በተባለችው ከተማ በአሁኑ ወቅት እጅግ ያልተለመደ እና አነጋጋሪ ክስተት እየታየ ይገኛል። በከተማዋ አሸዋማ እና አፈራማ አካባቢዎች ውስጥ ወርቅ እንዲሁም የከበሩ ድንጋዮች በብዛት ተገኝተዋል የሚል ወሬ በስፋት መሰራጨቱን ተከትሎ፣ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ አካባቢውን ወርሯታል። ይህንን ተከትሎ ህፃናት፣ ወጣቶች እንዲሁም አዛውንቶች ሳይቀሩ በከተማዋ በተለያዩ ስፍራዎች፣ በመናኽሪያ አካባቢ ጭምር አፈሩን ሲቆፍሩ ውለው እያደሩ መሆናቸውን ከተለያዩ ምስሎችና ቪዲዮዎች ለመረዳት ተችሏል። ነዋሪዎቹ በቡድን በመሆን ፍለጋቸውን በከፍተኛ ጉጉት አጠናክረው የቀጠሉ ሲሆን፣ አንዳንዶች በቁፋሮ ያገኟቸውን የሚያንፀባርቁ፣ ትላልቅ እና የከበሩ ድንጋይ የሚመስሉ ማዕድናት በሞባይል ስልክ ብርሃን እያበሩ ሲያሳዩ ይታያል። ይህ በድንገት የተቀሰቀሰው ህዝባዊ የማዕድን ፍለጋ ግርግር በከተማዋ የዕለት ተዕለት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ የራሱን ትልቅ ጫና እያሳደረ ይገኛል።gursha

ባንኩ ከ9:00 በኋላ አገልግሎት አይሰጥም! ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (June 30, 2026) የዓመቱ በጀት መዝጊያ ቀን ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በዕለቱ ሁሉም የባንኩ ቅርንጫፎች ከቀኑ 9፡
ባንኩ ከ9:00 በኋላ አገልግሎት አይሰጥም! ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (June 30, 2026) የዓመቱ በጀት መዝጊያ ቀን ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በዕለቱ ሁሉም የባንኩ ቅርንጫፎች ከቀኑ 9፡00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት እንደማይሰጡ አሳውቋል። በዚህም ባንኩ ደንበኞቹ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እዲያደርጉ ያሳሰበ ሲሆን ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች አገልግሎት እንደማይቋረጥ ገልጿል።         

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ስደተኞች ሀገሪቱን ጥለው እየሸሹ ነው! እንደ አልጀዚራ (Al Jazeera) የዜና ዘገባ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው ከፍተኛ የውጭ ዜጎች ጥላቻ (Xenophobia) እና
በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ስደተኞች ሀገሪቱን ጥለው እየሸሹ ነው! እንደ አልጀዚራ (Al Jazeera) የዜና ዘገባ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው ከፍተኛ የውጭ ዜጎች ጥላቻ (Xenophobia) እና ጥቃት ምክንያት፣ እንዲሁም June 30 ሊደረግ ከታቀደው መጠነ-ሰፊ ፀረ-ስደተኞች ሰልፍ አስቀድሞ በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞች ሀገሪቱን በከፍተኛ ስጋት እየለቀቁ ይገኛሉ። እንደ ማላዊ፣ ዚምባብዌ፣ ናይጄሪያ፣ ጋና እና ሞዛምቢክ ያሉ የአፍሪካ ሀገራት መንግስታት ዜጎቻቸውን በፈቃደኝነት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ (Repatriation) የአውቶቡስ እና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶችን እያደረጉ ሲሆን፣ በርካታ ስደተኞችም ጥበቃ ፍለጋ በየሀገራቱ ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች ደጅ ላይ ተሰባስበው ይገኛሉ። ይህ የጊዜ ገደብ መጀመሪያ ላይ የደቡብ አፍሪካን መንግስት አርማ ተጠቅሞ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት በተሰራጨ የሀሰት (AI-generated) ፖስተር የተነሳ የመጣ ቢሆንም፣ "ማርች ኤንድ ማርች" (March and March) የተባሉ የፀረ-ስደተኛ አደረጃጀቶች እና ቡድኖች ግን ህገ-ወጥ ስደተኞች በሙሉ እስከ June 30 ድረስ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ በማስገደድ የራሳቸውን መጠነ-ሰፊ ዘመቻ ከፍተዋል። ምንም እንኳን የተሰጠው የጊዜ ገደብ ህጋዊ ባይሆንም፣ በተለያዩ ከተሞች (ለምሳሌ በሞሰል ቤይ) በስደተኞች መኖሪያ ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል፣ ቤቶች ተቃጥለዋል፣ ንብረቶች ተዘርፈዋል እንዲሁም የሰው ህይወት ጠፍቷል። ጋና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿን በልዩ የአየር በረራ የመለሰች ሲሆን፣ ማላዊ ከ5,000 በላይ ሰዎችን በባስ ለማጓጓዝ እየሰራች ነው። ናይጄሪያ እና ሞዛምቢክም በተመሳሳይ ሁኔታ ዜጎቻቸውን የማስወጣት ስራ ላይ ናቸው። ጉርሻ

ውሻዉን ያልገደለ ግለሰብ በ50,000 ብር እና በእስራት እንዲቀጣ ታወጀ ! በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሆሳና ከተማ እያንዳንዱ ግለሰብ በቤቱ ያለዉን ዉሻ አውጥቶ እንዲገድል በታወጀው መሰረት ዉሻ ያላቸው ግለሰቦች .... ዉሻቸውን ገመድ በማጥለቅ በቀንጨት ላይ በማንጠልጠል ዉሾችን እያነቁ እየገደሉ መሆኑን በትናንትናው ዕለት ግዮን ማለዳ ዘግቦ ነበር። በሆሳእና ከተማ ከሰሞኑ በውሻ ምክንያት በሽታ ተከስቷል የተባለ ሲሆን ይህ የውሻ ግድያ ዘመቻ የተጀመረው አንድ ውሻ የ13 አመት ልጅ ነክሳው ከሞተ በኋላ መሆኑን ታውቋል። ቪዲዮዎች Ghion Maleda የቴሌግራም ቻናል እንደምታዩት የራሳቸው ባለቤት ያላቸውና ክትባት የተሰጣቸው ውሾችን ጨምሮ በእጅግ አሰቃቂ ሁኔታ በመንጋ ውሾችን እያስጮሁ ዛፍ ላይ በማ- ነቅ የገደሏቸው ። በኮምቦልቻ ከተማ የእብድ ውሻ በሽታ (Rabies) ከባድ የሕዝብ ጤና ስጋት መሆኑን ሪፖርቶች ቢወጡም መሰል ከሰባዊነት ያፈነገጠ ተግባር በፍጹም አልተደረገም ነበር ። በሆሳና ከተማ በጣም የሚያሳስበው፣ አንዳንድ ሕፃናት በእነዚህ ድርጊቶች ውስጥ ተሳትፈዋል በቪዲዮዎች ተመልክተናል ።ጉዳዩ የእንስሳት ደህንነት ብቻ ሳይሆን ለሚቀጥለው ትውልድ ምን ዓይነት እሴቶችን እያስተላለፍን እንዳለን የሚያስጠይቅ ነው። ርኅራኄ ይማራል፤ ጭካኔም እንዲሁ ይማራል። የእብድ ውሻ በሽታ (Rabies) ከባድ የሕዝብ ጤና ጉዳይ ነው፣ መቆጣጠር ያስፈልጋል። ሆኖም የሳይንስ ማስረጃዎች እንደሚያሳዩት ችግሩን በዘላቂነት የሚቀንሱት... ሰብዓዊና ውጤታማ መንገዶች እንደ የጅምላ ክትባት፣ የውሾች ማምከን፣ ለሕዝብ ግንዛቤ መስጠት እና ኃላፊነት ያለው የእንስሳት አስተዳደር ናቸው፤ ጭካኔ እና ግፍ ግን መፍትሔ አይደሉም።via Ghion maleda

የ6 ወር ነፍሰ ጡር ባለቤቱን የገደለው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ በጎፋ ዞን በላሃ ከተማ አስተዳደር የ6 ወር ነፍሰ ጡር ባለቤቱን የገደለው ተከሳሽ ጀማል ሁሴን በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን ፖሊስ
የ6 ወር ነፍሰ ጡር ባለቤቱን የገደለው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ በጎፋ ዞን በላሃ ከተማ አስተዳደር የ6 ወር ነፍሰ ጡር ባለቤቱን የገደለው ተከሳሽ  ጀማል ሁሴን በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን ፖሊስ አስታውቋል። ተከሳሹ በጎፋ ዞን በላሃ ከተማ አስተዳደር ሀብት-ምንጭ ቀበሌ ውስጥ ከባለቤቱ ጋር በነበረ የፍትሐ ብሔር ክስ ምክንያት ቂም በመያዝ  በስለታማ መሣሪያ በመውጋት ህይወቷ  እንዲያልፍ ማድረጉን  የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ሀይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ ያቀረባቸው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ክሱን ከጥርጣሬ በላይ እንደሚያስረዱ በመግለጽ ተከሳሹ እንዲከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር። ተከሳሹም "የመከላከያ ማስረጃ የለኝም" በማለቱ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ብሎ ወስኗል። በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የቅጣት አስተያየቶችን ከተቀበለ በኋላ ተከሳሹ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ ማስተላለፉንየደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ሀይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። Via_dagu @Seledadotio @Seledadotio

የቡና ኮንትሮባንድን ለመግታት እስከ 50 ሚሊዮን ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣትና የንብረት መወረስ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ተገለፀ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀገሪቱ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በሆነው የቡና ምርት ላይ የሚፈጸመውን ህገ-ወጥ ዝውውር (ኮንትሮባንድ) ለመግታት፣ ከተባባሪ አካላት ጋር በመቀናጀት እጅግ ጥብቅ የሆኑ የቁጥጥርና የቅጣት እርምጃዎችን መተግበር መጀመሩን አስታወቀ። የቡናና ሻይ ባለስልጣን የዋና ዳይሬክተር ፅህፈት ቤት ሀላፊ ዶር ሰፊሳ አባቡ እንደተናገሩት ህገ-ወጥ የቡና ንግድ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በእጅጉ እየጎዳ በመሆኑ፣ ድርጊቱን በቁርጠኝነት ለመከላከል አዲስ የክትትል ስትራቴጂ ተቀርጾ ወደ ስራ ተገብቷል በዚህም መሠረት ባለስልጣኑ ህገ-ወጥ የቡና ዝውውርን ለማስቆም ከፌዴራልና ክልል ፖሊስ፣ ከጉምሩክ ባለስልጣን እና ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር የጋራ ግብረ-ኃይል አቋቁሞ እየሰራ ይገኛል። በመሆኑም ያለ ህጋዊ ፈቃድና ሰነድ ሲንቀሳቀስ የተገኘ ማንኛውም የቡና ምርት ሙሉ በሙሉ ይወረሳል። በህገ-ወጥ የቡና ሰንሰለት ውስጥ ተሳትፈው በሚገኙ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ም እንደ ጥፋታቸው ደረጃ እስከ 50 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ከባድ የገንዘብ ቅጣት ይጣላል። የኬላዎች ቁጥጥርን በተመለከተም በመረጃዎችን በፈጣን ቴክኖሎጂ በመለዋወጥ፣ በዋና ዋና የቡና አምራች ክልሎችና መውጫ ኬላዎች ላይ ፍተሻዎች ተጠናክረዋል ሲሉ ዶ/ር ሰፊሳ ተናግረዋል::   የኮንትሮባንድ ቁጥጥሩ ውጤታማ የሚሆነው ከመነሻው ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለገበያ ማቅረብ ሲቻል ነው" ያሉት ኃላፊው፣ ምርቱ መሬት ላይ እንዳይሰጣ እና በአልጋ ላይ እንዲደርቅ የማስተማርና የመደገፍ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በተያያዘም የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ በማድረስ በሄክታር የሚገኘውን ምርት ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህ ጥራት ያለው ምርት በኮንትሮባንድ እንዳይባክን የቁጥጥር ስራው ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል

ኢትዮጵያ ጥይት ወደ ውጭ መላክና ወደ ሀገር ውስጥ ዶላር ማስገባት ጀመረች። የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት በሀገር ውስጥ የተመረቱ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን ለጎረቤት ሀገራት መላክ መጀመሩን አስታውቋል። ይ
ኢትዮጵያ ጥይት ወደ ውጭ መላክና ወደ ሀገር ውስጥ ዶላር ማስገባት ጀመረች። የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት በሀገር ውስጥ የተመረቱ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን ለጎረቤት ሀገራት መላክ መጀመሩን አስታውቋል። ይህ አዲስ ጅምር ለሀገሪቱ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ ሲሆን፣ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪዎች ምርቱን በራስ አቅም ማምረታቸው ቀደም ሲል የነበረውን የውጭ ጥገኝነትና ከፍተኛ ወጪ ሙሉ በሙሉ ማስቀረት አስችሏል። አሁን ላይ ምርቶቹን ለኤክስፖርት ማብቃት መቻሉ የኢትዮጵያን የማምረት አቅም ዕድገት የሚያሳይና ለኢኮኖሚዋም ትልቅ ምዕራፍ የሚከፍት ነው። ከዚህ ባለፈም ሀገሪቱ የድሮን እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂዎችን በማልማት የጸጥታ መዋቅሯን በከፍተኛ ሁኔታ እያዘመነች ትገኛለች። በቀጣዮቹ ዓመታትም ከቀላል ጥይቶች ባሻገር የተለያዩ የጦር መሣሪያ አካላትን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሠራ ሲሆን፣ ሂደቱ በትክክል ከተጠናከረ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑት የመከላከያ ኢንዱስትሪ ማዕከላት አንዷ እንደምትሆን ይጠበቃል። Via የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት @Seledadotio @Seledadotio

‹‹TDF እየሸሸ ነው፤ አልዋጋም ብሏል›› ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ‼️ ‹‹ቲዲኤፍ የሚባለው ጦር እየሸሸ ቤቱ ተቀምጧል፤ አልዋጋም ብሏል፤ ትግራይ ያሉ መሪዎች ከሻብያ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ተቀብለው
‹‹TDF እየሸሸ ነው፤ አልዋጋም ብሏል›› ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ‼️ ‹‹ቲዲኤፍ የሚባለው ጦር እየሸሸ ቤቱ ተቀምጧል፤ አልዋጋም ብሏል፤ ትግራይ ያሉ መሪዎች ከሻብያ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ተቀብለው የጦርነት ፍላጎታቸውን አልተዉም፤ ነገር ግን አቅማቸው ስለተመናመነ እየወላወሉ ነው፡፡ በፊት ማስተዳደር በቻሉበት አቅም ማስተዳደር ስላልቻሉ አፋኝ ሕግ አውጥተው ማስተዳደር ነው የሚፈልጉት፤ ቀደም ሲል የሰሩት ወንጀል ለመሸፈን ሌላ ወንጀል እየሰሩ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ጀነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ በዛሬው ዕለት የተናገሩት @Seledadotio @Seledadotio

ሰበር ዜና የአሜሪካ ኤምባሲ ለሕወሓት ማስጠንቀቂያ ሰጠ! የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል ያለውን ችግር ለመፍታት እየተካሄዱ ያሉ የሰላም ሂደቶችን “የሚያደናቅፉ” አካላት፤ በአፍሪካ ህብረት ለሚመራው
ሰበር ዜና የአሜሪካ ኤምባሲ ለሕወሓት ማስጠንቀቂያ ሰጠ! የአሜሪካ ኤምባሲ በትግራይ ክልል ያለውን ችግር ለመፍታት እየተካሄዱ ያሉ የሰላም ሂደቶችን “የሚያደናቅፉ” አካላት፤ በአፍሪካ ህብረት ለሚመራው የውይይት ጥረት “በአስቸኳይ ትብብር” እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡ የፖለቲካ መሪዎች የፕሪቶሪያ የግጭት ማቆም ስምምነትን “ሙሉ ለሙሉ” ተግባራዊ ማድረጋቸው “እጅግ አስፈላጊ” መሆኑንም ኤምባሲው ገልጿል። ኤምባሲው ይህን የገለጸው፤ በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ በቃል አቃባዩ በኩል ዛሬ አርብ ሰኔ 19፤ 2018 ባወጣው መግለጫ ነው። የዛሬው መግለጫ፤ አሜሪካ “አክራሪ” ባለቻቸው የህወሓት አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሏን ካሳወቀች ከአንድ ሳምንት በኋላ የወጣ ነው። የዛሬው የአሜሪካ ኤምባሲ መግለጫ ህወሓትን በቀጥታ ባይጠቅስም፤ “ሆነ ብለው” የሰላም ሂደቶችን “የሚያደናቅፉ” አካላት የሚል አገላለጽ ተጠቅሟል። በክልሉ ያሉ የፖለቲካ እና የሲቪል ማህብረሰብ መሪዎችም፤ “በፖለቲካዊ ውይይት” መሳተፍ እንደሚገባቸውም ኤምባሲው በመግለጫው አሳስቧል። መሪዎቹ በጥቅምት 2015 በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመውን የግጭት ማቆም ስምምነት “ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ” ማድረጋቸው “እጅግ አስፈላጊ” መሆኑንም ኤምባሲው አስገንዝቧል። አሜሪካ ይህን ብትልም የትግራይ ክልልን በአሁኑ ወቅት እያስተዳደረ ያለው ህወሓት፤ የፕሪቶሪያ የግጭት ማቆም ስምምነት “መፍረሱን” በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው መግለጫዎች ሲያስታውቅ ቆይቷል። @Seledadotio @Seledadotio

ታሞ ሊጠይቁት አስራ ሰባት ፍቅረኛሞቹ ሆስፒታል የመጡበት የቻይናዊው አስገራሚ ታሪክ ​በፈረንጆቹ 2015 ሚስተር ዩዋን የተባለ ቻይናዊ ሰው በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ሆስፒታል ይገባል። ይሁን
ታሞ ሊጠይቁት አስራ ሰባት ፍቅረኛሞቹ ሆስፒታል የመጡበት የቻይናዊው አስገራሚ ታሪክ ​በፈረንጆቹ 2015 ሚስተር ዩዋን የተባለ ቻይናዊ ሰው በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ሆስፒታል ይገባል። ይሁንና አደጋው በአካባቢው የዜና ማሰራጫዎች ላይ መተላለፉን ተከትሎ፣ ያላሰበው አስገራሚ ትዕይንት በሆስፒታሉ ውስጥ ተፈጠረ። ሊጠይቁት የመጡ 17 ፍቅረኛሞቹ በአንድ ጊዜ አልጋው አጠገብ ተገኙ! ​ሁሉም ሴቶች እርስ በርሳቸው በፍጹም አይተዋወቁም የነበረ ሲሆን፥ አንዳንዶቹ ከዩዋን ጋር ለዓመታት የዘለቀ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው ታውቋል። ይህ ሚስጥር በአንድ አደጋ ምክንያት በአደባባይ በመጋለጡ፣ በሆስፒታሉ የነበሩ ታካሚዎችና ነርሶች በሁኔታው በእጅጉ ተገርመዋል። ፍቅረኛሞቹም ጉዳዩን ሲረዱ በከፍተኛ ድንጋጤ እና ቁጣ ውስጥ ወድቀው ነበር። @Addis_News @Addis_News

የቤት ኪራይ በተመን ሊወሰን ነው‼️ ከ2019 ጀምሮ የቤት ኪራይ ዋጋ በአዲስ መተመኛ ሊወሰን ነው። በአዲስ አበባ ከተማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን ፍትሃዊ፣ ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ለመወ
የቤት ኪራይ በተመን ሊወሰን ነው‼️ ከ2019 ጀምሮ የቤት ኪራይ ዋጋ በአዲስ መተመኛ ሊወሰን ነው። በአዲስ አበባ ከተማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን ፍትሃዊ፣ ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ለመወሰን የተዘጋጀ የዋጋ መተመኛ ጥናት ዛሬ ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ፊት ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ የኑሮ ጫናን ለመቀነስ እና በቤት ኪራይ ገበያ ውስጥ የተስፋፉ ሕገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታት በተከታታይ እየሰራ ነው። እንደ ኃላፊዋ ገለጻ፣ በ2016 ዓ.ም. የተከናወነው ሰፊ የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ አሁን የቀረበው የኪራይ ዋጋ መተመኛ ጥናትም የውል ማደስ ሂደትን ፍትሃዊና ግልጽ ለማድረግ ያግዛል። ጥናቱ የአከራዮችን ተገቢ ገቢ ከወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ጋር በማጣጣም የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ተከራዮችም ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ እንዲከፍሉ እና የተረጋጋ የኢኮኖሚ ኑሮ እንዲመሩ እንደሚያስችል ተገልጿል። እንዲሁም ጥናቱ የቤት ኪራይ ገበያውን ጤናማና ሊተነበይ በሚችል መልኩ በማደራጀት፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን የእምነት ክፍተት ለመቀነስ እንዲሁም የሕገ-ወጥ ደላሎችን ጣልቃ ገብነት ለመግታት እንደሚረዳ ተጠቁሟል። ጥናቱ በአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፣ በ2019 በጀት ዓመት በተግባር እንደሚውል ተገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio