es
Feedback
ሰሌዳ | Seleda

ሰሌዳ | Seleda

Ir al canal en Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ሰሌዳ | Seleda

El canal ሰሌዳ | Seleda (@seledadotio) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 52 851 suscriptores, ocupando la posición 5 083 en la categoría Noticias y medios y el puesto 606 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 52 851 suscriptores.

Según los últimos datos del 30 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -126, y en las últimas 24 horas de 1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 17.69%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 14.16% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 9 346 visualizaciones. En el primer día suele acumular 7 479 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 56.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Seledanewsbot

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 31 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

52 851
Suscriptores
+124 horas
-517 días
-12630 días
Archivo de publicaciones
ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ሱዳን ካርቱም ገብተዋል! የኢጋድ ሊቀመንበሩ ጉዞ የሱዳኑን አስከፊ ጦርነት በድርደር ለመቋጨት ያለመ እንደሆነ ተዘግቧል፡፡ ባሁኑ ወቅት የሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር
ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ሱዳን ካርቱም ገብተዋል! የኢጋድ ሊቀመንበሩ ጉዞ የሱዳኑን አስከፊ ጦርነት በድርደር ለመቋጨት ያለመ እንደሆነ ተዘግቧል፡፡ ባሁኑ ወቅት የሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተለጠጠ እና በኢትዮጵያ ካለው የአገር ውስጥ ግጭት ጋር ተያይዞ እየተነሳ መሆኑ ይታወቃል፡፡

6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን ተወለደች ‎ ‎በቤንች ሸኮ ዞን አንዲት እናት 6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላግላለች። ‎ ‎በዞኑ የአማን ሻሸቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ ሳይ
+1
6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን ተወለደች ‎ ‎በቤንች ሸኮ ዞን አንዲት እናት 6 ነጥብ 4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላግላለች። ‎ ‎በዞኑ የአማን ሻሸቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች በተደረገላት ክትትል ህጻኑን በቀዶ ህክምና መገላገሏን በሆስፒታሉ የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ቹቹ አረጋ ገልጸዋል። ‎ ‎ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ በተመሳሳይ ከ6 ዓመት በፊት 2ኛ ልጇን ስትወልድ 5 ኪ.ግ መሆኑንና በቀዶ ጥገና ህክምና እንደተገላገለች ገልጻለች።

ኤችአይቪ በደማቸው ከሚገኙ ሰዎች መካከል 36 በመቶው የሚሆኑት ሴቶች ናቸው ‎ ‎አሁን ላይ በአገራችን ከፍተኛ የሆነ የኮንዶም ዕጥረት መኖሩም ተነስቷል። ‎ ‎ዕድሜያቸው ከ14-24 የሆኑ ሴቶች በተለ
ኤችአይቪ በደማቸው ከሚገኙ ሰዎች መካከል 36 በመቶው የሚሆኑት ሴቶች ናቸው ‎ ‎አሁን ላይ በአገራችን ከፍተኛ የሆነ የኮንዶም ዕጥረት መኖሩም ተነስቷል። ‎ ‎ዕድሜያቸው ከ14-24 የሆኑ ሴቶች በተለይ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለኤችአይቪ በከፍተኛ ሁኔታ የተጋለጡ መሆናቸው ተገልጿል። ‎ ‎በአገራችን ከግማሽ ሚሊየን በላይ ሰዎች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ይገኛል ተብሏል። ‎ ‎አሁን ላይ 7መቶ ሺህ ሰዎች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ይገኛል የተባለ ሲሆን፥ቁጥሩ ግን በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ሰምተናል። ‎ ‎ይህን የሰማነው የኔትወርክ ኦፍ ኔትወርክስ ኦፍ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ(ኔፕ ፕላስ) ይህን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ ነው። ‎ ‎ኔፕ ፕላስ በኤችአይቪ ህመም ዙሪያ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ ተቋም ሲሆን፥ ምስረታው ወደ 22 ዓመት እየተጠጋው ነው። ‎ ‎በዚህ ኔትወርክ ስር የተቋቋሙ ከ5መቶ በላይ ማህበራትን የያዘ መሆኑ ሲገለፅ፥ በዋናነት አሁን ላይ በንቃት የሚንቀሳቀሱት እና የግሎባል ፈንድ ተጠቃሚ ማህበራት ቁጥር 1መቶ29 ነው። ‎ ‎የኔትወርክ ኦፍ ኔትወርክስ ኦፍ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭስ ኢን ኢትዮጵያ(ኔፕ ፕላስ) ዋና ዳይሬክተር አቶ ካሳሁን ታደሰ፥ በሚቀጥለው ወር 21ኛ ጠቅላላ ጉባዔ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል። ‎ ‎ይህ ጉባዔ እየተዘነጋ ስላለው ነገርግን ዛሬም የብዙዎችን ህይወት እየቀጠፈ ስላለው የኤችአይቪ ህመም ሰፊ ግንዛቤ የሚሰጥበት ነው። ‎ ‎ድርጅቱ ለሁለት ጊዜ ያህል "Stigma index research" ማሰራቱን ገልጾ፥ ሶስተኛ ዙር ጥናት እያካሄደ መሆኑን አስታውቋል። ‎ ‎በጉባኤው ላይ የጤና ሚኒስቴር ሀላፊዎች ፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ ከኔፕ ፕላስ ማህበራት የተወከሉ በአጠቃላይ 1መቶ20 እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ‎ ‎

በሀዋሳ ከተማ በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ  👉አደጋው በ1ሰው ላይ ከባድ እና በ8 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት ኡድርሷል በሀዋሳ ከተማ ትናንት ምሽት በተከሰተው ያልተለመደ ኃይለኛ ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወቱ ማለፉን የከተማዋ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።በአደጋው አንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ8 ሰዎች ደግሞ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል። የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በአደጋው በርካታ ቤቶች ጣሪያዎች በኃይለኛው ንፋስ ተነስተው በመውደቃቸው በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።በተጨማሪም የኮንክሪት የኤሌክትሪክና የቴሌ ፖሎች በመውደቃቸው በከተማዋ በባህል አዳራሽ ምሥራቅ እና መሀል ክፍለ ከተማዎች አካባቢ የኃይል መቋረጥ መከሰቱን ገልጸዋል። በአደጋው ሁለት መኪኖችና አንድ ባጃጅ ላይ የዛፍ ቅርንጫፎች በመውደቃቸው የመስታወት መሰበር ጉዳት ቢደርስም ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ተጠቁሟል። በባጃጁ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ከአደጋው በፊት ወጥተው በመጠለላቸው ከጉዳት መትረፋቸው ተገልጿል።በከተማዋ የተሰሩት የኮሪደር ልማት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ለአቶ  ወንድሙ ብስራት ሬዲዮ ጥያቄ ያነሳ ሲሆን አዳዲስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች እና ቦዮች ወይም ካናሎች ጎርፍ በቀላሉ እንዲፈስ ስለረዱ ከጎርፍ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀናንሰውታል በኮሪደር ልማቱ ላይ የደረሰ የጎርፍ ጉዳት የለም ሲሉ ተናግረዋል። የከተማ አስተዳደሩና የተለያዩ አካላት በማድረግ ባሉት የመስክ ምልከታ መሠረት አስቸኳይ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ሥራዎች እየተጀመሩ መሆኑ ተገልጿል።አደጋው ለ8 ደቂቃ ያህል አጭር ጊዜ ቢቆይም የንፋሱና የበረዶው መጠን ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል። ህብረተሰቡም የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

በመንግሥት በተገነቡ መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ግብር ሊከፍሉ ነዉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚጣል ሲሆን፥ተሽከርካሪዎቹ በ
በመንግሥት በተገነቡ መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ግብር ሊከፍሉ ነዉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚጣል ሲሆን፥ተሽከርካሪዎቹ በመንግስት በተገነቡ መንገዶች ላይ ስለሚንቀሳቀሱ በየዓመቱ የሚከፈል ይሆናል ብለዋል። ይህም ከመደበኛው የተሽከርካሪ ዓመታዊ ምርመራ ወይም ቦሎ ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችል ግዴታ ነው። የምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ እንደገለፁት፥ግብር አጣጣሉም እንደ ተሽከርካሪዎቹ ዓይነትና እንደሚያመነጩት ጭስ (ካርቦን) ሊለያይ እንደሚችል ተናግረዋል። ይህ ማለት ብዙ ጭስ የሚለቁ አሮጌ ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ አዳዲሶች ደግሞ ዝቅተኛ እንዲከፍሉ ሊደረግ ይችላል ተብሏል። ይህ አሰራር በሌሎች አገራት ለምሳሌ በኬንያ፣ በሩዋንዳና በአውሮፓ አገራት የተለመደ ሲሆን፥መንግስት ለመንገድ ጥገና የሚውል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ያስችለዋል። ግብሩ በከተሞችና በክልሎች የሚሰበሰብ በመሆኑ የአካባቢ መስተዳድሮች የራሳቸውን የልማት በጀት እንዲያሳድጉ ትልቅ ዕድል ስለሚፈጥርላቸው በፌዴራል መንግስት ላይ ያለውን የገንዘብ ጫና ይቀንሳል። ይህ የታክስ ፕሮፖዛል በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተዘጋጅቶ  ለምክር ቤቱ ለማቅረብ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ አቶ ዋሲሁን አክለዉም ዝርዝር ደንቦችና መመሪያዎች ወጥተውለት ወደ ተግባር እንደሚገባና የኢኮኖሚው የገቢ ምንጭ እንደሚሆን እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። ከዚህ ግብር የሚገኘው ገቢ ከአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት 0.2 በመቶ ድርሻ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል።

📱 አንድን አይፎን 17 ፕሮ ገዝቶ ለመያዝ በስዊዘርላንድ 3 የሥራ ቀናት ብቻ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ አዲሱ አይፎን 17 ፕሮ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ የሚሸጥበት የገንዘብ መጠን በየትኛውም የዓለማች
📱 አንድን አይፎን 17 ፕሮ ገዝቶ ለመያዝ በስዊዘርላንድ 3 የሥራ ቀናት ብቻ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ   አዲሱ አይፎን 17 ፕሮ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ የሚሸጥበት የገንዘብ መጠን በየትኛውም የዓለማችን ክፍል ተመሳሳይ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን አንድ ግለሰብ ይህንኑ ስልክ ገዝቶ ለመያዝ የሚያወጣው የሥራ ጊዜና ድካም ግን እጅግ የተራራቁ የኢኮኖሚ እውነታዎችን ያንፀባርቃል ተብሏል።   ይህን የገቢና የኢኮኖሚ ልዩነት በግልጽ በሚያሳየው መረጃ መሠረት፣ በስዊዘርላንድ የሚኖር አንድ ሠራተኛ አዲሱን አይፎን 17 ፕሮ ለመግዛት 3 የሥራ ቀናት ብቻ የሚያስፈልጉት ሲሆን፣ በፊሊፒንስ 101 የሥራ ቀናት፣ በሕንድ 160 የሥራ ቀናት፣ እንዲሁም በመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ደግሞ 540 የሥራ ቀናት ሙሉ መሥራት ይጠይቃል ነው የተባለው።   አንድ አይነት ቴክኖሎጂ እና ተመሳሳይ የገበያ ዋጋ፤ ነገር ግን እጅግ የተራራቁ የሰዎች የኑሮ እውነታዎች! ይህ ንጽጽር አይፎን በዓለማችን ላይ ያለውን የገቢና የኢኮኖሚ እኩልነት ማጣትን የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ መሆኑን እና አንድ ሰው የተወለደበት ወይም የሚኖርበት ሀገር የሚገዛቸውን ዕቃዎች የመወሰን አቅሙ ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ በተግባር ያረጋገጠ መሆኑ ተመላክቷል፡፡  

በግብፅ ወደብ ላይ የአሜሪካ ንብረት በሆነ የጋዝ ጫኝ መርከብ ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጸመ‼️ በግብፅ የሜዲተራኒያን ወደብ በሆነው ዳሚየታ በሚገኝ የአሜሪካ ንብረት በሆነ ፈሳሽ ጋዝ የሚቀይርና የሚያከማ
በግብፅ ወደብ ላይ የአሜሪካ ንብረት በሆነ የጋዝ ጫኝ መርከብ ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጸመ‼️ በግብፅ የሜዲተራኒያን ወደብ በሆነው ዳሚየታ በሚገኝ የአሜሪካ ንብረት በሆነ ፈሳሽ ጋዝ የሚቀይርና የሚያከማች መርከብ ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የእሳት መከሰቱንና በኋላም እሳቱ በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሌላ መርከብ መሸጋገሩን ሮይተርስ ዘግቧል። የብሪታኒያው የባህር ላይ ደህንነት ተቋም አምብሬይ የመጀመሪያ ደረጃ ምዘና እና የደህንነትና የንግድ መረጃዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ 'ኤነርጎስ ዊንተር' (Energos Winter) የተባለችው መርከብ የቀኝ ጎኗ በድሮን ጥቃቱ ተመቷል።  በመቀጠልም እሳቱ በወደቡ ላይ ወደነበረችው 'ጋስሎግ ሳሌም' (Gaslog Salem) ወደተባለች ሌላ የጋዝ መርከብ ተዛምቷል። በግምት 138,250 ኩቢክ ሜትር የማከማቸት አቅም ያላት 'ኤነርጎስ ዊንተር'፣ መቀመጫው አሜሪካ ለሆነው 'ኤነርጎስ ኢንፍራስትራክቸር' የተባለ ኩባንያ ንብረት ስትሆን፤ የቴክኒክ፣ የደህንነት እና የንግድ እንቅስቃሴዎቿ የሚመሩት ደግሞ በ'ቪልሄልምሰን ሺፕ ማኔጅመንት' ነው።

#TECNO_SPARK_50 አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 አብረዎት ለረጅም ጊዜ እንዲዘልቅ ከመሰራቱ ባሻገር የIP64 ሬቲንግ ያለው ውሀ እና አቧራ እንዳያበላሸው ተደረጎ መሰራቱ እና ማረጋገጫ ማግኘቱ በየ
#TECNO_SPARK_50 አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 አብረዎት ለረጅም ጊዜ እንዲዘልቅ ከመሰራቱ ባሻገር የIP64 ሬቲንግ ያለው  ውሀ እና አቧራ እንዳያበላሸው ተደረጎ መሰራቱ እና ማረጋገጫ ማግኘቱ በየትኛውም ቦታ ያለምንም ስጋት ሊጠቀሙበት የሚችሉት ለርሶ የተሰራ ስልክ ነው፡፡ አዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 50 ይገባዎታል!! #Spark50 #Spark50Series #TECNOAI #TECNOET @tecno_et

የ«ሁሉ ስፖርት» የፈቃድ ስረዛ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሻረ፤ አገልግሎቱ ግን አሁንም ታግዷል ​የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና የገቢዎች ሚኒስቴር በ«ሁሉ ስፖርት» ላይ
የ«ሁሉ ስፖርት» የፈቃድ ስረዛ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሻረ፤ አገልግሎቱ ግን አሁንም ታግዷል ​የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና የገቢዎች ሚኒስቴር በ«ሁሉ ስፖርት» ላይ አስተላልፈውት የነበረውን የንግድ ፈቃድ ስረዛ ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሻረ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው ተቋማቱ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት ሕግን ሳይከተሉ እና የተቋሙን የመሰማት መብት ጥሰው ፈቃድ መሰረዛቸውን በመግለፅ ነው። ​መንግሥት ድርጅቶቹ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ሰውረዋል ቢልም፣ ፍርድ ቤቱ ይህ በወንጀል ሕግ የሚታይ እንጂ በደፈናው ለአስተዳደራዊ ፈቃድ ስረዛ ምክንያት ሊሆን አይችልም ብሏል። ​ሆኖም የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በውሳኔው ላይ ይግባኝ ማቅረቡን ተከትሎ፣ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አፈጻጸም ከሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ15 ቀናት እንዲታገድ ተደርጓል። በመሆኑም ጉዳዩ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ «ሁሉ ስፖርት» ወደ ሥራ አይመለስም። ​ይህ በእንዲህ እንዳለ የሎተሪ አገልግሎቱ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ምንም ዓይነት የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ድርጅት እንደሌለ አስታውቋል።

+6
ሐዋሳ በከባድ ዝናብ ተመታች‼️ 👉ጎርፍና ኃይለኛ ንፋስ ከዝናብ ጋር በቀጣይ ቀናቶችም ሊቀጥሉ ይችላሉ። ​አሁን ባለው የክረምት ወቅት ሀዋሳን ጨምሮ በዙሪያዋ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ እየጣለ ይገኛል። የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ባለስልጣን በሰጠው መረጃ መሠረትም የዝናቡ መጠን በቀጣዮቹ ቀናት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል። ​በከተማዋ እየጣለ ባለው ከባድ ዝናብ፣ በረዶና ኃይለኛ ንፋስ በአንዳንድ አካባቢዎች ዛፎችንና የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን በመጣሉ በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት አስከትሏል። በተጨማሪም በመሠረተ ልማት ላይ በደረሰ ውድመት ምክንያት በአንዳንድ የከተማዋ ክፍሎች የመብራት አገልግሎት ተቋርጧል። ​የከተማ አስተዳደሩ በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልፆ፤ በተጎዱ አካባቢዎች ፈጥኖ በመድረስ ተጎጂዎችን ወደ ሕክምና የማድረስና በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት በመለየት ተገቢውን ድጋፍ የማድረግ ሥራዎችን አስጀምሯል። ​በቀጣይም የክረምቱ ወቅት እስኪያልቅ ድረስ መሰል የተፈጥሮ አደጋዎች ሊያጋጥሙ ስለሚችሉ፣ ጉዳቱን ለመቀነስና ለመከላከል የሚያስችሉ የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ ይገኛሉ። ​በመሆኑም በቀጣዮቹ ቀናት ኃይለኛ ንፋስ የታጀበ ዝናብና የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስተዳደሩ ያሳስባል። ​በተለይም ዛፎች፣ ያረጁ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና አጥሮች ሊወድቁ ስለሚችሉ፣ በዝናብ ወቅት ከእነዚህ አካባቢዎች በመራቅ ራሳችሁንና ቤተሰቦቻችሁን እንድትጠብቁ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል። ሐዋሳ ከተማ ኮሙኒኬሽን

ግብጾች የአባይን ውሃ ስለሚጠቀሙ ለኢትዮጵያ ሊከፍሉን ይገባል ዶክተር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖ
ግብጾች የአባይን ውሃ ስለሚጠቀሙ ለኢትዮጵያ ሊከፍሉን ይገባል ዶክተር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ፣ ግብፅ የአባይን ውኃ በነፃ እየተጠቀመች አገሯን እያለማች በመሆኗ ለኢትዮጵያ ተገቢውን ክፍያ ልትፈጽም እንደሚገባ ገለጹ። ሚኒስትሩ በቆይታቸው እንደጠቆሙት፤ ኢትዮጵያ የጎርፍ አደጋ በታችኞቹ የተፋሰሱ አገራት—በተለይም በግብፅ ላይ እንዳይደርስ ከፍተኛ የክትትልና የእንክብካቤ ሥራ እያከናወነች ትገኛለች። ሆኖም አገራቱ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሀብት ያለምንም ክፍያ በመጠቀም አገራቸውን እያለሙ በመሆናቸው፣ ለሚጠቀሙበት ውኃ ለኢትዮጵያ ክፍያ ሊፈጽሙ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። @Seledadotio @Seledadotio

ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራ
ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል። "ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር  ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል። በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ። ​ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል። @Seledadotio @Seledadotio

በርካታ አካባቢዎች መብራት ይቋረጣል‼️ የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል። ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00 • ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው። • ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው። • 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው። • ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው። ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00 • አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው። ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30 • ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው። • አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው። ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00 • መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው። ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00 • ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው። • ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው። በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።

ደቡብ ኮሪያ ዜጎቿ ትዳር እንዲመሠርቱእና ልጅ እንዲወልዱ ገንዘብ እየከፈለች እንደሆነ ተነገረ። በዓለማችን ዝቅተኛው የወሊድ መጠን የሚገኝባት ደቡብ ኮሪያ፣ የህዝብ ቁጥሯ እንዳይቀንስና የህጻናት ቁጥር
ደቡብ ኮሪያ ዜጎቿ ትዳር እንዲመሠርቱእና ልጅ እንዲወልዱ ገንዘብ እየከፈለች እንደሆነ ተነገረ። በዓለማችን ዝቅተኛው የወሊድ መጠን የሚገኝባት ደቡብ ኮሪያ፣ የህዝብ ቁጥሯ እንዳይቀንስና የህጻናት ቁጥር እንዲጨምር ትልቅ አዲስ ዘመቻ ጀምራለች! መንግሥት ወጣቶች እንዲጋቡና ልጅ እንዲወልዱ የሚያበረታቱ የገንዘብ፣ የቤት እና የህጻናት ማደጊያ ድጋፍ ፕሮግራሞችን ይፋ አድርጓል። ወዲያው ጋብቻ የሚፈፅሙ አዲስ ባለትዳሮች 1ኛ የመኖሪያ ቤት ድጋፍ፣ 2ኛ የህጻናት ማደጊያ አበል፣ 3ኛ የወሊድ ክፍያ እና የአካባቢ አስተዳደሮች የሚሰጧቸውን ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች በአንድ ላይ ሲደመሩ አጠቃላይ የሚያገኙት ድጋፍ ከፍተኛ መጠን ሊደርስ ይችላል። ኢትዮጵያ ውስጥ ተመሳሳይ የጋብቻና የወሊድ የገንዘብ ማበረታቻ ቢጀመር... እርስዎ ያገባሉ?

የሰው ልጅ ከ5 እስከ 7 ዓመታት ውስጥ ማርስ ላይ ሊያርፍ እንደሚችል ኢሎን ማስክ ገለጹ ​ቢሊየነሩ ኢሎን ማስክ የሰው ልጅ በሚቀጥሉት ከ5 እስከ 7 ዓመታት ውስጥ በማርስ ላይ እግሩን ሊያኖረው እንደ
የሰው ልጅ ከ5 እስከ 7 ዓመታት ውስጥ ማርስ ላይ ሊያርፍ እንደሚችል ኢሎን ማስክ ገለጹ ​ቢሊየነሩ ኢሎን ማስክ የሰው ልጅ በሚቀጥሉት ከ5 እስከ 7 ዓመታት ውስጥ በማርስ ላይ እግሩን ሊያኖረው እንደሚችል አስታወቁ። ​ማስክ ይህንን ያሉት አራት አባላት ያሉት የጠፈር ተመራማሪዎች ቡድን ወደ ማርስ ለመላክ ከ10 እስከ 15 ዓመታት ሊወስድ እንደሚችል የተናገሩትን የናሳ (NASA) አስተዳዳሪ ጃሬድ አይዛክማን አስተያየት በመቃወም እና ምላሽ በመስጠት ነው። ​እንደ ማስክ ማብራሪያ ከሆነ፣ የሰው ልጅን ማርስ ላይ የሚያሳርፈው መንኮራኩር ከተገመተው ጊዜ ይበልጥ ቀደም ብሎ ዝግጁ ሊሆን ይችላል። የስፔስ ኤክስ  ባለቤት የሆኑት ማስክ በማርስ ላይ የሰው ልጅ መኖሪያ ለመገንባት የሚያስችሉ ዘመናዊ የጠፈር መንኮራኩሮችን የማልማት ሥራቸውን አፋጥነው እያከናወኑ ይገኛሉ። ​ይህ አዲስ የጊዜ ሰሌዳ በጠፈር ምርምር ዘርፍ ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ ሲሆን፣ ወደ ማርስ የሚደረገው ታሪካዊ ጉዞ ከተጠበቀው በላይ በፍጥነት ሊሳካ እንደሚችል ያመላክታል።

የአሜሪካ ኩባንያ አውሮፕላኖች ለሱዳኑ 'አር ኤስ ኤፍ' የጦር መሣሪያ ሲያቀብሉ መያዛቸው ተገለጸ፡፡ የተመድ ባለሙያዎች በሚስጥር ባዘጋጁት ረቂቅ ሪፖርት፣ ከአሜሪካ ወታደራዊ ድርጅት ጋር ግንኙነት ያላቸው አውሮፕላኖች ለሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) ድሮኖች እና የጦር መሣሪያዎችን ሲያጓጉዙ ተደርሶበታል። የቀድሞ የአሜሪካ ልዩ ኃይል አባል ከሆኑት ስቲቨን ሻውሊስ ጋር የተያያዙት እነዚህ አውሮፕላኖች ከቻድ ተነስተው በሱዳን ኒያላ ከተማ በምሽት ሚስጥራዊ በረራዎችን ሲያደርጉ እንደነበር ሪፖርቱ አጋልጧል። በጎርጎርሳዊው 2023 ከተቀሰቀሰ ወዲህ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን ከቀዬአቸው ያፈናቀለው የሱዳን ጦርነት አሁን ደግሞ የውጭ አገር ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ማዕከል ሆኗል። የፊታችን መስከረም ወር በይፋ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ሙሉ ሪፖርት በዳርፉር የተፈጸሙ ተጨማሪ አሰቃቂ ድርጊቶችን እና የጦር መሣሪያ አቅራቢዎችን በይፋ ያሳያል ተብሎ ይጠበቃል። @Seledadotio @Seledadotio

#TECNO_SPARK_50 እጅግ ጫጫታ የሆነ ቦታ ሆነው በጣም የሚፈልጉት ስልክ ተደውሎ የት ሄጄ ላውራ የሚል ስጋት ገብቶት ያውቃል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ጋር እንደዚህ እይነት ስጋት ታሪክ ነ
#TECNO_SPARK_50 እጅግ ጫጫታ የሆነ ቦታ ሆነው በጣም የሚፈልጉት ስልክ ተደውሎ የት ሄጄ ላውራ የሚል ስጋት ገብቶት ያውቃል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ጋር እንደዚህ እይነት ስጋት ታሪክ ነው፡፡ ለምን ካላችሁ የፈለገ ጫጫታ ቦታ ቢሆኑ እንኳን ባዶ ክፍል ውስጥ ሆነው እያወሩ እስኪመስል ድረስ ፅጥ የሚያደርግ የNoise Cancellation ቴክኖሎጂ ስላለው የፈለጉትን ስልክ በፈለጉት ቦታ ያለምንም ድምፅ ብክለት ማውራት ያስችሎታል፡፡ ቴክኖ ስፓርክ 50 በልዩነት የሚመርጡት ስልክ!! #Spark50 #Spark50Series #TECNOAI #TECNOET @tecno_et

💥 ሰበር ዜና፡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ «የማይቀመስ ከባድ አደብ የማስተማሪያ ጥቃት እንሰነዝራለን» ሲሉ ዛቱ! የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ
💥 ሰበር ዜና፡ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ «የማይቀመስ ከባድ አደብ የማስተማሪያ ጥቃት እንሰነዝራለን» ሲሉ ዛቱ! የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ-መጠይቅ፣ በዮርዳኖስ በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ የተቃጣውን ያልተጠበቀ የኢራን የባሊስቲክ ሚሳይል ጥቃት በመኮነን አሜሪካ እጅግ በሐይል የተሞላ ምላሽ እንደምትሰጥና ኢራንን «አደብ እንደሚያስተምሯት» አስታወቁ። ፕሬዚዳንቱ በሰጡት ጠንካራ መግለጫ፣ የአሜሪካ አየር መከላከያ ኃይሎች የተኮሱትን ሚሳይሎች ለማከሸፍ የነበራቸው ጊዜ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ እንደነበረ ገልጸው፣ የጦር ኃይሎቹ በቅጽበት ባደረጉት ቅንጅት ሚሳይሎቹን ሙሉ በሙሉ አየር ላይ ማክሸፍ መቻላቸውን አደንቀዋል። በተጨማሪም ትራምፕ ሌሊቱን ከአሜሪካ እና ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር በመቀናጀት በኢራቅ በሚገኙ የኢራን ድጋፍ በሚደረግላቸው የሺዓ ታጣቂዎች ላይ የተፈጸመው የአየር ጥቃት ከኢራቅ መንግሥት ጋር በሙሉ ስምምነት የተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰራተኞቹን የቤት ችግር ለመፍታት በጀመረው ስራ በጥር ወር 2 ሺ 500 የሚሆኑ ቤቶች ግንባታ ይጠናቀቃል አለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰራተኞቹን የቤት ችግር ለመፍታት በጀመረው ስራ በጥር ወር 2 ሺ 500 የሚሆኑ ቤቶች ግንባታ ይጠናቀቃል አለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ 9 አዳዲስ የጉዞ አውሮፕላኖች እና ስምንት ዲኤ 40 ኤንጂ የተሰኙ ለፓይለቶች ማሰልጠኛ የሚሆኑ 8 አውሮፕላኖች መገዛታቸውን ገልጸዋል፡፡ ‎በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ተርሚናሎችን የማደስና እንደ አዲስ የመስራት ተግባራት ተከናውነዋል ነው ያሉት፡፡‎የሰራተኞችን የቤት ችግር ለማቃለል በተጀመረው ስራ 5 ሺህ ለሚሆኑ ሰራተኞች የቤት ግንባታ መጀመሩን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 500 የሚሆኑት ቤቶች እስከ 2019 ዓ.ም ጥር ወር ድረስ እንደሚጠናቀቁ አብራርተዋል፡፡ ቀሪዎቹ ቤቶች ደግሞ በ2019 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃሉ ነው ያሉት፡፡የአየር መንገዱ የአቪየሽን ዩኒቨርሲቲ ከተቀበላቸው 2 ሺህ 183 ተማሪዎች ውስጥ 1 ሺህ 713 ተማሪዎችን ማስመረቅ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ አየር መንገዱ ለበጎ አድራጎት ስራዎች ከ5 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio

🚨የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ጉዳዮች፣ የአህጉራችን ኢኮኖሚና የዓለም ታላላቅ ሁነቶች እንዴት እርስ በርሳቸው ይያያዛሉ? 📌 እኛ የምዕራባውያን ሚዲያዎች የሚያልፏቸውን ታሪኮች፣ አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ባገ
🚨የሀገር ውስጥ ወቅታዊ ጉዳዮች፣ የአህጉራችን ኢኮኖሚና የዓለም ታላላቅ ሁነቶች እንዴት እርስ በርሳቸው ይያያዛሉ? 📌 እኛ የምዕራባውያን ሚዲያዎች የሚያልፏቸውን ታሪኮች፣ አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ባገናዘበ አዲስ እይታ እናቀርባለን። 📌እናንተ፡ የተወሳሰቡ ዜናዎችን ፈጣን፣ ግልጽ እና ሚዛናዊ በሆነ ትንተና በደቂቃዎች ውስጥ ታገኛላቹ ጊዜዎን ቆጥበው የአስተሳሰብ አድማስዎን የሚያስፉ መረጃዎችን ቀድመው ለማግኘት አሁኑኑ ይቀላቀሉን 👇 🔗 https://t.me/+EUyJimhjCeY2ZTVi 📣 @sputnik_ethiopia