fa
Feedback
ቅ/ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ አርማ

ቅ/ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ አርማ

رفتن به کانال در Telegram

በ1928 የተመሠረተ ፩ ክለብ ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️ @SAINTGEORGEFC የመወያያ ግሩፑኑን ለመቀላቀል @talksanjaw ለአስተያየት እና ለጥያቄ ⬇️ @SAINTGEORGEFCV_bot

نمایش بیشتر
8 785
مشترکین
-1024 ساعت
-417 روز
-9630 روز
آرشیو پست ها
ዳፍ ትራክ ላይ እንዲሁም በተለያዩ የሀገራችን ክልሎች ከልጅነቱ ጀምሮ እየተጓዘ ክለቡን የሚደግፈው የሳንጃው የልብ ወዳጅ ማይኮ ማረፉን ሰማን 😭 እጅግ ልባችን ተሰብሯል የወንድማችንን ነፍስ ፈጣሪ በ
ዳፍ ትራክ ላይ እንዲሁም በተለያዩ የሀገራችን ክልሎች ከልጅነቱ ጀምሮ እየተጓዘ ክለቡን የሚደግፈው የሳንጃው የልብ ወዳጅ ማይኮ ማረፉን ሰማን 😭 እጅግ ልባችን ተሰብሯል የወንድማችንን ነፍስ ፈጣሪ በቅዱስ ስፍራው ያሳርፋት ለመላው ቤተሰቡ ለወዳጅ ጓደኞቹ በሙሉ መፅናናትን ከልብ እንመኛለን 🙏

#የጊዮርጊስትንሳዔ፦ ከተቋም መደላደል እስከ ሀገራዊ ተምሳሌትነት.. ኢትዮጵያዊነትን በስፖርቱ መድረክ ቀድሞ በመሰለፍ፣ በክብርና በኩራት ለዘመናት የዘለቀው አንጋፋው ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ዛሬ ላይ የታሪኩን አዲስ ምዕራፍ እየፃፈ ይገኛል። ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊ ክለብ እንደ ስሙ ግርማና እንደ ስፋቱ ልክ፣ ለሞዴልነት የሚበቃ ቋሚ ንብረትና መሰረተ ልማት ሳይኖረው መቆየቱ በደጋፊውም ሆነ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ የቆየ ቁጭት ነበር። ዛሬ ግን ያ ቁጭት ወደ ተግባር፣ ያ ምኞትም ወደ እውንነት የመቀየር አዲስ የለውጥ ንፋስ እየነፈሰበት ይገኛል። የስፖርቱ ዓለም #የጋራዕብደት እና #የፈውስፍለጋ.. በሀገራችን የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ስህተት #ክለብ የሚለውን ትርጉም በውጤትና በዋንጫ ብቻ መገደቡ ነው። እኛ አሰልጣኞች፣ አመራሮችና ኤጀንቶች በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠር መዋዕለ ንዋይ ለተጫዋቾች ግዢ ስናፈስ፣ ለነገው ተተኪ ትውልድ የሚሆን አካዳሚ፣ ዘመናዊ የስልጠና ማዕከልና ፕሮፌሽናል አደረጃጀት መዘንጋቱ ለዓመታት የዘለቀ #የጋራዕብደት ሆኖ እየቀጠለ ነዉ። የዚህ ድምር ውጤት ደግሞ በሊጉ ዋንጫ ብናነሳም፣ በአህጉራዊ መድረክ ግን ከጎረቤቶቻችን ከግብፅ፣ ከሞሮኮና ከደቡብ አፍሪካ ክለቦች ጋር ለመፎካከር አቅም አጥተን እንድንቀር አድርጎናል። ይህን የቆየ ስንክሳር ሰብሮ ለመውጣት ግን ራዕይ ያለውና ለነገው የሚጨነቅ ቆራጥ መሪ ማግኘት የግድ ነበር። የክቡር አቶ #ጀማልአህመድ/የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ/ አመራርና አዲሱ ራዕይ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከገጠመው የፋይናንስ ቀውስ ከማሻገር ባለፈ፣ ስትራቴጂካዊ መንገዶችን በአግባቡ በመንደፍና በመተግበር ወደሚፈለገዉ ከፍታ ለማሻገር የያዙት ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው። ከብዙ በጥቂቱም #ክለብንበመሰረትመገንባት የሚለው መርኋቸው የክለቡን የነገ ተስፋ በእጅጉ የሚያለመልም ነው። ይህ አዲስ አመራርም በሁለት አበይት ተግባራት ላይ ትኩረት አድርጎ መንቀሳቀሱ ለለውጡ ማሳያ እየሆነ ነው፦ ለምሳሌ..1ኛ/ #የአካዳሚውህያውመሆን፦ በደብረዘይት የሚገኘው የክቡር አቶ ይድነቃቸው መታሰቢያ ስፖርት አካዳሚ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገባ እየተደረገ ያለው ርብርብ፣ ክለቡ የራሱን የችግኝ ጣቢያ በማዘጋጀት ለወደፊት ተወዳዳሪነቱ ዋስትና እንዲኖረው ያደርጋል። 2ኛ/#የመሰረተልማት ጥማት፦ ክለቡ በአዲስ አበባ ለስታዲየም ግንባታ ተሰጥቶ የነበረውና በሂደት ተረስተው የነበሩ መሬቶችን በማስመለስ፣ ወደ ግንባታ ለመግባት የሚደረገው ጥረት የክለቡን የሀብት ባለቤትነት የሚያረጋግጥ ትልቅ እርምጃ ነው። ይህ ጥረት ለጊዮርጊስ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችን እግር ኳስም የሞዴልነት ሚና ይኖረዋል። #መከራን ወደ #መልካም አጋጣሚ መለወጥ:- ምንም እንኳን ክለቡ የፊፋ የአንድ ዙር የዝውውር ዕገዳ ቢኖርበትም፣ ይህን ፈተና በጥበብና በማስተዋል ወደ ዕድል እየቀየረው ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ክለቡ ትኩረቱን እያበቡ ባሉ የራሱን #ወጣትተሰጥኦዎች ላይ በማድረግ፣ ጥቂት ልምድ ያላቸውን ወጣቶች በማከል የጊዮርጊስን የታሪክ ልክ የሚመጥን ጠንካራ ስብስብ እየገነባ ይገኛል። ይህ ሂደት በገንዘብ ኃይል ሳይሆን በእውቀትና በራዕይ የሚመራ በመሆኑ ዘላቂነቱ የታመነ እንደሚሆን ጥርጥር የለዉም። #ማጠቃለያ:- ዛሬ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከገባበት የፋይናንስና የአደረጃጀት ቀውስ ወጥቶ፣ በተረጋጋና በሰከነ አመራር ወደ ቀደመ ግርማው እንደሚመለስ እሙን ነው። ይህ ጉዞ ግን የአመራሩ ብቻ ሳይሆን የመላው ደጋፊ እገዛና ትዕግስት ይጠይቃል። በጥበብና በራዕይ የሚመራውን ክለባችንን ያለጥርጥር መደገፍና ወደ ከፍታው ማሻገር የሁሉም ታሪካዊ ኃላፊነት ነው። #የጊዮርጊስትንሳዔ ጀምሯል፤ ይህ ጅማሮ ደግሞ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ያለ ጥርጥር አዲስ ብርሃን ይሆናል። አሰልጣኝ ስዩም

የታላቁ ቅዱስ ጊዮርጊስ የበላይ ጠባቂ ሼህ ማህመድ ሁሴን አሊ አላሙዲን ዛሬ ልደታቸው ነው ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን 🎂 መልካም ልደት 🎂 ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ
የታላቁ ቅዱስ ጊዮርጊስ የበላይ ጠባቂ ሼህ ማህመድ ሁሴን አሊ አላሙዲን ዛሬ ልደታቸው ነው ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን 🎂 መልካም ልደት 🎂 ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

ክብሩን አባቴ የድንግል ልጅ እየሱስ ክርስቶስ ይውሰድ 🙏🙏 👉 ባለፈው ሁለት አመታት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የነበረኝን የሁለት ዓመታት ግዜ ጨርሼ ለሌላ ኃላፉነት እራሴን አዘጋጅቼያለው በእነዚህ ሁ
ክብሩን አባቴ የድንግል ልጅ እየሱስ ክርስቶስ ይውሰድ 🙏🙏 👉 ባለፈው ሁለት አመታት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የነበረኝን የሁለት ዓመታት ግዜ ጨርሼ ለሌላ ኃላፉነት እራሴን አዘጋጅቼያለው በእነዚህ ሁለት ዓመት በተለይ በዘንድሮ ዓመት ቡድናችን ከደረጃ በታች እንዳይሆን በትጋት ፣ በትግስት አቅማችን የፈቀደውን አድርገን በመጨረሻም ተሳክቶልናል ። በቆይታዬ ግዜ 👉 ውድ ተጨዋቾች : በእያንዳንዱ ጉዞሀችን ውስጥ በከፍታም በዝቅታም ውስጥ ትህዛዜን በፍቅር በእምነት መንፈስ ስለተቀበላችሁኝ ፣ በችግራችንም ግዜ ላሳያችሁት ትጋትና ለሙያ መታመን በመጨረሻ ላጋኘነው ውጤት ትልቅ አስተዋህፆ አድርጓልና ከልብ አመሰግናለው ። 👉 ውድ የአሰልጣኝ ቡድን አባላት : የእናንተ የትብብር መንፈስ የቡድን ፍቅር በቡድኑ ላይ የፈጠረው ተፅህኖ ከፍተኛ ነበር። በእያንዳንዱ ጉዞሀችን ከራስ በላይ ለቡድን የሚለው አስተሳሰብ ለቡድኑ የከፈላችሁት መስዋትነት ከፍተኛ ነበር ክብር ለእናንተ ። 👉 ሁሌም የቡድኑ ቀኝ እጅ የሆናችሁ ደጋፊዎቻችን ስንሸነፍ እያበራታችሁ ስናሸንፍ ደግሞ እየዘመራችሁ በትክክል የቡድን ደጀን ስለነበራችሁ ከአንገቴ ዝቅ ብዬ አመሰግናለው ። 👉 የነበረብንን ችግር ደርሶ መፍትሄ ለሰጠን ለአቶ ጀማል አህመድና ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩብ እና ለቦርድ አባላት ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው ። በመጨረሻም ሁሉንም ማብራራት አይቻልም ወይም ደግሞ ቃላቶች ያንሳሉ ለእኔ ይሄንን ቡድን ማሰልጠን ክብርም ኩራትም ነው ። ክለቡን ለቅቄ የሚሄድበት ግዜ ቢደርስም በእያንዳንዱ ጉዞዬ የነበረኝን ደስታና አክብሮት አይቀንሰውም አመሰግናለው 🙏🙏🙏 አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ

የማራቶን ጀግና አበበ ቢቂላ ❤️✌️ ጀግናው ለውድድር ከመድረሱ በፊት ትሬዲንግ የሚሰራው በእኛ ማልያ ነበረ አበበ ቢቂላ ታማኝ የክለባችን ደጋፊም ነበረ በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በዓለም አትሌቲክስ የ
የማራቶን ጀግና አበበ ቢቂላ ❤️✌️ ጀግናው ለውድድር ከመድረሱ በፊት ትሬዲንግ የሚሰራው በእኛ ማልያ ነበረ አበበ ቢቂላ ታማኝ የክለባችን ደጋፊም ነበረ በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በዓለም አትሌቲክስ የማይረሳ ወርቃማን ታሪክ ፅፏል ቅዱስ ጊዮርጊስ የሀገራችን እግርኳስ አባት ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

ታፌ ለሰሞኑ ወሬ ✋✋ ጉራ ብቻ ብላለች 😂 ቱታው ቪ በልቡ ከአሜሪካ ተመችቶናል ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC
ታፌ ለሰሞኑ ወሬ ✋✋ ጉራ ብቻ ብላለች 😂 ቱታው ቪ በልቡ ከአሜሪካ ተመችቶናል ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

ቃላት ብንደረድር ለአንተ ያለንን ፍቅር አይገልጸውም መቼም የማንረሳው ውለታ አለብን ታላቅ ታሪክ ከልጅነት እስከ እውቀት ለዚህ ክለብ ሰርተሃል ፋሲሌ እንወድሃለን እናከብርሃለን ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️
+3
ቃላት ብንደረድር ለአንተ ያለንን ፍቅር አይገልጸውም መቼም የማንረሳው ውለታ አለብን ታላቅ ታሪክ ከልጅነት እስከ እውቀት ለዚህ ክለብ ሰርተሃል ፋሲሌ እንወድሃለን እናከብርሃለን ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

የሰለጠነ የተጠና የዝውውር አካሄድ በክለባችን አመራሮችና በኮቺንግ ስታፉ እየተደረገ ነው ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም ሌሎች ጋር ያለው እብደት እኛ ጋር የለም የታቀዱት ተጫዋቾች ይመጣሉ ከዛ ውጪ ፈል
የሰለጠነ የተጠና የዝውውር አካሄድ በክለባችን አመራሮችና በኮቺንግ ስታፉ እየተደረገ ነው ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም ሌሎች ጋር ያለው እብደት እኛ ጋር የለም የታቀዱት ተጫዋቾች ይመጣሉ ከዛ ውጪ ፈልገን የምናጣው ምንም ነገር የለም ስለዚህ በሚናፈሰው ወሬ አትሸበሩ ጊዜው ሲደርስ እያንዳንዱ ነገር በክለባችን በኩል ይፋ ይሆናል የሚገራርሙ ስራዎች እየተሰሩ ነው

🏆1995 🏆 በባከነ ሰዓት ያስቆጠርናት ጎል ነች ተጋብዛቹኃል ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

🏆1995 🏆 በባከነ ሰዓት ያስቆጠርናት ጎል ነች ተጋብዛቹኃል ለዚህ ነው 🏆#እንበላዋለን 🏆የምንለው 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን...✌️

‘’ በ2019 የውድድር ዓመት አዲስ አበባ የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይደረግባት ትችላለች! ‘’ ይህንን ያለው የውድድር እና ስነስርዓት ኮሚቴ ነው፡፡ የአዲስ አበባን ነዋሪ ያገለለ ውድድር ላይ ክለቦቻ
‘’ በ2019 የውድድር ዓመት አዲስ አበባ የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይደረግባት ትችላለች! ‘’ ይህንን ያለው የውድድር እና ስነስርዓት ኮሚቴ ነው፡፡ የአዲስ አበባን ነዋሪ ያገለለ ውድድር ላይ ክለቦቻችን በፍጹም መሳተፍ የለባቸውም በአስቸኳይ መፍትሔ ፍጠሩ እኛን ያገለለ ነገሮች ሁሌ ሲወሰኑ ዝም ብላቸሁ ውሳኔው አትቀበሉ የከተማችን አስተዳደር ለእኛም ለከተማዋ ኳስ አፍቃሪ ህብረተሰብ ትኩረት ሊሰጠን ይገባል

#ሐምሌ10/1995... አንበሳው ቅዱስ ጊዮርጊስ የዋንጫው ጌታ ወያላን ያሳፈረ በዘመናት መካከል የማይረሳ ጀግንነት 🏆🏆🏆
+1
#ሐምሌ10/1995... አንበሳው ቅዱስ ጊዮርጊስ የዋንጫው ጌታ ወያላን ያሳፈረ በዘመናት መካከል የማይረሳ ጀግንነት 🏆🏆🏆

My journey at St George has come to an end,I would like to thank the management for giving me an opportunity to represent the
My journey at St George has come to an end,I would like to thank the management for giving me an opportunity to represent the biggest club in Ethiopian football.I would also like to thank the coaching staff for always believing in me even at my lowest point especially Goalkeeper coach Daniel who has been a father figure to me.I would also like to thank my fellow players who have stood with me side by side in the battle field especially when we were at our lowest during the financial crisis at the club,You guys are family 🙌🏾….I would also like to extend my sincere appreciation to the most important people who are the amazing fans at St. George who never gave up on us even when things seemed hopeless,May God bless you and May God bless Saint George…..All the best in the coming season and your future endeavors #SanjieAnibesa🦁 #Teamwaza

እየመጣን ነው 🏆 አንበሳው ሳንጃው ❤🏆❤ ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈
እየመጣን ነው 🏆 አንበሳው ሳንጃው ❤🏆❤ ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

ቅዱስ ጊዮርጊስ ብሩክ እንዳለ እና ተመስገን ብርሃኑን ለማስፈረም ተስማማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ የ2019 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድሮችን በተሻለ ዝግጅትና በጠንካራ ስብስብ ለመሳተፍና ውጤታማ ለመሆን እያከናወነ ባለው የቡድን ግንባታ ሂደት ብሩክ እንዳለ እና ተመስገን ብርሃኑን ለማስፈረም መስማማቱን ሲገልፅ ደስታ ይሰማዋል፡፡ በዛሬው እለት በተደረገው ውይይት ብሩክ እና ተመስገን ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለመጫወት የተስማሙ ሲሆን የህክምና ምርመራ አድርገው በቀጣይ በሚከፈተው የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት በፌዴሬሽን ተገኝተው ፊርማቸውን የሚያኖሩ ይሆናል፡፡ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ድንቅ አቋሙን በማሳየት ከተስፋ ሰጪ ወጣት ተጫዋቾች መካከል ስሙን ያስጠራው ብሩክ እንዳለ ስምምነቱን አስመልክቶ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለመቀላቀል በመስማማቱ ከፍተኛ ደስታ እንደሚሰማው በዚህ መልኩ ገልጿል። "ቅዱስ ጊዮርጊስ ታሪካዊና ትልቅ ክለብ ነው። የዚህ ክለብ አካል መሆን ለእኔ ትልቅ ክብር ነው፤ የተጣለብኝን ኃላፊነት በሙሉ አቅሜ ለመወጣት እሰራለሁ።" ብሏል። በፍጥነቱ፣ በግብ የማግባት ብቃቱና በተፅዕኖ ፈጣሪ አጨዋወቱ የሚታወቀው ተመስገን ብርሃኑም ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለመጫወት በመስማማቱ የተሰማውን ስሜት ሲገልፅ "ቅዱስ ጊዮርጊስን የማውቀው ከድልና ከዋንጫ ጋር ነው። ከአዲሶቹ የቡድን አጋሮቼ ጋር በጋራ በመሆን ክለቡን ወደሚገባው የድል መንገድ ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት አደርጋለሁ።" ብሏል። የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ ፕሬዝዳንት አቶ ነሲቡ ጫኮ በበኩላቸው፤ ክለቡን ወደ ቀደመ ክብሩና ስኬቱ ለመመለስ በሜዳ ላይም ሆነ ከሜዳ ውጪ የሚከናወኑ ስትራቴጂያዊ ስራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥሉ ገልጸው በዛሬው እለት ለክለቡ ለመጫወት የተስማሙት ተጫዋቾች የዚህ ረጅም ጊዜ የቡድን ግንባታ እቅድ አስፈላጊ አካል መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ የቡድን ግንባታውን በማጠናከር በመጪው የውድድር ዘመን ለሁሉም ዋንጫዎች በጠንካራ ፉክክር ለመቅረብ ያለመ ሲሆን በቀጣይም ሌሎች የቡድን ማጠናከሪያ እርምጃዎችን በተከታታይ ያሳውቃል። ክቡራን የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችም ትክክለኛውን የክለባችሁን መረጃ ከክለቡ ኦፊሻል የሶሻል ሚዲያዎች እና ከምንጊዜም ጊዮርጊስ የሬዲዮ ፕሮግራም ብቻ እንድታገኙ እንጠይቃለን፡፡ ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

እንኳን ደህና መጣችሁ
+1
እንኳን ደህና መጣችሁ

2019 ዓ.ም 😁 ሼባዉ ለዋንጫ፣ __ ለሩጫ። ❤✌️❤ ቪ በልብ ❤✌️❤ ❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ ❤️ #ምንጊዜም_ጊዮርጊስ 💛❤️ 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 👉 @SAINTGEORGEFC 👈 ፩ ክለብ  ፩ ቤተሰብ ሁሌም ስለ ሳንጃው እንዘግባለን✌️

አዲስ ሮናልዶ ✌️ በክለባችን ደጋፊዎች ዘንድ ተወዳጅነት ያተረፈው ከተጫዋችነትም በላይ በሜዳም ሆነ ከሜዳ ውጪ የማይረሱ ጊዜያትን በክለባችን ያሳለፈው አዲስ ግደይ ተሞሽሯል መልካም ጋብቻ ❤️
+1
አዲስ ሮናልዶ ✌️ በክለባችን ደጋፊዎች ዘንድ ተወዳጅነት ያተረፈው ከተጫዋችነትም በላይ በሜዳም ሆነ ከሜዳ ውጪ የማይረሱ ጊዜያትን በክለባችን ያሳለፈው አዲስ ግደይ ተሞሽሯል መልካም ጋብቻ ❤️

"ትኩረታችንን ራሳችን ላይ እናድርግ" ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች አንድ መልዕክት እናስተላልፋለን ይህ መልዕክት የክረምቱ መርህ ሆኖ ትልቁና ብቸኛው የስኬት መንገድ እንዲሆን እናድርገው። ይህንን መርህ
"ትኩረታችንን ራሳችን ላይ እናድርግ" ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች አንድ መልዕክት እናስተላልፋለን ይህ መልዕክት የክረምቱ መርህ ሆኖ ትልቁና ብቸኛው የስኬት መንገድ እንዲሆን እናድርገው። ይህንን መርህ በተግባር መከተል ማለት ምን ማለት ነው? • ከማንም ጋር አለመነካካት፦ የሌሎችን ቡድኖች አካሄድ፣ ወሬ ወይም ትንኮሳ ወደ ጎን ትቶ ሙሉ ትኩረትን በቢጫና ቀዩ ቤተሰብ እና በምንወደው ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለባችን ላይ ብቻ ማድረግን ያካትታል። • የውስጥ አንድነታችንን እናጠናክር ፦ በደጋፊው፣ በቦርዱ እና በተጫዋቾች መካከል ያለውን ግንኙነት በማጥበቅ ቡድኑን የሚጠብቁትን ፈተናዎች በጋራ መጋፈጥ ጀምረናል ይህንን ደግሞ ይበልጥ ማጠናከር ይኖርብናል ስንል ትኩረታችንን ራሳችን ላይ እናድርግ እንላለን። • ለ2019 ዝግጅት፦ አዲስ የውድድር ዘመን ሲመጣ ካለፈው ስህተት ተምሮ፣ ቡድኑን በሃሳብ፣ በሞራል እና በፋይናንስ ደግፎ ለሻምፒዮናነት ማዘጋጀት የሚል መነሻ ይኖረዋል። ይህ ደሞ የብስለት እና የታላቅነት መገለጫ ነው። ✌️ የ2019 የሻምፒዮናነት ጉዞ በዚሁ ፅኑ መንፈስ ይጀምራልና! 👉 "ትኩረታችንን ራሳችን ላይ እናድርግ" Via ፍቅር ለጊዮርጊስ

ክረምት እንደገባ የምናውቀው በወራቱ ወይንም በዝናቡ አይደለም ሁሌ በየዓመቱ በጎረቤቶቻችን የእንበላዋለን ፉከራ ነው ወዳጄ እኛ ተኝተን ዋንጫ ያለበላህ ከተኛንበት በተነሳንበት እለት በህልምህ አበላም
ክረምት እንደገባ የምናውቀው በወራቱ ወይንም በዝናቡ አይደለም ሁሌ በየዓመቱ በጎረቤቶቻችን የእንበላዋለን ፉከራ ነው ወዳጄ እኛ ተኝተን ዋንጫ ያለበላህ ከተኛንበት በተነሳንበት እለት በህልምህ አበላም ሁሌም ፍፃሜው የታወቀ ነው ዘንድሮም ታይቷል ቀጣይም ይቀጥላል ውርዬ ቢጫና ቀዩን ብትለብሺ የኛን ሙሉ ስኳድ በውሰት ብንሰጥሽ እንኳን ዋንጫ አትበይም ብዙ አትፎክሪ Screenshot አድርጉት ይሄን ፁሁፍ በእርግጠኝነት በተከታታይ ዓመታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ክብሩ በመመለስ ዋንጫው ይበላል 🏆🏆