fa
Feedback
Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Diinii kee Anaakara (Md Ali)

رفتن به کانال در Telegram

دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol

نمایش بیشتر
1 610
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
Fakut yan taamah arac, faxa marak

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
+1
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

+2
ACBAASH MA MARAAY ? 🔊 SHEK QALI QABDALLA

ሳይታወቀን የሸር መክፈቻ እንዳንሆን ~ የሆነ ጊዜ አንድ ጎረቤት ከሌላ ጎረቤቱ ቤት እየተጫወተ ይቆያል። ምግብ ቀረበ። ጎረቤት ከምግቡ ጋር የተያያዘ የቀልድ አስተያየት ጣል አደረገ፣ እንዲሁ እየሳቀ
ሳይታወቀን የሸር መክፈቻ እንዳንሆን ~ የሆነ ጊዜ አንድ ጎረቤት ከሌላ ጎረቤቱ ቤት እየተጫወተ ይቆያል። ምግብ ቀረበ። ጎረቤት ከምግቡ ጋር የተያያዘ የቀልድ አስተያየት ጣል አደረገ፣ እንዲሁ እየሳቀ ነበር። አንዳንድ እየተባለ በባልና ሚስት መሃል ያልታሰበ ከባድ ጥል ተከሰተ። ሲመስለኝ የቀደመ ክፍተት ኖሮ ጎረቤት ሳያስበው ሰበብ ሆኗል። የልጅነት ትዝታ ስለሆነ ዝርዝሩ ትዝ አይለኝም። ትዝ ቢለኝም የሚጠቅም አይደለም። ቀጥዬ ለማነሳው ነጥብ ማሳያ ምሳሌ እንዲሆነኝ ነው ያነሳሁት። ሚስትን ከባል፣ ልጅን ከወላጅ፣ ሰራተኛን ከአሰሪ፣ ጓደኛን ከጓደኛ፣ ሸይኽን ከሸይኽ፣ ማጋጨትና ማለያየት የከፋ ሸር እንደሆነ ለማንም ግልፅ ነው። ነገር ግን አንዳንዴ እንዲህ አይነት ጥፋቶችን ክፋትን ሳናስብ ልንፈፅመማቸው እንደምንችል እንዘነጋለን። * ታመህ ሊጠይቅህ የመጣ ሰው ምንም ክፋትን ሳያስብበት እንደዋዛ "እንትና ይጠይቅሃል?" ብሎ የጣለው ቃል ውስጥህን ሊያደፈርሰው ይችላል። * "ባልሽ ለጥሎሽ ያደረገው ይሄው ነው? የወለድሽ ጊዜስ? የኔኮ እንዲህ እንዲህ አድርጎልኛል?" የሚል ቃል ምናልባት ሚስትን በባሏ ላይ ቅሬታ ውስጥ ሊከት፣ እሱንም "አቅሜን እያወቀች ለምን ታጨናንቀኛለች? እንዴት አትረዳኝም?" እያለ ነገር ተጓጉኖ ያልተጠበቀ ውጤት ሊያስከትል ይችላል። * "ጓደኛህ እገሌ ግን ምን ሆኖ ነው ሰርግህ ላይ ያልተገኘው?"፣ "ሰራተኛሽ ምግብ ከናንተው ጋር ነው የምትቀርበው? ይሄማ ማቅበጥ ነው!"፣ "ልጅህ ምን ሆኖ ነው ለዒድ መጥቶ ያልዘየረህ?"፣ ... የመሳሰሉ ጥያቄዎች እና ሀሳቦች እንደዋዛ ጥለናቸው አልፈን ውጤታቸው የከፋ ሊሆን ይችላል። እና ባላሰብነው አቅጣጫ ሰዎችን ማቀያየም፣ ትዳርን ማደፍረስ፣ አሰሪና ሰራተኛን ማለያየት፣ ጓደኛና ጓደኛን ማራራቅ ውስጥ እንዳንገባ እላፊ ቃላትን ከመሰንዘር መጠንቀቅ አይከፋም። የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፦ إن من الناسِ مفاتيحُ للخيرِ، مغاليقُ للشرِ، وإن من الناسِ مفاتيحُ للشرّ، مغاليقُ للخيرِ، فطوبى لمن جعلَ اللهُ مفاتيحَ الخيرِ على يديهِ، وويلٌ لمن جعلَ الله مفاتيحَ الشرِّ على يديهِ "ከሰዎች ውስጥ የኸይር መክፈቻዎች እና የሸር መዝጊያዎች የሆኑ አሉ። ሌሎች ደግሞ የሸር መክፈቻዎች እና የኸይር መዝጊያዎች የሆኑ አሉ። አላህ የኸይር መክፈቻዎችን እጁ ላይ ያደረገለት ሰው ምንኛ የታደለ ነው!! አላህ የሸር መክፈቻዎችን እጁ ላይ ያደረገበት ሰው ወዮለት!!" [አስሶሒሐህ፣ አልባኒይ፡ 1332] = የቴሌግራም ቻናል፦ t.me/IbnuMunewor t.me/IbnuMunewor

+1
1 Haytoh Exxa Acbaash Mamaraay.mp311.59 MB

+1
خطبة مكه١٤ جماد.mp325.56 MB

خطبة د.ادريس.m4a20.09 MB

Bidqa bilqisaanam isih bidqa.m4a66.91 MB

ከጁሙዐ ጋር የተያያዙ ጥቂት ነጥቦች ~ 1- መስጂድ ሳይሞላ በየ ጎዳናው በርቀት ሶፍ ሰርቶ መቀመጥ አይፈቀድም። 2- በቂ ቦታ እያለ ከኢማም ተቀድሞ መስገድ አይቻልም። ቦታ ከተጨናነቀ እና አማራጭ ከሌለ ግን ቢቀደምም ችግር የለውም። 3- ኹጥባ እየተደረገ ማውራት፣ በሰዎች ትከሻ ላይ እያቆራረጡ ማለፍ ክልክል ነው። በሞባይል፣ በሲዋክ (መፋቂያ) ራሱ መጠመድ አይገባም። ያንቀላፋ ከሆነ ብቻ እንቅልፉን ለማባረር ሲዋክ ሊጠቀም ይችላል ይላሉ ኢብኑ ዑሠይሚን። 4- በብዙ መስጂዶች የሚከስተው ጁሙዐ እየጠበቁ ረፋድ ላይ በድምፅ ማጉያ ቁርኣን መክፈት ሱና አይደለም። ሱናው ሱረቱል ከህፍም ሆነ ሌላ ሱራ በራስ መቅራት ነው። በድምፅ ማጉያ መክፈት በግላቸው የሚቀሩትን መወስወስ ነው። በዚህ ላይ የሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ሒዛምን ፈትዋ ማየት ይቻላል። 5- በየትኛውም ቀንና ጊዜ መስጂድ የገባ ሰው ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ ቢሆን እንኳን ሁለት ረከዐ "ተሒየተል መስጂድ" መስገድ የጠነከረ ሱና ነው። 6- ጁሙዐ ቀን ዱዓእ እና ሶላት 0ለ ነቢ ማብዛት የተወደደ ነው። እዚህ ላይ ልምዱ አለን ግን? ትኩረት እንስጠው። 7- ለጁሙዐ ገላን መታጠብ ችላ ሊባል የማይገባው ተግባር ነው። ሽቶ መቀባት (ለወንድ)፣ መፋቂያ መጠቀም ተወዳጅ ተግባራት ናቸው። 8- ለወንዶች የጁሙዐ ሶላትን ከነ ጭራሹ አለመጥጣድ ከባድ ጥፋት እንደሆነ ሊያውቁ ይገባል። ተቀጣሪ ሰራተኞችና ተማሪዎች የሚጥጣዱባቸው መስጂዶች መዋጮ በማሰባሰብ እና በረጃጅም ኹጥባ የተነሳ ሰዎች ከጁሙዐ ሶላት እንዳይቀሩ መጠንቀቅ ይገባል። = የቴሌግራም ቻናል:- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

ጫት ~ ጫት የዲን፣ የጤና፣ የቤተሰብ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ ህይወት፣ የሃገር እድገት ፀር ነው። በጫት የተነሳ ትውልዱ ወኔው የፈሰሰ፣ ሞራሉ የላሸቀ የወጣት ጡረተኛ ሆኗል። የጫት ሱስ ወንድም በገዛ እህቱ ላይ፣ ወላጆች በገዛ ልጃቸው ላይ፣ ጎረምሶች በገዛ ወላጆቻቸው ላይ እንዲጨክኑ አድርጓቸዋል። በሰው ፊት ተገርፈው፣ ክፉ ደግ አይተው፣ እንቅልፍ አጥተው፣ ተንገላተው የሚያገኙት ገንዘብ ከጉዳት በስተቀር አንድ ቁም ነገር ለሌለው ነገር እንደ ዋዛ መበተን የጭካኔ ጥግ ነው። በዚህ የተነሳ እህቶቻችንና ወንድሞቻችን ለአመታት በሰው ሃገር ደክመው ያጠራቀሙት ጥሪት እንዲሁ መና ቀርቷል። የጫት ጉዳት ከሚገለፀው በላይ የከፋ ነው። ለችግሩ መባባስ አንዱ ሰበብ ደዕዋ ላይ ያሉ ሰዎች የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ባገናዘበ መልኩ ተገቢ ትኩረት ሰጥተው አለማስተማራቸው ነው። አሁንም በሚገባ ልንነቃ ይገባል። የወገናችን ጉዳት የሚያመው፣ ከልቡ መቆርቆር ያለው ሁሉ! በሚችለው መድረክ ሁሉ ከዚህ መርዛማ ቅጠል ሰዎችን ሊያስጠነቅቅ ይገባል። በዚህ ቅጠል የተለከፉ ወገኖችን ከሱስ ማውጣት ቢያቅተን እንኳ ቢያንስ ልጆቻቸውን በሚጠብቁበት መልኩ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ብናደርግ ቀላል ስኬት አይደለም። ~ የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

Acbaash Umaane kee ken uma qaqhiida macaay? Oson Mamaraay? #shekh_qali_q... https://youtube.com/watch?v=nbTHAhaiZ-8&si=lufXiZHhN2WE5mNo

ቁርአን ለመቅራት እያሰብን በsocial media ምክንያት የምንዘናጋ ሰዎች አንድ ናይጄሪያዊው ወንድማችን የሚገርም አፕ ሰሮቷል። ቁርአን መቅራት የምንፈልግበት ወቅትና ለስንት ደቂቃ መቅራት እንፈልጋ
ቁርአን ለመቅራት እያሰብን በsocial media ምክንያት የምንዘናጋ ሰዎች አንድ ናይጄሪያዊው ወንድማችን የሚገርም አፕ ሰሮቷል። ቁርአን መቅራት የምንፈልግበት ወቅትና ለስንት ደቂቃ መቅራት እንፈልጋለን የሚለውን set እናደርጋለን ከዛ ፌስቡክ ወይም ሌላ ማህበራዊ ሚዲያ ለመግባት set ያደረግነው ደቂቃ ያክል ቁርአን መቅራት ይጠበቅብናል ካልሆነ አይከፍትም። በዚህ ሊንክ ተጠቀሙ https://play.google.com/store/apps/details?id=com.app.quranunlock ለአይፎን:- https://apps.apple.com/ng/app/quran-unlock/id6754449406

እንዲህ አይነት ሰዎች በኃላፊነት ላይ እስካሉ ድረስ፤ ኡማው በአላህ ፈቃድ ከኸይር አይወገድም‼ እኚህ ሰው የአማራ ክልል መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ኑረዲን ቃሲም ሲሆኑ፤ በትናንትናው ዕለት በደሴ ከተማ በሚገኘው ደዌ ሜዳ መስጂድ ካደረጉት የጁሙዓህ ኹጥባህ የተወሰደ ነው። ©: Video Credit: ነሲሓ ቲቪ / Nesiha Tv

አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥም ፊትን ለወንድ መግለጥ ~ አንዳንዴ ፊታቸውን ከባዳ ወንዶች የሚሸፍኑ እህቶቻችን እንዲገልጡ የሚገፋ ጫና ይገጥማቸዋል። ለምሳሌ ጥጋበኛ እጅ ላይ ወድቀው ካልገለጡ ለከባድ ጥቃት ሊጋለጡ ይችላሉ። በመሰል ሁኔታዎች ላይ መግለጥ ይችላሉ? ወይስ ችግሩ የፈለገ ቢከፋ እምቢ ማለት አለባቸው? አስገዳጅ ሁኔታ ሲገጥም የማይፈቀድ ነገር ይፈቀዳል። الضرورات تبيح المحظورات የሚለው የፊቅህ መርህ ጠንካራ መነሻ ያለውና የታወቀ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፦ { لَا یُكَلِّفُ ٱللَّهُ نَفۡسًا إِلَّا وُسۡعَهَاۚ } አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም።" [አልበቀረህ: 286] በአስገዳጅ ሁኔታ ህይወትን ለማትረፍ በክት መብላት ይቻላል። ተጨባጭ የሆነ አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመ የክህደት ንግግር በመናገርም ራስን ማትረፍ ይቻላል። { مَن كَ.فَرَ بِٱللَّهِ مِنۢ بَعۡدِ إِیمَـٰنِهِۦۤ إِلَّا مَنۡ أُكۡرِهَ وَقَلۡبُهُۥ مُطۡمَىِٕنُّۢ بِٱلۡإِیمَـٰنِ } "ከእምነቱ በኋላ በአላህ የካደ ሰው (ብርቱ ቅጣት አልለው)፡፡ ልቡ በእምነት የረጋ ሁኖ (በክህደት ቃል በመናገር) የተገደደ ሰው ብቻ ሲቀር።" [አነሕል: 106] ሌሎችም ጉዳዮች እንዲሁ ይታያሉ። የሙስሊሟ ለባዳ ወንዶች ፊቷን መግለጥም በዚሁ አግባብ የሚታይ ይሆናል። ይህንን መርህ በመንተራስ አስገዳጅ ጉዳይ ሲገጥም ጊዜ ሴት ልጅ ፊቷን መግለጥ እንደምትችል ዓሊሞች ይገልፃሉ። በዚህ ላይ በምሳሌነት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ውስጥ የሚከተሉትን ማንሳት ይቻላል:- 1ኛ፦ በማጨት ጊዜ :- ይሄ ሐዲሦች የመጡበት እንዲሁም ኢጅማዕ ያለበት በመሆኑ ለብዙ ሰውም የሚሰወር ስላልመሰለኝ ለማሳጠር ያክል በዚሁ ልለፈው። 2ኛ፦ ለህክምና፦ ጉዳቱ ያለበት ክፍል ፊትም ሆነ ሌላ ክፍል መግለጥ ይቻላል። ከተቻለ ባል ወይም ሌላ መሕረም (ቅርብ ቤተሰብ) አብሮ መኖር አለበት። ባይሆን ሴት ሃኪም ካለ ወደ ወንድ፣ ሙስሊም ካለ ወደ ሌላ መሄድ አይገባም ይላሉ ዓሊሞች። ለህክምና በሚያስፈልገው መጠን ሃኪሙ አካሏን መመልከት ይችላል ይላሉ ኢብኑ ቁዳማ። [አልሙግኒ፡ 7/459] በነገራችን ላይ ጦር ሜዳ ላይ ሴቶች ሶሐቢያት ወንዶችን ያክሙ ነበር። ኡሙ ዐጢያህ - ረዲየሏሁ ዐንሃ - እንዲህ ትላለች፦ غَزَوْتُ مَعَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ سَبْعَ غَزَوَاتٍ أَخْلُفُهُمْ فِي رِحَالِهِمْ، فَأَصْنَعُ لَهُمُ الطَّعَامَ، وَأُدَاوِي الْجَرْحَى وَأَقُومُ عَلَى الْمَرْضَى "ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር ሰባት ዘመቻዎችን ዘምቻለሁ። እቃዎቻቸውን እጠብቅ፣ ምግባቸውን አዘጋጅ፣ ቁስለኞችን አክም እንዲሁም ህመምተኞችን እንከባከብ ነበር።" [ሙስሊም፡ 1812] የቡኻሪን باب هل يداوي الرجل المرأة، والمرأة الرجل እንዲሁም ዘርዘር ያለ ነገር የፈለገ ፈትሑል ባሪን መመልከትም ይቻላል። 3ኛ፦ ችሎት ላይ፦ በፍርድ ችሎት ላይ ፍርድ ለመስጠት ዳኛው አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ፊቷን ይመለከታል። ካልሆነ ሐቅን ማስከበር አስቸጋሪ ሊሆንበት ይችላል። ምስክር ሆና ስትቀርብ ወይም በሷ ላይ ምስክርነት ለመስጠትም እንዲሁ መገለጥ ግዴታ ሊሆን ይቻላል። ኢብኑ ቁዳማ እንዲህ ይላሉ፦ وللشاهد النظر إلى وجه المشهود عليها لتكون الشهادة واقعة على عينها، قال أحمد: لا يشهد على امرأة إلا أن يكون قد عرفها بعينها "መስካሪ ሰው ምስክርነቱ ቦታው ላይ ያረፈ ይሆን ዘንድ የሚመሰከርባትን ሴት ሊመለከት ይችላል። (ኢማሙ) አሕመድ 'በትክክል ለይቶ እስካላወቃት ድረስ አንዲት ሴት ላይ አይመሰክርም' ብለዋል።" [አልሙግኒ፡ 7/459] ይሄ የሳቸው ሃሳብ ብቻ አይደለም። ሌሎችም "ኒቃብ በለበሰች ሴት ላይ ፊቷን ሳትገለጥ መመስከር አይቻልም" ይላሉ። [አሸርሑል ከቢር፣ ደርዲር፡ 4194] 4ኛ፦ በግብይት ላይም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ሻጭ ወንድ ገዢዋን ሴት ሊመለከት እንደሚችል ዑለማኦች ይገልፃሉ። [አልሙግኒ፡ 7/459] ያለበለዚያ በግብይቱ ላይ ለተፈጠረ ክፍተት ማስተካከያ ለማድረግ ሊቸገር ይችላል። ለምሳሌ እቃ ሽጦላት ፊቷን ካላየ ኋላ ላይ እቃው ችግር ኖሮበት መመለስ ቢያስፈልግ በትክክል እሷ መሆኗን መለየት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል። 5ኛ፦ አስገዳጅ ህግ ባለበት ሁኔታ፦ በአንዳንድ ሃገራት ህግ ወይም ኤርፖርት አካባቢ ወይም ሌላ አስገዳጅ ሁኔታ ከገጠመም ፊቷን መግለጥ ትችላለች። ለምሳሌ በመጥፎ ሰዎች እጅ ላይ ወድቃ ራሷን አደጋ ላይ ከምትጥል ፊቷን በመግለጥ ራሷን ማትረፍ ትችላለች። "አስገዳጅ ሁኔታዎች የተከለከለን ነገር ያስፈቅዳሉ።" ስለዚህ ማንነቷን ለመለየት የሚጠይቅ አስገዳጅ ሁኔታ ቢገጥም ወይም ሌላ ተጨባጭ ምክንያት ከኖረ ፊቷን መግለጥ ትችላለች ማለት ነው። ይሄ እንግዲህ ከዑለማኦች አቋም ውስጥ ለደረሰች ሴት ልጅ ፊትን መሸፈን ግዴታ ነው የሚለውን ስንወስድ ነው። የሆነ ሆኖ ጫን ያለ ሁኔታ ካልገጠማት በስተቀር ለትንሽ ለትልቁ እጅ ልትሰጥ አይገባም። ፍተሻና መሰል ቦታዎች ላይ ሴቶችን መጠቀም የሚቻልበት ሁኔታ ካለ ወይም ደግሞ ጉዳዩ አንገብጋቢ ካልሆነ ባዳ ለሆኑ ወንዶች ፊትን መግለጥ አይገባም። አስገዳጅ ችግር ሲገጥም ደግሞ ጉዳዩን በችግሩ መጠን ብቻ ማስተናገድ ይገባል። "አስገዳጅ ሁኔታዎች በልካቸው ነው የሚስተናገዱት።" እንጂ ችግሩን ማመሀኛ አድርጎ አጉል መዘናጋት ውስጥ መግባት አይገባም። ወላሁ አዕለም! በነጥቡ ላይ ሃሳብ ያለው ሰው ማካፈል ይችላል። = (ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 01/2017) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

Baxsa le farmo... Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council gubat raqtah tan fatwâ malah buxa afdeerâ daqaarak cayli gubbil y
Baxsa le farmo... Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council gubat raqtah tan fatwâ malah buxa afdeerâ daqaarak cayli gubbil yekke bakaqak ugutak maybalaalaqa yeceen. Ta maybalaalaqal aham yalli waktiik waktil isi astoota akah yayballeem isi naqoosa edde meysiisá iggidaay, kaaduk qhiyaama xayiimih astooti kinnuuk yamaate jumqaatah qhiyaamah astooti elle baxxaqisan khutba imaamoota taceeh, ummatta kee sadga yaymaggeeniih, yunzullume marah cakki gacsaanam kee kalah tan meqaane yaymaggeenim kee yalla fanah yadaareenim faxxintam kassiisen. Afar Kassis Media