Central Ethiopia Regional Health Bureau
رفتن به کانال در Telegram
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ 🔵 https://m.facebook.com/centralethiopiarhb 📞 📩
نمایش بیشتر4 312
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+87 روز
+2330 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
مارس '25
مارس '25
+7
در 0 کانالها
فوریه '25
+66
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '25
+98
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '24
+135
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '24
+127
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '24
+106
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '24
+89
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '24
+200
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '24
+215
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '24
+138
در 0 کانالها
Get PRO
مه '24
+180
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '24
+134
در 2 کانالها
Get PRO
مارس '24
+120
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '24
+119
در 1 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+103
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+105
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+33
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '23
+36
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+32
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+89
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+98
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+73
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+99
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+64
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+41
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+44
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+123
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+3 479
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 03 مارس | +3 | |||
| 02 مارس | +3 | |||
| 01 مارس | +1 |
پستهای کانال
| 2 | ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከርና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ እና መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ።
በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢኒስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር የተመራው የጤና ሚኒስትር ደጋፋዊ ክትትል ቡድን ከማዕከላዊ ኢት/ያ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በክልሉ የወባ በሽታ መከላከልና የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂዷል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ክትትል ቡድን ከማዕከላዊ ኢት/ያ ክልል ኃላፊዎች የማናጅመንት አካላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሁሉም የጤና አጠባበቅ እና የወባ ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡
የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የወባ ወረርሽኝን ከመከላከል ከመቆጣጠር አኳያ በርካታ ስራዎች መሠራታቸውን በመጠቆም ከዚሁ ስራ በተያያዘ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች, የፌደራል ባለድርሻ ተቋማት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች አስከታችኛው መዋቅር ያሉ የተለያዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አመራር አካላትና የጤናው ሴክተር አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ማህበረሰቡ ያደረጉት ድጋፍና ክትትል ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል ብሎም ለመግታት በክልሉ የሚገኙ ጤና ተቋማት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡
በጤና ሚኒስቴር የአርማወር ሀንሰን ኢኒስቲትዩት የተመራው የድጋፋዊ ክትትል ቡድን የህብረተሰቡን ጤና የማስጠበቅ ጉዳይ ለጤና ቢሮ ብቻ የሚተው ሳይሆን የሁሉም ባለድርሻን ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን አስረድተው በክልሉ እየተደረገ ያለው ስራ በጥሩነት አንስተዋል፡፡
የድጋፋዊ ክትትል ቡድኑ በክልሉ ውስጥ በተለያዩ የክልሉ መዋቅሮች በቀጣይ ለተከታታይ ሳምንት በዞን በልዩ ወረዳዎች በጤና ተቋማት እና ቤት ለቤት በመንቀሳቀስ የድጋፍ ክትትል ስራውን ያከናውናል ተብሎ ይጠበቃል።
የማ/ኢት/ክ/ጤና ቢሮ | 1 522 |
| 3 | የጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጥናት ለሚያደርግ የጥናት ቡድን ስምሪት መሰጠቱ ተገለጸ።
የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ለጥናታዊ ቡድኑ የስራ ስምሪት በሰጡበት ወቅት ጥናቱ በክልሉ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች በ39 ጤና ጣቢያዎች በ10 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች እና በ3 አጠቃላይ ሆስፒታሎች በጥናት የተደገፈ ተግባር የሚፈጽም መሆኑን አስረድተዋል።
የሰው ሀይል ውጤታማነት፣ የግብአት እና የመድሀኒት አቅርቦት እንዲሁም አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ስርአት፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እንዲሁም በጤና ተቋማት የሚታዪ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ትኩረት ባደረገ መልኩ ጥናት እንደሚደረግ አቶ ሳሙኤል አክለው ገልፀዋል።
የጥናት ግኝቱ የጤናው ሴክተር ላይ በተለይም የጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት መሻሻል ላይ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሳሙኤል ለዚሁ ተግባር ስኬታማነት በየደረጃው ያሉ መዋቅሮች እና ጤና ተቋማት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ እና ትክክለኛ መረጃ ለጥናት ቡድኑ መስጠት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል:።
የክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ እና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን ለጥናቱ በቢሮው በኩል በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልፀው የጥናት ቡድኑ የጥናቱን አላማ በተገቢው በመረዳት ተግባሩን በጥብቅ ስነምግባር ሊፈጽሙት እንደሚገባ አሳስበው
ጥናቱ በአራት ቡድን 52 ጤና ተቋማት ላይ ለቀጣይ 15 ቀናት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ | 1 395 |
| 4 | بدون متن... | 1 636 |
| 5 | የአለም የአዕምሮ ጤና ቀን በወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እየተከበረ ይገኛል።
የአለም የአዕምሮ ጤና ቀን"በሥራ ቦታ ለአዕምሮ ጤና ቅድሚያ የምንሰጥ ጊዜ ነው" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑም ታውቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ የስነ አዕምሮ የጤና ችግር በሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ የሰው ልጆችን ሊያጠቃ የሚችል በሽታ መሆኑን ገልጸዋል።
ተከታታይነት ያለው የአስተሳሰብ እና የባህሪ ለውጥ እና ከበድ ያለ የአዕምሮ ጭንቀት ሲያጋጥም ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባ የገለጹት አቶ ሳሙኤል የሥነ ልቦናና የማህበራዊ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በክልሉ በሚገኙ ሆስፒታሎች የአእምሮ ጤና ችግርን ለመከላከል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሙሉ አቅሙ ህክምናውን እየሰጠ መሆኑን አመላክተዋል።
የስነ አዕምሮ ህመም የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል የግን እዛቤ ማስጨበጫ መስራት እንደሚገባ በመግለጽ ህብረተሰቡ ለአዕምሮ ጤናና ተጓዳኝ የሆኑ የጤና ችግር ለሚያስከትሉ ለሚችሉ ሱሶች ተጋላጭ እንዳይሆን እየተሰራ መሆኑንም አቶ ሳሙኤል አክለው ገልጸዋል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ህይወት ሰለሞን በበኩላቸው የአዕምሮ ጤና ችግር ከፍተኛ የጤና ችግር ከሚያስከትሉ በሽታዎች መካከል አንዱ መሆኑ ገልጸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የሚያስከትል መሆኑን አስገንዝበዋል።
የአዕምሮ ጤና ጉዳይ በሁሉም ቦታ ሊከሰት የሚችል መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ ህይወት ለአዕምሮ ጤና ችግር ማህበረሰቡን ከሚዳርጉ ችግሮች እራሱን እንዲጠብቅ በማድረግ፣ የጤና ችግሩ ሲያጋጥም ፈጥኖ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ገልጸዋል።
የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ በበኩላቸው በሆስፒታሉ የአዕምሮ ጤና ህክምና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረው የአዕምሮ ጤና ችግርን ለመቅረፍ በጋራ ቅንጅታዊ አሰራሩን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አቶ ሌልሳ አማኑኤል የጤና ሚንስትር ሚንስተር ዴኤታ ከፍተኛ አማካሪ ፣አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የማዕ/ኢት/ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ፣፣ ዶክተር ህይወት ሰለሞን የጤና ሚንስትር በሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ ፣ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ የወራቤ ኮምፕሬሄንሲብ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስካያጅ፣ አቶ ጀማል ሽፋ የቅ/ጰ/ሚ/ሜ/ኮ/ሆስፒታል አስተዳደር እና ቢዝነስ ም/ፖሮቮስት፣ሀጂ መሀመድ ከሊል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዚዳንት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ መሆናቸው ታውቋል።
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ | 1 390 |
| 6 | بدون متن... | 1 191 |
| 7 | የአለም የአዕምሮ ጤና ቀን በወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እየተከበረ ይገኛል።
የአለም የአዕምሮ ጤና ቀን"በሥራ ቦታ ለአዕምሮ ጤና ቅድሚያ የምንሰጥ ጊዜ ነው" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑም ታውቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ የስነ አዕምሮ የጤና ችግር በሁሉም የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ የሰው ልጆችን ሊያጠቃ የሚችል በሽታ መሆኑን ገልጸዋል።
ተከታታይነት ያለው የአስተሳሰብ እና የባህሪ ለውጥ እና ከበድ ያለ የአዕምሮ ጭንቀት ሲያጋጥም ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚገባ የገለጹት አቶ ሳሙኤል የሥነ ልቦናና የማህበራዊ ድጋፍ መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በክልሉ በሚገኙ ሆስፒታሎች የአእምሮ ጤና ችግርን ለመከላከል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሙሉ አቅሙ ህክምናውን እየሰጠ መሆኑን አመላክተዋል።
የስነ አዕምሮ ህመም የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል የግን እዛቤ ማስጨበጫ መስራት እንደሚገባ በመግለጽ ህብረተሰቡ ለአዕምሮ ጤናና ተጓዳኝ የሆኑ የጤና ችግር ለሚያስከትሉ ለሚችሉ ሱሶች ተጋላጭ እንዳይሆን እየተሰራ መሆኑንም አቶ ሳሙኤል አክለው ገልጸዋል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ህይወት ሰለሞን በበኩላቸው የአዕምሮ ጤና ችግር ከፍተኛ የጤና ችግር ከሚያስከትሉ በሽታዎች መካከል አንዱ መሆኑ ገልጸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የሚያስከትል መሆኑን አስገንዝበዋል።
የአዕምሮ ጤና ጉዳይ በሁሉም ቦታ ሊከሰት የሚችል መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ ህይወት ለአዕምሮ ጤና ችግር ማህበረሰቡን ከሚዳርጉ ችግሮች እራሱን እንዲጠብቅ በማድረግ፣ የጤና ችግሩ ሲያጋጥም ፈጥኖ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ገልጸዋል።
የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ በበኩላቸው በሆስፒታሉ የአዕምሮ ጤና ህክምና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረው የአዕምሮ ጤና ችግርን ለመቅረፍ በጋራ ቅንጅታዊ አሰራሩን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
አቶ ሌልሳ አማኑኤል የጤና ሚንስትር ሚንስተር ዴኤታ ከፍተኛ አማካሪ ፣አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የማዕ/ኢት/ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ፣፣ ዶክተር ህይወት ሰለሞን የጤና ሚንስትር በሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈፃሚ ፣ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ የወራቤ ኮምፕሬሄንሲብ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስካያጅ፣ አቶ ጀማል ሽፋ የቅ/ጰ/ሚ/ሜ/ኮ/ሆስፒታል አስተዳደር እና ቢዝነስ ም/ፖሮቮስት፣ሀጂ መሀመድ ከሊል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዚዳንት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ መሆናቸው ታውቋል።
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ | 860 |
| 8 | بدون متن... | 1 320 |
| 9 | በጤናው ሴክተር የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የውይይት መድረክ ባደረገበት ወቅት የማህበረሰቡን የጤና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ርብርብ በጉልህ ለደገፉ አካላት የዕውቅናና የማበረታቻ ሰርተፊኬት መርሀ ግብር አካሂዷል።
በገንዘብ በህክምና መገልገያ መሳሪያዎች በሀሳብ እንዲሁም የእርሻ መሬታቸውን ለጤና ተቋም ግምባታ በመስጠት የጤናውን ሴክተር ተግባር በአግባቡ በመደገፍ ለህብረተሰቡ ፍትሀዊና ጥራት ያለው የጤና አገ/ት ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የክልሉ ጤና ቢሮ ልባዊ ምስጋናውን እያቀረበ በቀጣይም በሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማሳሰብ ሌሎች ባለድርሻ አካላትም የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ተጠይቋል።
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ | 1 271 |
| 10 | بدون متن... | 1 114 |
| 11 | بدون متن... | 907 |
| 12 | የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥ ይበል የሚያስብል ነው ሲሉ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ገለጹ!
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ም/ል ርዕሰ መስተዳድርና የት/ት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ በኢፌድሪ ጤና ሚ/ር ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ የተመራ የሚ/ር መስሪያ ቤቱ የማኔጅመንት አካላት ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌና የማኔጅመንት አካላትና እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናቱና የስራ ኃላፊዎቹ የሆስፒታሉን የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
ዶ/ር ካሊድ ከሆስፒታሉ መቋቋም ታሪካዊ ዳራ ጀምረው የተደረገውን የአገልግሎት ማስፋፊያና የወደፊት ራዕዩን ለጎብኚዎቹ ያብራሩ ሲሆን ጉብኝት የተደረገባቸውን የስራ ክፍሎችም የአገልግሎት አሰጣጥና አቅም አስረድተዋል።
ተቋሙ በህ/ሰብ ከፍተኛ ተሳትፎ መገንባቱን የገለጹት ዋና ስራ አስኪያጁ ከአካባቢውና አጎራባች ዞኖች ባሻገር ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ለሚመጡ ዜጎች የስፔሻሊቲና የሰብ-ስፔሻሊቲ የህክምና አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ አክለዋል።
ሆስፒታሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ አገልግሎቱን እያስፋፋ መሆኑንም በማንሳት ማስፋፊያውን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማኖርም የመንግስትን ድጋፍ እንደሚሹ ጠቁመዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ም/ል ርዕሰ መስተዳድር፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አንተነህ ፍቃዱ ሆስፒታሉ በከፍተኛ የህክምና መሳሪያዎች በመደራጀት የሚሰጠው አገልግሎት የዜጎችን አላስፈላጊ እንግልት የሚቀንስ መሆኑን ጠቁመው ይህም ከክልሉም አልፎ ለሀገር አቅም መሆኑን በመጥቀስም ከጤና ቢሮ ጋር በመተባበር አስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
ተቋሙ የቀዶ ህክምና የሚሰጥበት የስራ ባህል ሊበረታታና ለሌሎችም ተሞክሮ መሆን የሚችል መሆኑን ያነሱት የኢፌድሪ ጤና ሚ/ር ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ የአዕምሮ ህክምና ክፍል የሚሰጠው አገልግሎት ከፍተኛ መሆኑን በመጥቀስም ወደሌሎች የአካባቢው የህክምና ተቋማት መስፋት ይኖርበታል ብለዋል።
ሆስፒታሉ ለዜጎች የሚሰጠውን አገልግሎት አጠናክሮና አስፋፍቶ እንዲቀጥል በማሳሰብ ለዚህም የመንግስት ድጋፍ እንደማይለየው ቃል ገብተዋል።
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በበኩላቸው ሆስፒታሉ ለሌሎች ጤና ተቋማት የሚያደርገው እገዛ የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር መሆኑን በማንሳት ይህንኑ ለማገዝ በቢሮው በኩል የተቻለው ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
ዘገባው የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነው | 623 |
| 13 | بدون متن... | 865 |
| 14 | بدون متن... | 710 |
| 15 | የጤናው ፖሊሲ ዜጎች ጤናቸውን የማበልጸግ ሂደት ላይ ንቁ ተሳትፎ አንዲኖራቸው የሚያግዝ መሆኑን የማ/ኢት/ክ/መ/ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ ገለጹ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2016 በጀት አመት አፈጻጸም ግምገማ እና የንቅናቄ መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሔደ ይገኛል።
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ በምክክር መድረኩ እንደገለጹት ክልሉ የተመሰረተበትን አንደኛ አመት እያከበረ ባለበት ወቅት
መሆኑን ጠቁመው የተረጋጋ ሰላማዊ በዜጎች ተመራጭ እና ፈጣን እድገት እያስመዘገበ ያለ ክልል እንደሆነም አስረድተዋል።
ጤና ለሁሉም ነገር የዕድገት መሰረት ከመሆኑም ባሻገር የማህበረሰቡን የጤና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ብሎም ለህብረተሰቡ ብልጽግና መሰረት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ያመላከቱት ኃላፊው ለሰው ልጆች መሰረታዊ መብት ስለመሆኑም አቶ አንተነህ አክለው ገልጸዋል።
ዜጎች ጤናቸውን የማበልጸግ ሂደት ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ሆኖ የተቀረጸውን የጤና ፖሊሲ ስርዓቱን ወደ ተግባር ከመለወጥ ጋር ተያይዞ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ አንተነህ ዘመኑ ያፈራቸውን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም የጤናውን ሴክተር ስራ በጤና ተቋማት ደረጃ በማዘመን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ የጤና አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ እድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል።
የክልሉ ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴርም እና በክልሉ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት ይህንን ተግባር በበላይነት በመፈጸም ስራዎችን በአግባቡ ማሳለጥ የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት እንዳለበትም አቶ አንተነህ ተናግረዋል።
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በክልሉ የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፣ የነፍሰ ጡር እናቶች ማቆያ፣ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን፣ ወባን የማጥፋት ፕሮግራም፣ በጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የተከናወኑ ተግባራትን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
በድንገተኛ ወረርሽኞች የማይበገር የጤና ስርዓት ለመዘርጋት በትኩረት እንደሚሰራ የገለጹት አቶ ሳሙኤል
በጤናው ዘርፍ ያሉትን ጠንካራ ጎኖች በማስፋት እና በጉድለት የሚጠቀሱ ጉዳዮች እንዲታረሙ በልዩ ትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።
የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ውጤታማነት ሞዴል ወረዳዎችን በመፍጠር በገጠር እና በከተማ አካባቢዎች በዘርፉ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል።
ከክትባት አገልግሎት አንጻር ሽፋኑን መቶ በመቶ መድረስ የተቻለ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊው ከመረጃ ጥራት እና ከሪፖርት ተአማኒነት ጋር ተያይዞ ያሉ ጉድለቶችን ለማረም በትኩረት እንደሚሰራ አቶ ሳሙኤል አስገንዝበዋል።
የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በበኩላቸው መከላከልን መሠረት ያደረገውን የጤና ፖሊሲ ተግባራዊ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን የጤና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል።
የህብረተሰቡ የጤና ችግር ሆነው የቆዩ በሽታዎችን መከላከል ፣መቆጣጠርና መቀነስ የተቻለበት ሂደት መኖሩን ዋና አስተዳዳሪው አስረድተዋል።
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ | 697 |
| 16 | بدون متن... | 941 |
| 17 | ነሀሴ 27/2016 ዓ/ም
የአመራር እና የፈፃሚ ተነሳሽነት ቁርጠኝነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ የህዝባችንን የጤና አገልግሎት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን እናረጋግጥ በሚል መሪ ቃል የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ የንቅንናቄ መድረክ በቡታጀራ ከተማ እየተካሄደ ነዉ።
የአመራር እና የፈፃሚ ተነሳሽነት ቁርጠኝነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ የህዝባችንን የጤና አገልግሎት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን እናረጋግጥ በሚል መሪ ቃል የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የንቅንናቄ መድረክ በቡታጀራ ከተማ እየተካሄደ መሆኑን የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ ገልጿል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የንቅናቄ መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት የዜጎችን የጤና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ እና ማህበረሰቡን የጤናው ባለቤት በማድረግ የበለፀገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት እና በተጠያቂነት መንፈስ ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።
በቢሮዉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በርካታ ተሞክሮ ሊቀመርባቸው የሚችሉ ተግባራት መከናወናቸውን የጠቆሙት ሀላፊው በድንገት በወረርሽኝ መልክ የሚከሰቱ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ጠንካራ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።
በክልሉ የኮሌራ፣ የኩፍኝ፣ በሽታ ወረርሽኞች ተከስተው በየደረጃው ያሉ አመራሮች ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው ባደረጉት ርብርብ የከፋ የጤና ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የጠቆሙት ኃላፊው ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጡን ተከትሎ የጎርፍ አደጋ እና የወባ ወረርሽኝ እየተስፋፋ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ ችግሩን ለመቅረፍ የሚያስችል ጠንካራ ተግባራት መከናወናቸውን በመግለጽ በዚያዉ ልክ ጉድለቶችን ለይቶ ውጤት በሚያመጣ መልኩ ርብርብ ማድረግ አንደሚገባ አስረድተዋል ።
የንቅናቄ ጉባኤው ስራዎችን ታሳቢ ያደረገ እና የህብረተሰቡን የጤና ተጠቃሚነት መነሻ በማድረግ እንዲሁም አመታዊ አፈፃፀምን መሠረት ያደረገ ውጤታማ ውይይት ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የተሳካና ለቀጣይ ስራ መሠረት የሚጣልበት ውይይት በማድረግ በተለይ የማህ/ ዓቀፍ ጤና መድን ላይ፣ ከሀብት ማሰባሰብ ጀምሮ እስከ ሀብት ብክነት ድረስ ያሉ ጉዳዮችን እንዲሁም የቁጥጥር ዘርፉን ተግባር በአግባቡ ማጠናከር ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የንቅናቄ መድረኩ የጤና ልማት ስራውን በአግባቡ በማሳለጥ የማህበረሰቡን የጤና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያለመ እና በየደረጃው በጉድለት ለተለዩ ተግባራት ችግር ፈቺ ወይይት በማድረግ በቀጣይ የድርጊት መርሃ ግብር በማውጣት ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግበትም አቶ ሳሙኤል አክለው ገልጸዋል።
በጤናው ዘርፍ የአመራር እና የፈጻሚ ተነሳሽነት ቁርጠኝነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ የህዝቡን የጤና አገ/ት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ የንቅናቄ ሰነድ በቡድን ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ የዞንና የልዩ ጤና መምሪያ እና ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች አጋር ድርጅቶች፣ በክልሉ የሚገኙ ደም ባንኮች፣ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረኩ ተሳታፊዎች መሆናቸው ታውቋል።
የንቅናቄ መድረኩ የክልሉ እና የፌዴራል ጤና ሚኒስትር ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በነገው ዕለት የሚቀጥል እንደሆነም ተገልጿል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ | 929 |
| 18 | بدون متن... | 1 615 |
| 19 | የማዕላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በስልጢ ወረዳ የጎፍለላ ቀበሌ የጎርፍ ተፈናቃዮችን ጎበኙ!
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የተመራ ቡድን የጎፍለላ የጎርፍ ተፈናቃዮችን ጎብኝተዋል።
የቢሮ ኃላፊውና ልዑካቸው በጎፍለላ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች ያሉበትን ሁኔታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል ::
የተከሰተውን አደጋ ለመከላከልና ተፈናቃዮችን ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከጎርፉ ጋር ተያያዥ የሆኑ የጤና ጠንቆች እንዳይቀሰቀሱ የክልሉ ጤና ቢሮ ድርሻውን ይወጣል ሲሉ አቶ ሳሙኤል ተናግረዋል ።
የስራ ኃላፊዎቹና የቢሮው የባለሙያዎች ቡድን የኩኖ ጤና ጣቢያ አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ያደረጉ ሲሆን በምልከታቸው ማጠቃለያም በቦታው ለተገኙ በየእርከኑ ላሉ የጤና ባለድርሻ አካላትም ስምሪት ሰጥተዋል።
አቶ ሳሙኤል ተፈናቃዮች ክረምቱንና ጎርፉን ተከትሎ ከሚከሰቱ በሽታዎች እራሳቸውን መጠበቅ እንዳለባቸውም አክለው ገልጸዋል ።
ከተከሰተው ችግር ጋር ተያይዞ ተጎጂዎችን ለማቋቋምና አደጋውን ለመከላከል ሁሉንም አማራጮች እንጠቀማለን ሲሉ ተናግረዋል።
በጉብኝቱም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የጤና ኤክስፐርቶች፣ የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ ሀይረዲንና ሌሎች የዞንና የወረዳ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
ለስ/ወ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ዘገባ
የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ | 1 208 |
| 20 | بدون متن... | 1 300 |
