cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Central Ethiopia Regional Health Bureau

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ 🔵 https://m.facebook.com/centralethiopiarhb 📞 📩

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 744
المشتركون
+224 ساعات
+227 أيام
+10930 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

1
ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነፃ ቀበሌያትን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ። የምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የምዕራብ ሙጎ ቀበሌ የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት መስፈርቶችን አሟልቶ ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነጻ ሆኖ ተመርቋል። "የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት ሽፋን በማሳደግ ጽዱ ኢትዮጵያን እውን እናድርግ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የፅዱ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ተጠናክሮ ቀጥሏል ። ቀበሌው የግልና የጋራ መጸዳጃ ቤት በጥራት በመስራት እያንዳንዱ ቤተሰብ የራሱን ጤና ከመምራት ባለፈ ማህበራዊ ሃላፊነትን ወስዶ በተደራጀና ቀጣይነት ባለው መልኩ የአከባቢውን የጤና ሁኔታ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት እየሰራ ይገኛል ። የምዕ/ሙጎ ቀበሌ በተለያዩ ተግባራት  ሞዴል መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ላይም እያደረገ ያለውን ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል የፅዱ ኢትዮጵያን ምዕራፍ በማሻገር ዘላቂ የጤና መፍትሄ መፍጠር እንደሚገባም ተገልጿል ። ከለላ ያለው፣ ወለሉ መታጠብ የሚችል፣ ጣሪያው ዝናብ የማያስገባ፣ ግጣም(ክዳን) ያለው፣ ውሃና ሳሙና ያለው፣ ከ1 ሜትር ከፍታ በላይ ያለውና ሌሎችም የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት መስፈርት መሆኑን በዕለቱ ተመላክቷል። በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ዋና አፈ ጉባዔ ክብርት ወ/ሮ ለይላ ራመቶ ፣ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አ/ፈታ መሀመድ፣  የሴቶችና ህጻናት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሸቦ ሳይድ፣ ጤና ኤክስቴንሽኖች፣የጤና ጣቢያና ጤና ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች እንዲሁም የጤና ልማት ሰራዊትና ሌሎችም ተገኝተዋል። ህብረተሰቡ ከተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች ራሱን መጠበቅ የሚችለው የግልና የአከባቢ ንጽህና በመጠበቅ መሆኑን አውቆ የመጸዳጃ ቤትና ሌሎች መሰል ተግባራትን  በጥራት ማከናወን እንደሚገባ ተጠቁሟል ። በመጨረሻም ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ጉልህ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት እውቅና የተሰጠ ሲሆን ተግባሩ የአንድ ጊዜ ብቻ አለመሆኑን በመገንዘብ ስራዉ ከዚህ በተሻለ መልኩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በምርቃ ፕሮግራሙ ማጠቃለያ  ላይ  ተገልፆዋል። ለስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ዘገባ የማ/ኢት/ክ/መ/ጤ/ ቢሮ
إظهار الكل...
👍 1
🙏 1
2
የበሪዮ ቀበሌ ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ ሆኖ ተመረቀ። ሰኔ 29/2016፣ ወልቂጤ፣ የቀ/ል/ወ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የበሪዮ ቀበሌ 18ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ተግባራዊ በማድረጉ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። በስፍራው የተገኙት የቀቤና ልዩ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድልማሊክ አብደላ እንደተናገሩት ህብረተሰቡ የግልና የአካባቢውን ንጽህና በመጠበቅ ከተላላፊ በሽታዎች ራሱን መጠበቅ እንዲሁም ለህክምና የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን በቀላሉ አካባቢን በማፅዳት አና የተሻሻለ መፀዳጃ ቤት ገንብቶ በመጠቀም መከላከል እንደሚቻል ተናግረው ቀበሌው ፅዱ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። የልዩ ወረዳው ጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድለሀይ ኑርሀሰን እንደተናገሩት በፅዱ መንደር ፕሮግራም የተመረጡ ቀበሌዎች 10 መሆናቸውን በማስታወስ የበሪዮ ቀበሌ ሲመረቅ ዘጠነኛው ነው ብለዋል። በተጨማሪም በቀበሌው የተጀመሩ የጤና ኤክስቴንሽን ስራዎችን ለማስቀጠል ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ያሉ ሲሆን ቀበሌው ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ በመሆኑ እና ሞዴል ቀበሌ ሆኖ በመመረቁ ለቀበሌው ነዋሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። በመጨረሻም በቀበሌው የተሰሩ የግልና የአካባቢ መጸዳጃ ቤቶችን ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን እየተሰሩ ያሉ ሰሰራዎች አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የአንድ ቀን ተግባር ሆነው እንዳይቀሩ ጥብቅ መልዕክት በማስተላፍ ቀበሌው ሞዴል እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ሰርተፍኬት ተሰጥቷቸዋል። **** #ውጤታማ ተግባቦት ለሀገር አንድነት ❗️ ለቀ/ል/ወ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ዘገባ የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ
إظهار الكل...
👍 2
"ኤግዚቢሽኑ ከዝቅተኛ የህክምና ግብዓት አምራችዎች ጀምሮ በዘርፉ ለተሰማሩ አምራችዎች የእርስ በርስ ግንኙነትን ለማጠናከር እና የሀገር ውስጥ ምርትን ለማሻሻል ጠቃሚ ነው!!" ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ____ የአገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ከሰኔ 15/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ መካሄዱ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ በኤግዚበሽኑ ጉብኝት ላይ ተገኝተው አጠቃላይ ስለ ኤግዚቢሽኑ መረጃ የሰጡት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንዳሉት በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው የአገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽንን በርካታ ጎብኚዎች እየተሳተፉበት እንደሆነ አንስተው በሁለቱ ቀናት ውስጥ ሃያ ስምንት ሺህ ጎብኚዎች ጎንኝተውታል ብለው በኤግዚቢሽኑ በርካታ የመረጃ ልውውጥና የዕውቀት ሽግግር እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ የህክምና ግብሃትንና መሳሪዎችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሀገሪቱ ለመድሃኒትና ለህክምና ግብአት የምታወጣውን ወጪ በመቀነስ የጤናውን ዘርፍ የገንዘብ አቅም ማሻሻል እና የመድሃኒትና የህክምና ግብዓት አምራችዎችን የእርስ በርስ ግንኙነትን ለማጠናከር እና የሀገር ውስጥ ምርት አጠቃቀምን በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረው የህክምና ግብዓት አምራችዎችን ፣ተቆጣጣሪ አካላትን፣የጥናትና ምርምር ባለሙያዎችና ዩኒቪርስቲዎች ፣ህክምና ግብዓት ምርት ፈላጊዎችንና ወኪል ድርጅቶችን እንዲሁም ባለድርሻ አካላትን ለማገናኘት ጉልህ አስተዋጽ እንዳለውም ዶ/ር መቅደስ አብራርተዋል፡፡ ኤግዚቢሽኑን የጎበኙት የመንግስት ግዢ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ክፍሌ ገ/ማሪያም በበኩላቸው በኤግዚበሽኑ ምንያህል የሀገር ውስጥ አምራችዎች እንዳሉና የምርት አይነቶችን እንደሚገኙ መመልከት እንደቻሉ ተናግረው ከዚህ በፊት ከሀገር ውስጥ ምርት 6ከመቶ ብቻ ግዢ ይፈጸም የነበረው በአሁን ሰዓት ወደ 36 ከመቶ ማደጉን ጠቁመው ወደፊት የጤናውን ዘርፍ የህክምና ግብዓት አቅርቦትን ማሻሻል ከተቻለ የሀገር ውስጥ ምርት ፍላጎትና አቅርቦትን ማሳደግ እንደሚቻል አክለዋል፡፡
إظهار الكل...
👍 1 1
أرشيف المشاركات
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.