cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media

እሔ የቴሌግራም መንፈሳዊ ቻናላችን ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖታችን ምንማማርበት መንፈሳዊ መድረክ ነው። ለሌሎች ያጋሩ፣ አዳዲሶችም ተቀላቀሉ(join) አድርጉ።

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
2 319
Suscriptores
+724 horas
+587 días
+17830 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

01:05
Video unavailableShow in Telegram
"አማኝ ናት፥ ሀይማኖት አላት፥አባት ትወዳለች፥ታሪክ አላት" ----------------------------------------------- ሐሰተኛ ቆዳና ቆብ ለበስ የሰለጠኑ አጥፊዎችን ተጠቅመው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማፍዘዝ የሰሩት ተንኮል....👆
Mostrar todo...
2.71 MB
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪ የሆነው ሱራፌል አያና 8ኛ ክፍል ከተፈተኑ ከ85000 በላይ የአዲስ አበባ ተማሪዎች 99.9% በማምጣት 1ኛ ሆኗል! በታላቁ አባት በአቡነ ጎርጎርዮስ ስም የተሰየመው ትምህርት ቤት ትውልድን በስነምግባርና በእውቀት በመቅረፅ እያደረገ ያለው አስተዋፅኦ አንዱ ማሳያ ነው። ቅርንጫፎች ቢበዙና በኮሌጅ ደረጃም ማሰልጠን ቢጀመር ትውልዱ ያተርፋል!
Mostrar todo...
👏 10
የአብይ አህምድ አሊ ሠራዊት ሴት ተማሪዎችን በአውቶብስ ጭኖ በካምፕ ውስጥ አስገድዶ ደፈራቸው አደረ!! በፀጥታ አመራሮች ልዩ ስብሰባ የቦምብ ፍንዳታ!ተማሪዎች በወታደራዊ ካምፕ ምን ተደረጉ!16 July 2024 https://youtube.com/watch?v=h0kACO5X2bw&si=UIfCLdRka7OMzUjl
Mostrar todo...
በፀጥታ አመራሮች ልዩ ስብሰባ የቦምብ ፍንዳታ!ተማሪዎች በወታደራዊ ካምፕ ምን ተደረጉ!16 July 2024

በፀጥታ አመራሮች ልዩ ስብሰባ የቦምብ ፍንዳታ!/ተማሪዎች በወታደራዊ ካምፕ ምን ተደረጉ!?/ክምር ድንጋይ.! ደምቢያ.! ወልዲያ.! ቡሬ.! Ethio News_ኢትዮ ኒውስ ቻናል 2@ethionewschannel2 [email protected]

https://t.me/beletekassa

👆🏾👆🏾👆🏾👆🏾 ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች ከላይ የተለጠፈውን ዜና አድምጠን ለአፍታ ራሳችንን እንመርምር? ይህን መዕራፍ አንብበን ስንጨርስ የሚከተሉትን ጥያቄዎች እንጠይቅ? የት እንደቆምን እናስብ። እኛ ክርስቲያኖች ነን ስንል ምን እንደሆንን፥ በምን አይነት የቤተ መንግሥትና የቤተከ ክህነት እረኞች እንደምንመራ እናስብ፥ ከላይ የሰማችሁትን ተማሪዎችን በአውቶብስ ጭኖ ወታደር ካፕም እሰገብቶ የሚደፍር የአብይ አህምድ አሊን ሠራዊት እናስብ፥ ሠራዊቱ የሠለጠነበትን መንገድ እናስብ፥ ሠራዊቱ ይህን አድርጎ በዚህ አገር መኖር መቻሉን በማሰብ ሕዝብ ምን አይነት ስነ ልቦና ውስጥ እንደሚገኝም እናስብ። በመጨረሻም በራሳችን ላይ ምን መሆን አንደሚገባን፥ ምን ማድረግ እንዳለብን እንወስን። ምርጫችን በዘላለም ሕይወትና በዘላለም ሞት መካከል ብቻ ነውና አስበን እንወስን!! ( ፩) በአሕዛብ ስንኳ የሌለ ዝሙት፥ አገር አንዲጠብቅ እረኛ በተባለ መንግሥት የራስን ልጅ አፍኖ በካፕም ውስጥ በቡድን መድፈር የፈቀደ ሕሊና፥ መንግሥታዊ ሥርዓት፥ ይሀን ተሸክሞ የሚኖር ሕዝብ ምን አይንእ የሞራል ደረጃ ላዑእ ነው? (፪) ይህንን ነውር የሚሠሩትን የማያስወግድ መንግሥት፥ ቤተ እምነት ምን አይነት ደረጃ ላይ ይገኛል? (፫) ይህን ድርጊት የማያወግዝና በዘምታ “እየተመካከርን ነው፥ በጥበብ ቤተ ክእስቲያንን እያሻገርን ነው፥ ሕንጻ እየሠራን ነው ወአተ” የሚሉ ጳጳሳትና መነኮሳት፥ ካህናትና የሰበካ ጉባዔ መሪዎች “እምነት” በመጽሐፍት የተጻፈልንና እንከተለዋለን የምንለው የሐዋርያት ቀዳሚት እምነት ናት? (፬) ጥቂት አርⶄ ሊጡን ያቦካዋልና አዲስ ሊጥ ሁኑ የተባለውን የጌታን ትምህርት ወዴት ጥለነው ነው በመላው አገሪቱ የሰፈነውን መንግሥታዊና ቤተክህነታዊ ሁለንተናዊ ሙስና (የሞራል ውድቀት፥ የቁስ ስስትና ሌብነት፥ ዝሙት፥ ዘረኝነት፥ ማኅበራዊ መፋረስ) አገሩ ሁሉ በአዛባዊ እርⶄ ሲቦካ እረኞች ተስማምተው የሚኖሩት? እኛም በዝምታ የተዋጥነው? (፭) በዓላቶቻችን በቅንነትና በእውነት ቂጣ የሚደረጉና በእርግጠኝነት ከአሮጌ እርሾ በክፋትና በግፍ እርሾም አለመሆኑን ልናረጋግጥ እንችላለን? ወይስ እስከነ ሁለንተናዊ ሙስናችን በከበሮ፥ በያሬዳዊ ዜማ፥ በሞንታርቦ፥ በጧፍ ብርሃን፥ በአብለጭላጪ ልብስ ውስጥ የተሰወረ አሕዛባዊነት ነው? (፮)ከሴሰኞች ጋር እንዳትተባበሩ በመልእክቴ ጻፍሁላችሁ። ብሎ ቅዱሱ የመንፈስ ቅዱስ ማኅደር ቅዱስ ጳውሎስ ትዕዛዝ የተቀበልን እኛ አንዴት ከሴሰኛ ምንግሥትና ቤእምነት ጋር እንደዚህ ተባበርን? (፯) ከዚህ ዓለም ሳትወጡ የዓለምን ርኩሰትና ሴሰኝነት ተዋጉት፥ መስክሩበት (ቁጥር 10) ተብለን እንዴት ልጆቻችንን በጅምላ የሚደፈር የጦር ሠራዊት አሠልጥኖ የሚመራ የአብይ አህምድ አሊ አይነት በግብሩ ሰይጣንን የሚሰቀና ሰው አገራችንን አንዲመራ ፈቀድንለት? (፰) የውጨውስ አሕዛቢ ርኩሰት ከቁጥጥራችን ውጭ ሆኗል፥ በትምህርትና በተግሣጽ የማይመለስ መንግሥታዊ ሥርዓት ሆኗን፥ መፍትሔው በጦር መሣሪያና በሕዝባዊ እንቢተኝነት ብቻ የሚወጡት ነው ብንል ስንኳ፥ የጥመቀት ልጆች በቤኣችንና በሠራዊቱ ውስጥ ሴት ደፋሪና ነፍ ገዳይ ሲሆኑ መናገርና መከላከል ለምን ተሳነን? ======================================================= ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5፥1 በአጭር ቃል በእናንተ መካከል ዝሙት እንዳለ ይወራል የዚያም ዓይነት ዝሙት በአሕዛብስ እንኳ የማይገኝ ነው፥ የአባቱን ሚስት ያገባ ሰው ይኖራልና። 2 እናንተም ታብያችኋል፤ ይልቅስ እንድታዝኑ አይገባችሁምን? ይህን ሥራ የሠራው ከመካከላችሁ ይወገድ። 3-4 እኔ ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን፥ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን፥ 5 መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው። 6 መመካታችሁ መልካም አይደለም። ጥቂት እርሾ ሊጡን ሁሉ እንዲያቦካ አታውቁምን? 7 እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤ 8 ስለዚህ በቅንነትና በእውነት ቂጣ በዓልን እናድርግ እንጂ በአሮጌ እርሾ በክፋትና በግፍ እርሾም አይደለም። 9 ከሴሰኞች ጋር እንዳትተባበሩ በመልእክቴ ጻፍሁላችሁ። 10 በጠቅላላው የዚህን ዓለም ሴሰኞችን፥ ወይም ገንዘብን የሚመኙትን ነጣቂዎችንም፥ ወይም ጣዖትን የሚያመልኩትን አላልሁም፤ ይህስ ቢሆን ከዓለም ልትወጡ ይገባችሁ ነበር። 11 አሁን ግን ወንድሞች ከሚባሉት አንዱ ሴሰኛ ወይም ገንዘብን የሚመኝ ወይም ጣዖትን የሚያመልክ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካር ወይም ነጣቂ ቢሆን ከእርሱ ጋር እንዳትተባበሩ እጽፍላችኋለሁ፤ እንደነዚህ ካለው ጋር መብል እንኳን አትብሉ። 12 በውጭ ባሉ ሰዎች ላይ መፍረድ ምን አግዶኝ? በውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ እናንተ አትፈርዱምን? 13 በውጭ ባሉቱ ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል። ክፉውን ከመካከላችሁ አውጡት።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
እሄ ደግሞ ምን ሚሉት ልብስ ነው ጎርጎራ ላይ የለበሱት? ዳኒን ግን አብረው ፎቶ ያላስነሱት ንቀውት ነው? ለመሆኑ ዳኒ ሰሞኑን ከፎቶ እርቋል ምክንያቱ ግልፅ ባይሆንም
Mostrar todo...
ቤተ ክርስቲያን  ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ቤተሰብ ማለት ነው። ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ገነት ናት (ሳዊሮስ 259) ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቤተሰብ (Holy family) ማለት ነው ቤተ ክርስቲያን ቤተሰብ ናት። ለዚህ ነው በሰይጣን በዓለም የምትጠላው። የዓለሙ ገዢ ሰይጣን ነውና። መዳን የሚገኘው በቤተ ክርስቲያን ስለኾነ ነው። salivation and resumption.  ጠላት ቤተ ክርስቲያን ከተወለደች ከሁለት ሺኽ  ዓመት በፊት ጀምሮ  ይጣላታል። የዘንዶውን ራስ የቀጠቀጠው ማን እንደሆነ ያውቃል። “በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።” ዘፍ.3:15 የሴቲቱ ዘር ራሱን ይቀጠቅጣል። የሴቲቱ ዘር ማነው? እርሱም  ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ማንም የሰው ልጅ ከሴት ብቻ የተወለደ የለም። ኹሉም ሰው የሚወለደው ከሴትና ወንድ ነው። ከሴት ብቻ መወለድ ተፈጥሮ አይፈቅድም። ብቸኛው አስታራቂ እርሱ ነው። እናቱ ማርያም ናት አባቱ እግዚአብሔር አብ ነው።  ለምን ብቸኛ እሱ ብቻ ከሴት ብቻ ተወለደ ? ምክንያቱ ኃጢአት ወደ ሰው የገባው በወንድ  ዘር ነው። ሴት ዘር የላትም። ዘር seed የወንድ ነው። እኛ ኃጢአትን የወረስነው (inherited) ከአዳም ነው። ሔዋን ስትበላ እግዚአብሔር ምንም አላለም። “ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች” ይላል። ይኽ ማለት ግን ፈቀደላት ማለት አይደለም። ዘፍ.3:6 አዳም ሲበላ ግን እግዚአብሔር ተቆጣ። እሷ ናት ቀድማ የበላችው። “የተታለለም አዳም አይደለም፥ ሴቲቱ ግን ተታልላ በመተላለፍ ወደቀች” 1 ጢሞ.2:15 ከፊቴ ሂጂ አላላትም። አዳም ሲበላ ግን ለምን በላህ ተባለ። “እነርሱም ቀኑ በመሸ ጊዜ የእግዚአብሔርን የአምላክን ድምፅ ከገነት ውስጥ ሲመላለስ ሰሙ፤ አዳምና ሚስቱም ከእግዚአብሔር ከአምላክ ፊት በገነት ዛፎች መካከል ተሸሸጉ።  እግዚአብሔር አምላክም አዳምን ጠርቶ፦ ወዴት ነህ? አለው።  እርሱም አለ፦ በገነት ድምፅህን ሰማሁ፤ ዕራቁቴንም ስለ ሆንሁ ፈራሁ፥ ተሸሸግሁም።  እግዚአብሔርም አለው፦ ዕራቁትህን እንደ ሆንህ ማን ነገረህ? ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍ በውኑ በላህን?” ዘፍ.3:8 ኃጢአት ወደ አለም ገባን ከአዳም የወሰድነው ውርስ ኃጢአት “እኔ እኔ” የሚል ነው። me me me እኔ ነኝ I'm  እርሱ የዓለም መድኃኒት ነውና ከሴት መወለድ ግድ አለው። ሴት ዘር የላትም የአዳም በደል አያገኘውም። ጥንተ አብሶ በወንድ ዘር ውስጥ ነው። “ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ” ሮሜ.5:12 ለዚህ ነው ወልድ ከሴት ያለ ኃጢአት ፍጹም እግዚአብሔር ፍጹም ሰው ሆኖ የተወለደው። “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ” ገላ.4:4  ነገረ መለኮቱ ከሦስቱ አካል አንዱ በእመቤታችን ማሕጸን ሲያድር የሰውን ባሕርይ ለበሰ እንጂ የወንድን ዘር seed አይደለም። ለዚህ ነው ዘፍ.3:15 ከሴት ዘር የሚለው። የእባቡን ራስ የቀጠቀጠው። ጌታ በቃና ገሊላ ለዚህ ነው “አንቺ ሴት…” ያላትን የዘፍጥረት ትንቢት ፍጹም መሆኑን አሳየ።  ለዚህ ነው በሰይጣን የሚመራው ዓለም ቤተ ክርስቲያንን የሚጠላው። የሴቷ ዘር ነው ራሱን የቀጠቀጠው። ስሙም ኢየሱስ  ነው። እርሱ “እኔ ነኝ” I'm ነው። ሁሉን የፈጠረ፣ በሁሉም ሁሉም ነው።  ቤተ ክርስቲያን ቤተሰብ ናት። የቤተሰብ ድርሻ ምንድነው? እርስ በርስ መረዳዳት ማገዝ። አንዱ ለአንዱ መያያዝ መተማመን፣ እርስ በርስ መጣላት አይደለም። ዓለም በፍጹም ቤተሰባዊነትን አያበረታታም። ማኅበራዊ ሚዲያ TV ቤተሰብ አያበረታታም ግላዊነት individualism ነው። እኔ እኔ እኔ አንተ አንቺ ማለት ነው። ልጄቹን እዩ free ነህ ይላቸዋል ዓለም። የጌታ ትልቁ ትኩረት ቤተሰብ ነው። አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ቤተሰብ ናቸው። ባል  ልጅ ሲኖረው አባት ይሆናል። ቤተሰብ ቀዳሚ ነው።  ለራሳችን ብቻ ስንኖር ራስወዳድ እንሆናለን ። ከራስ ወዳድ ስንወጣ ሰይጣን ይጣላናል። ወጣቶች ተመልከቱ ማንም ጣልቃ እንዳይገባባቸው ይፈልጋሉ መጨረሻቸውን ግን ማየት ነው። የት አጠናቁቅ ?  ወደ ቤተሰብ እንድንመጣ እግዚአብሔር በመካከል ሊሆን ይገባልም ማንም አይበትነንም። ልጆች ወላጅጆችን አያገባሽም ካሉ ያበቃል። በራሴ እሰራለሁ ካሉ ልጆች ይጠፋሉ። ቤተሰብ ያበቃለታል። ከክርስቶስ ጋር መኖር። በሕይወት ክርስቶስ ያስፈልገናል። የሕይወት ምንጭ ነው source of life.  ምርጫ ሳይሆን የምንቀበለው እውነት ነው። ከዚያ ውጭ ሞትና ጨለማ ነው።  እንደ አንድ ቤተሰብ መኖር ነው። በእርሱ መልካም ቤተሰብ ነን። በአንድ ቀለም ጥሩ ስእል አይሳልም። ብዙ ቀለም በአንድ ሲጣመርና ሲሳል ነው የሚያምረው። ሕይወት ነው። አጽናኙ እንዲያጽናናን እርሱ ሁሌ ከእኛ ጋር ይኖራል።  መ/ር ንዋይ ካሳሁን
Mostrar todo...
❤️❤️❤️🙏🙏🙏 በብሬል የተጻፈ መዝገበ ጸሎት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተበረከተ። ሕፃን ሶሊያና እና ሕፃን ሄራን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለዓይነ ስውራን ለሆኑ አገልጋዮች እንዲሁም ምዕመናን የጸሎት መጽሐፍ በብሬል አዘጋጅተው በመቀየር ለቅድስት ቤተክርስቲያን በዛሬው እለት በሥጦታ አበረከቱ። ልበ ብርሃን ህጻናቱ ከኅዳር 19 እስከ ታኅሣስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ባለው አንድ ወር ጊዜ መጽሐፍ እንደጻፉ የተገለጸ ሲሆን በዛሬው እለት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሰጥተዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶ ተመርምሮ መጽሐፉን ከገመገመ በኋላ ለህጻናቱ የእውቅና ደብዳቤ ለህጻናቱ ተበርክቶላቸዋል። ቤተ ክርስቲያኑም በቀጣይ የአካል ጉዳተኛ አማኞች በመሰል ስራዎች ዙሪያ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ሶስቱ መንታ ህጻናቱ የፊታችን ሐሙስ ለህክምና ወደ ባንኮክ የሚያመሩ ሲሆን ሲመለሱ በድምቀት የምስጋና እና የምረቃ ዝግጅት እንደሚኖር ተጠቁሟል። Via ጌች ሀበሻ ሰላም አደራችሁ ውድ ኦርቶዶክሳዊይልን
Mostrar todo...
የመ/ር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ። ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት የዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ አዘጋጅ መ/ር ሥዩም ጉልላት  ሥርዓተ ቀብር ብፁዕ አቡነ አብርሃም  የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሰሜን ጎጃምና የባሕር ዳር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት  የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የመምህር ሥዩም ጉልላት ቤተሰቦችና ዘመዶች በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል። በሥርዓተ ቀብሩ ጸሎተ ፍትሐት የተከናወነ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ትምሕርተ ወንጌል ተሰጥቷል። በትምህርታቸውም አሽከርካሪዎችና እግረኞች በመንገድ አጠቃቀም ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል። መ/ር ሥዩም ጉልላት ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት የነበሩ ሲሆን በ 37 ዓመታቸው በመኪና አደጋ ሕይታቸው ማለፉ ይታወሳል። ©EOTC TV
Mostrar todo...
5
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.