es
Feedback
እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media

እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media

Ir al canal en Telegram

እሔ የቴሌግራም መንፈሳዊ ቻናላችን ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖታችን ምንማማርበት መንፈሳዊ መድረክ ነው። ለሌሎች ያጋሩ፣ አዳዲሶችም ተቀላቀሉ(join) አድርጉ።

Mostrar más
2 248
Suscriptores
-424 horas
-107 días
-2530 días
Atraer Suscriptores
agosto '26
agosto '26
+2
en 0 canales
julio '26
+52
en 5 canales
Get PRO
junio '26
+149
en 5 canales
Get PRO
mayo '26
+38
en 7 canales
Get PRO
abril '26
+35
en 4 canales
Get PRO
marzo '26
+29
en 3 canales
Get PRO
febrero '26
+19
en 3 canales
Get PRO
enero '26
+38
en 3 canales
Get PRO
diciembre '25
+60
en 4 canales
Get PRO
noviembre '25
+84
en 4 canales
Get PRO
octubre '25
+29
en 3 canales
Get PRO
septiembre '25
+32
en 3 canales
Get PRO
agosto '25
+39
en 3 canales
Get PRO
julio '25
+34
en 3 canales
Get PRO
junio '25
+47
en 4 canales
Get PRO
mayo '25
+45
en 4 canales
Get PRO
abril '25
+40
en 3 canales
Get PRO
marzo '25
+39
en 2 canales
Get PRO
febrero '25
+29
en 2 canales
Get PRO
enero '25
+43
en 3 canales
Get PRO
diciembre '24
+64
en 2 canales
Get PRO
noviembre '24
+90
en 4 canales
Get PRO
octubre '24
+87
en 2 canales
Get PRO
septiembre '24
+133
en 3 canales
Get PRO
agosto '24
+202
en 2 canales
Get PRO
julio '24
+273
en 2 canales
Get PRO
junio '24
+296
en 4 canales
Get PRO
mayo '24
+287
en 3 canales
Get PRO
abril '24
+220
en 4 canales
Get PRO
marzo '24
+298
en 3 canales
Get PRO
febrero '24
+229
en 2 canales
Get PRO
enero '24
+133
en 1 canales
Get PRO
diciembre '23
+100
en 3 canales
Get PRO
noviembre '23
+41
en 3 canales
Get PRO
octubre '23
+19
en 1 canales
Get PRO
septiembre '23
+69
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+9
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+30
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+19
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+30
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+66
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+52
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+441
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+174
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+48
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+488
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
01 agosto+2
Publicaciones del Canal
ጉዳያችን ከአጥፊው ወሃ'ብያ ጋር እንጂ ከሰላም ወዳዱ ሙስሊም ጋር አይደለም የምንለው ለዚህ ነው። በፎቶ የምትመለከቱት ኡስታዝ እነአህመዲን ጀበል በምክክር ኮሚሽኑ ያነሡት ሐሳብ ከሌሎች ጋር አያኗኑር
ጉዳያችን ከአጥፊው ወሃ'ብያ ጋር እንጂ ከሰላም ወዳዱ ሙስሊም ጋር አይደለም የምንለው ለዚህ ነው። በፎቶ የምትመለከቱት ኡስታዝ እነአህመዲን ጀበል በምክክር ኮሚሽኑ ያነሡት ሐሳብ ከሌሎች ጋር አያኗኑርም፤ ሀገርን ይበትናል፤ ክህደት ነው፤ ከሌሎች ጋር ተስማምተን እንድንኖር አያደርግም በማለቱ ከፍተኛ የሆነ ዘመቻ ተከፍቶበታል። የዘመቻውን ትእዛዝ የሰጠው ራሱ አህመዲን ጀበል ነው። ወሃ'ብያ የራሱን የአጥፊነት ሚና የማይጫወትለት ከሆነ ለሌላው ክብር የለውም። አክ'ራ'ri ካልሆንክለት ሙስሊም ብትሆንም ያሳድድሃል። ዓላማችን ልክ እንደ አባቶቻችን ተዋዶ ተከባብሮ መኖር ነው። እስልምናና ክርስትና በመከባበር እሴት ኢትዮጵያ በምትባል ዋርካ ሥር ኖሯል። የእኛም ሆነ የሀቀኛ ሙስሊሞች ፍላጎት ይኸው ነው። ጉዳያችን የክርስትናን እሴት አያሳየኝ ብሎ በተነሣው ወሃ'ብያ ላይ ነው። በስድብ ናዳ፣ በማስፈራሪያ፣ በዘመቻ፣ በልምምጥ፣ በማታለል ዝም ልንል አንችልም። ይዛችሁት የተነሣችሁት አደገኛ አካሄድ እስከሆነ ድረስ አካሄዳችሁን አስተካክላችሁ ወደቀልባችሁ እስከምትመለሱ እኛም ዝም አንልም።

2
የምክክር ኮሚሽን እና ተወያዮች በታሪክና ትርክት የሚመራ ከሆነ ከሕውሃትና ከኦነግ ትርክት መነሳት የለበትም። ከመሠረቱ ይነሳ
የምክክር ኮሚሽን እና ተወያዮች በታሪክና ትርክት የሚመራ ከሆነ ከሕውሃትና ከኦነግ ትርክት መነሳት የለበትም። ከመሠረቱ ይነሳ
135
3
የኢትዮጵያዊነት ጠላቶች የምክክር ጉባኤ ባለቤቶችና ተመካካሪዎች እነማናቸው? የሚመከርባቸውስ?
የኢትዮጵያዊነት ጠላቶች የምክክር ጉባኤ ባለቤቶችና ተመካካሪዎች እነማናቸው? የሚመከርባቸውስ?
138
4
ውብ አህያ ስለ ኦርቶዶክስ ያለው አመለካከት ይኽ ነው
ውብ አህያ ስለ ኦርቶዶክስ ያለው አመለካከት ይኽ ነው
211
5
❝ተክለሃይማኖት ሆይ የብርሃናት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በትዕግስት ለፈተናቸው ኩልያቶችህ ሰላም እላለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ ስግደትህ በማዕረገ መላእክት ደረጃ ነውና አከናውነህ የሠራሃት ጸሎትህ ባለ ዘ
❝ተክለሃይማኖት ሆይ የብርሃናት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በትዕግስት ለፈተናቸው ኩልያቶችህ ሰላም እላለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ ስግደትህ በማዕረገ መላእክት ደረጃ ነውና አከናውነህ የሠራሃት ጸሎትህ ባለ ዘመኔ ሁሉ ከጦርነት ከጽኑ መከራ ሁሉ ጠባቂ ትሁነኝ።❞ለኩልያቲከ  መልክዓ ተክለሃይማኖት https://c.org/QnvbXPW6LF ❝ In the last three months, more than 144 people have been slaughered, believers massacred in their homes and Churches razed in a surge of ethnic and religious attacks.❞ Hoollie McKay
182
6
የኢትዮጵያ እንደ ሃገር የምትታወቅባቸውን ሁሉ ለማጥፋት ያለመው ምክክር በሀገራዊ የምክክር መድረኩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ አንዳንድ ጽንፈኛና ሀገር ጠል ቡድኖች የሚያነሷቸው ሃሳቦች አጠቃላይ አካታችነ
የኢትዮጵያ እንደ ሃገር የምትታወቅባቸውን ሁሉ ለማጥፋት ያለመው ምክክር በሀገራዊ የምክክር መድረኩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ አንዳንድ ጽንፈኛና ሀገር ጠል ቡድኖች የሚያነሷቸው ሃሳቦች አጠቃላይ አካታችነትን ማዕከል ያደረጉ ሳይሆኑ፣ በተለይ የኢትዮጵያዊ እሴቶችንና ቅርሶችን በይፋ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱበት ነው። እነዚህ አካላት የራሳቸውን መፍትሔ ሰጪ አማራጭ ሃሳብ ማቅረብ ባልቻሉበት ሁኔታ፣ ለምሳሌ "የዘመን አቆጣጠሩ ሃይማኖታዊ ይዘት ስላለው ይቀየር" የሚል አጀንዳ ያነሳሉ። ሆኖም ግን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን ሃይማኖታዊ መነሻ የሌለውና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያገኘ የዘመን አቆጣጠር አለ ወይ? ለሚለው ምላሽ የላቸውም። በመሆኑም፣ ሂደቱ ሁሉንም ዜጎችና ሃይማኖቶች በእኩልነት የሚያስተናግድ እውነተኛ ሀገራዊ ምክክር ከመሆን ይልቅ፣ መንግሥት ሂደቱን አካታች ለማስመሰልና የራሱን አጀንዳ ለማስፈጸም በካድሬዎችና በአክራሪ ሙስሊሞች የሚመራ መድረክ አድርጎታል። የሕዝብና የሀገር ሀብት በማባከን ለ35 ቀናት እየተካሄደ ያለው ይህ ምክክር፣ የዜጎችን እውነተኛ ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ የመንግሥትን ፍላጎት የሚያስፈጽሙ ካድሬዎችንና ሃገር ጠል አክራሪ አካላትን አጀንዳ ማስፈጸሚያ እየሆነ ነው። ስምዐ ተዋሕዶ
213
7
Sin texto...
1 070
8
ስለ ትንሹ የኢትዮጵያው አይኤስ ቅርንጫፍ ብዙ ሰው አልገባውም። ስለ አህመዲን ጀበል ስንጽፍ ግለሰባዊ ጉዳይ የሚመስለው ብዙ የዋህ አለ። ስለ ወሃ'ብያ ስንጽፍ የሙስሊም ጥ'la'ቻ የሚመስለው አለ። ስ
ስለ ትንሹ የኢትዮጵያው አይኤስ ቅርንጫፍ ብዙ ሰው አልገባውም። ስለ አህመዲን ጀበል ስንጽፍ ግለሰባዊ ጉዳይ የሚመስለው ብዙ የዋህ አለ። ስለ ወሃ'ብያ ስንጽፍ የሙስሊም ጥ'la'ቻ የሚመስለው አለ። ስለ አይኤስ መልካም ጎን ከነገርከኝ ስለነአህመዲን ቡድን መልካም ጎን እነግርሃለው። የነአህመዲን ቡድን ማለት አማርኛ ተናጋሪ አይኤስ ነው። እነሶርያን፣ ሊቢያን እና የመንን ያፈራረሰው አይኤስ ኢትዮጵያን እንዲያፈርሱ የወከላቸው ናቸው። አሁን ያለውን የቤተ ክርስቲያንን መገፋት አጋጣሚ ተጠቅመው ኦርቶዶክሳዊነት ሕልውናው አይደለም መታሰቢያው ከኢትዮጵያ እንዲጠፋ ያለ ዕረፍት የሚሠሩ ናቸው። 24 ሰአት ያለ ዕረፍት ወጣቶችን እየመለመሉ እያሠለጠኑ ነው። በመንግሥት መዋቅር የራሳቸውን ሰው እየሰገሰጉ ነው። በምክክር ኮሚሽኑ ከዘመን አቆጣጠራችን ጀምሮ እስከ መጠሪያ ቦታዎች ድረስ ታሪክ ለማጥፋት እየተከራከሩ ነው። እመኑኝ፤ ይህ ቡድን አጋጣሚውን ተጠቅሞ በለስ ከቀናው ጭምብል ለብሶ ታጥቆ አላህ ወአክበር እያለ አንገት መቁረጥ ይጀምራል። አይኤስ በኢትዮጵያ ፊት ለፊት የመብት ተሟጋች መስሎ መጥቶል፤ ከጀርባ ያደራጃል። አጋጣሚውን ሲያገኝ ከአርሲ አዲስ አበባ ለመግባት ግማሽ ቀን አይወስድበትም።
224
9
የዛሬ 90 ዓመት! ረፋድ አካባቢ... ክብድ ያለ ቀን ነበር፡፡ አደባባይ ላይ የተሰበሰበው የአዲስ አበባ ህዝብ የሚሆነውን ነገር ለማየት በጭንቀት ባህር ውስጥ ሆኖ ይጠባበቃል... • ወዲያው አንድ ቁመታቸው ረዘም፣ ፊታቸው ዘለግ ያለ መልካቸው ጠየም ያለና አዋቂነታቸው ከገፃቸው ላይ የሚነበብ ሰው... በጭቃ የተለወሰ ጥቁር የጵጵስና ካባቸውን እንደለበሱ በከበቧቸው ፈርጣማ ወታደሮች እየተገፉ ከህዝቡ ፊትለፊት ቆሙ... • ደቂቃዎች ነጎዱ... አንዳች አስፈሪ ድባብ ሁኔታውን ለማየት በተሰበሰበው ህዝብ መሀል ነግሷል... በወታደሮች ተከበው የመጡት የጳጳስ ልብስ የለበሱት ቆራጥ ሰውዬ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሟቸውም ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው አጠገባቸው ቆሞ የነበረውን ወታደር በትህትና ጠየቁት። እንዲቀመጡ ፈቀደላቸው... • ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩ የሞት ፍርዳቸው ለህዝቡ ተነበበ... ሰውዬው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለእርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየፀለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያውም የሞታቸው ሰዓት መድረሱን አውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። ምንም አይነት ፍርሃት በፊት ገፃቸው ላይ አይነበብም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣልያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥና ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ይታይ ነበር... •Jemal Abdulaziz ብዙም ሳይቆይ በአቅራቢያቸው ከነበረው ግንብ አጠገብ ጀርባቸውን ወደ ህዝቡ አዙረው እንዲቀመጡ ተደረገ... ከዚያ በኋላ 8 የታጠቁ ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተጠንቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ «ተኩስ» በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም የታጠቁትን ጥይት በኢትዮጵያዊዩ ጳጳስ ላይ አዘነቡ፡፡ ንፁህ ደም ከጳጳሱ ገላ ላይ እየተንዠቀዠቀ ወደ መሬት ፈሰሰ... • በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ... ይህ የግፍ ግድያ ልክ በዛሬዋ እለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ከ89 አመታት በፊት በጨካኞቹ የኢጣሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያዊዩ አርበኛ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ ተፈፀመ... ትረካ: Dagmawi Dagmawi
237
10
+1
Sin texto...
211
11
‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተ
‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት፡፡ ወዲያው ወታደሮቸ በሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው፡፡ ይህ እንደሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ። ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት ‹‹በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል›› አለኝ፡፡ ‹‹እንዴት?›› ብለው ‹‹አላየህም ሲያጨበጭብ?›› አለኝ፡፡ ‹‹ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል›› አልኩት፡፡ ‹‹እንዴት?›› ቢለኝ እጄን አጨብጭቤ አሳየሁት፡፡" አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ በቦታው ሆነው የተከታተሉት ሙሴ ፓይላክን የተባሉ ግለሰብ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ለጳውሎስ ኞኞ ከነገሩት የተወሰደ፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ/ም
185
12
ነፍሰ ይማር የኔታ (ፕሮፌሰር) መስፍን ወልደማርያም፣ የታላቁን ሰማዕት የአቡነ ጴጥሮስን ፍቅር፣ ትዕግሥት፣ ጽናት፣ የእምነት ተጋድሎቸውንና የመንፈስ ልእልናቸውን መሠረት በማድረግ ‘‘ኢትዮጵያ ከየት ወደየት?!’’ በሚል መጽሐፋቸው የሰማዕቱን የአቡነ ጴጥሮስን የፀረ-ፋሽስት ተጋድሎ በጴጥሮሳዊነት መንፈስ እንዲህ አመስጥረውት ነበር። አቡነ ጴጥሮስ እንደሌሎቹ ሁሉ ኢጣልያ ኢትዮጵያን የወረረችው «የእግዚአብሔር ፈቃድሆኖ ነው»፤ በማለት የኢጣልያ ወታደር የኢትዮጵያን ሕዝብ አበሳውን ያሳየው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው በማለት ሊገብሩና የተደላደለ ኑሮ ለመኖር ይችሉ ነበር። አቡነ ጴጥሮስ የራሳቸውንና የሀገራቸውን ጉዳይ ወደ እግዚአብሔር ሳይወረውሩ ሓላፊነታቸውን ሳይሸሹ «እምቢኝ አሻፈረኝ!» አሉ። በእምቢተኛነታቸውም የኢጣልያን ክርስቲያንነትና ሥልጡንነት ፈተና ውስጥ ከተቱት። በእምቢተኛነታቸው ለእግዚአብሔር ለአምላከ ፅድቅ ያላቸውን ፍቅርና ክብር፤ ለሃይማኖታቸው ያላቸውን ፅናት፤ ለጨበጡት መስቀል ለመስዋዕትነት ምልክቱ ፣ያላቸውን ስሜት ለሀገራቸውና ለወገናቸውም ያላቸውን ታማኝነት አረጋገጡ፤ በመትረየስ ተደበደቡ። ዛሬ በዚህ ድርጊት ኢትዮጵያ ትኮራለች፤ ኢጣልያ ታፍራለች። ጴጥሮሳዊነት የምለው የአቡነ ጴጥሮስን ዓይነት የእምቢተኛነት መንፈስ ነው። ጴጥሮሳዊነት በእግዚአብሔር አምላክ ፅድቅነት (ፅድቅ እውነት ማለት ነው) አምኖ የራስንም ሓላፊነት ከነውጤቱ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ብሎ መቀበል ነው። ጴጥሮሳዊነት በመሠረቱ መንፈሳዊነት በመሆኑ የሚመካበት ኃይል መንፈሳዊ እንጂ አካላዊ ወይም ጠመንጃ አይደለም። የጴጥሮሳዊነትም ዓላማ አስፈላጊ ከሆነ ለእምነቱ ለመሞት እንጂ ለመግደል አይደለም። ሰው ሲገደል የሚቀረው በድን ሬሣ ነው። ገዳዩም ከዚያ ከበድን ሬሣ የተለየ፤ ወይም ከተጠቀመበት የመግደያ መሣሪያ የማይለይ ነው። በአካል ደረጃ ገዳይና የተገዳዩ ሬሣ ቢመሳሰሉም፣ በመንፈስ ደረጃ የማይገናኙ ናቸው። እውነትን እገድላለሁ ብሎ የሰውን ሕይወት የሚያጠፋ በድን፣ እውነትና የሰው ደም እንዳስደነበረውና እንዳቃዠው ከበድንነት ወደ በድንነት ይተላለፋል። ለእውነት የተገደለው ግን እውነትን በሕይወቱ መስዋዕትነት አዳብሮና አፋፍቶ ያልፋል። መግደል የአእምሮ በሽተኞችና የልጆች ጨዋታ ነው። ለመሞት መዘጋጀትና ለእውነትና ለእምነት መሞት ግን ወኔን ይጠይቃል፤ መንፈሳዊ ወኔን። የኢትዮጵያ ባህል ለጠመንጃ የሚሰጠው ክብር ከራሱ ከሰውነት ክብሩ ጋር የተያያዘ ነው። ጠመንጃ ኃይል ይሆናል፤ አያስጠቃም። ገዳይ ጀግና ተብሎ ይከበራል። ሠርቶ ከመክበር ያንድ መኳንንት ሎሌ ሆኖ ጠመንጃ መሸከም ያስከብር ነበር፤ አሁንም አልቀረም። ይህንን ክፉና የማይጠቅም ባህል በጴጥሮሳዊነት መለወጥ ያስፈልገናል። በጠመንጃ ኃይል ከመተማመን በመንፈሳችን ኃይል መተማመኑ ወደ ተሻለ የእድገት ጎዳና ያመራናል። ለጠመንጃ የማይበገር መንፈስ በመሀከላችን ሲዳብር ከጠመንጃ ይልቅ በጽሑፍ፤ ከጥይት ይልቅ በቃላት ቅራኔዎቻችንን ማለሳለሱ ወደ ሥልጣኔ ፈር ውስጥ ያስገባናል። እምነታችን የቱንም ያህል ቢለያይ፣ ሀሳባችን ቢራራቅና መግባባት የሚያስቸግር ቢሆንም ሀሳቦቻችን ይጋጩ፣ ይፋጩ እንጂ እኛ ጎራዴ መዝዘን ወይም ጠመንጃ አጉርሰን፣ ከአእምሮና ከመንፈስ ደረጃ ወደ እንሰሳነት ደረጃ ወርደን ስንጋደል እምነቶቻችንና አሳቦቻችን ያደፍጣሉ እንጂ እንደማይሞቱ ይግባን። ጴጥሮሳዊነት በአቡነ ጴጥሮስ መስዋዕትነት ላይ የተመሠረተ የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ነው። አቡነ ጴጥሮስ ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው፣ የተሰውበትም ዋና ምክንያት የኢትዮጵያ ነፃነት በመሆኑ ፣ጴጥሮሳዊነትን ኢትዮጵያዊነት እንበለው እንጂ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የሰው ልጆች ታሪክ በየሀገሩ የሚያሳየው የሰው መንፈስ ነው። ስለዚህም ጴጥሮሳዊነት ዓለምአቀፋዊነት ባሕርይም አለው። እውነትን ክዶ በውሸት ከመኖር ለእውነት ሞቶ እውነትን ሕያው ማድረግ የመንፈስ ዕርገት ነው። እንዲህ ዓይነቱ የመንፈስ ዕርገት የሚቀጥለውን ትውልድ ከእንሰሳት ደረጃ ወደላቀ የሰውነት ደረጃ ያነሣዋል። ከዚህ የተሻለ ውርስ አይኖርም። ጠመንጃ የያዘ ሁል ጊዜም እንዲያሸንፈን መንፈሳችን ከተዳከመ ለጠመንጃ መድኃኒቱ ጠመንጃን ማንሣት እየሆነ እስከዛሬ እንደነበረው ወደፊትም ይቀጥላል። ይህንን የቁልቁለት መንገድ በጴጥሮሳዊነት ልናቆመውና ወደዕርገት እንዲያመራን ማድረግ እንችላለን። የእያንዳንዳችንን ውሳኔ የሚጠይቅ ነው። የዛሬ 90 አመት ሐምሌ 22/1928 ዓም ተሰዉ ትውልድ ለዘላለም ሲዘክራቸው ይኖራል #ሼር
186
13
+1
Sin texto...
190
14
አርበኞች መሞትን ማን አስተማራቸው ታላቁ ጴጥሮስ ነው ባርኮ የሰጣቸው ጴጥሮሳዊነት ያሸንፋል!!! የባንዶች መንፈስ አሸንፎ አያውቅም። የኢትዮጵያም የክርስትናም ጠላቶች አዲሶች አይደሉም ደጋግመው ሞክረ
አርበኞች መሞትን ማን አስተማራቸው ታላቁ ጴጥሮስ ነው ባርኮ የሰጣቸው ጴጥሮሳዊነት ያሸንፋል!!! የባንዶች መንፈስ አሸንፎ አያውቅም። የኢትዮጵያም የክርስትናም ጠላቶች አዲሶች አይደሉም ደጋግመው ሞክረው አፈር በልተዋል። ባንዶች አቡነ ጴጥሮስን ገረፉት። አላንበረከኩትም!! ሁሌም ማባበያ አለ፤ አቡነ ጴጥሮስ ጋር ማባበያው አልሰራም!!! ምክንያቱም ክርስትና በመከራ ውስጥ ማበብ ነዋ! ሀገርንም ቤተክርስቲያንንም ከጥፋት የሚታደገው ጴጥሮሳዊነት ነው። እውነተኛ እረኝነትን አክብሮ መሞት ክብር ነው። ባንዳ አተላ መሸከም መብቱ ነው። ጴጥሮሳዊነት ግን ለክብር መሞት ነው፤ ለክብር መውደቅ ነው፤ ለእውነት መሰዋት ነው፤ ጴጥሮሳዊነት አርበኝነት ነው። አርበኝነት ይለምልም!!! መ/ታ ብርሃኑ ተክለያሬድ
219
15
በምክክር ጉባኤው ላይ ከቀረቡት መነጋገሪያ ጉዳዮች መካከል አንዱ የቀን መቁጠሪያ ካላንደር ነበር። አንዳንዶች ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው የኢትዮጵያ የቀን መቁጠሪያ ፣ የወራትና የቀና
በምክክር ጉባኤው ላይ ከቀረቡት መነጋገሪያ ጉዳዮች መካከል አንዱ የቀን መቁጠሪያ ካላንደር ነበር። አንዳንዶች ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው የኢትዮጵያ የቀን መቁጠሪያ ፣ የወራትና የቀናት ስያሜ እንዲሁም የአዲስ ዓመት መቀየሪያ ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመጣ ነውና እነዚህ ነገሮች ይቀየሩልን ➠ ዓመተ ምህረት የሚለው ከቀን መቁጠሪያ ላይ ይሰረዝ ➠ በሚዲያዎች ላይ ከክርስቶስ ልደት በፊት በዃላ የሚሉ አገላለጾች ይሰረዙ ➠ በአፋር በሱማሌ በኦሮሚያ እና በሌሎች አካባቢዎች እስላማዊውን የሂጂራ ዘመን አቆጣጠርን እንከተል ➠ የመንግስትና የንግድ ቦታዎች ላይ እስላማዊ የካላንደር አቆጣጠር እንጠቀም ➠ የወራትና የቀናት ስያሜዎች ለውጥ ይደረግ፤ አሁን ያሉት የወራት እና የቀናት ስያሜዎች ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር የተያያዙ በመሆናቸው እንዲቀየሩ ➠ አዲስ ዓመት መስከረም 1 ላይ መሆኑ ቀርቶ በሌላ ቀን እንዲሆን (ይህም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጋር ስለሚያዬዝ ይቀየር) ➠ ሃይማኖትን መሰረት ያላደረገ ካላንደር እንከተል (አሁን ያለው የክርስቶስ ልደት መሰረት ያደረገው ካላንደር ይዘረዝ) ይህ የመጨረሻው ሃሳብ ያስቃል፤ ሐይማኖትን መሰረት ያላደረገ ካላንደር የትኛው ነው? እንደ ሰሜን ኮሪያ የአምባገነን መሪያቸውን የልደት ቀን መሰረት አድርገው እንደሚቆጥሩት ዓይነት ማለት ነው? 😅 የቱን ካላንደር ትጠቀሙት? አረቦቹ ራሳቸው እንደ UAE የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ያሉ አገሮች ጭምር በግሪጎሪያን (የክርስቶስን ልደት መሰረት ባደረገው) ካላንደር ነው የሚቆጥሩት እኮ! ማርያማዊት ሄኖክ ለሜሳ
205
16
ይኸ በሐሰት ቫይረስ የተበከለ ሰውየ የማይለው ነገር የለም፡፡ ይኸ የአእምሮ በሽተኛ አንድም ቀን የራሱን ፎቶ ሳይለጥፍ ጽሑፍ ጽፎ አያውቅም፡፡ ወይ ፊቱ አያምር ወይ ንግግሩ አያምር፡፡ ሁለቱንም ደግሞ
ይኸ በሐሰት ቫይረስ የተበከለ ሰውየ የማይለው ነገር የለም፡፡ ይኸ የአእምሮ በሽተኛ አንድም ቀን የራሱን ፎቶ ሳይለጥፍ ጽሑፍ ጽፎ አያውቅም፡፡ ወይ ፊቱ አያምር ወይ ንግግሩ አያምር፡፡ ሁለቱንም ደግሞ ይለጥፋቸዋል፡፡ በነገራችን ላይ ''እስልምና ፎቶና ምስል መስቀልን ይቃወማል'' ይሉሃል ይኸ በሽተኛ የራሱን ፎቶ ፌስቡክ ላይ በመስቀል የሚወዳደረው ግን የለም፡፡ ከውብአህያ አንድም ሰው 'ሐራም የሆነ ነገር እያደረክ ነው' ያለው አልተገኘም፡፡ ውብአህያ ለእስልምና ጭንቀት የለውማ፡፡ ከዚያ ውጭ የሚጽፈው ነገር ትርጉም የማይሰጥ ነገር ግን የብጥብጥ ጠላ መሆኑን የሚጠፋው የለም፡፡ እሱና ደቀ መዛሙርቱ፣ 'በዓለም ላይ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ሐሰትን ደጋግሞ በመናገር ጥቅማችንን ማስጠበቅ እንችላለን፣ ዐዲስ ታሪክ ማንበር እንችላለን፣ ዐዲስ ኢትዮጵያ መፍጠር እንችላለን' ብለው ቀን ከሌት ድካም ላይ ናቸው፡፡ ሐሰት ደግሞ በቅንጣት እውነት ድርምስምሷ ነው የሚወጣው፡፡ ይኸ ድሪቷቸው ሁሉ ከውነት ፊት እንደ ጢስ በኖ ይጠፋል፡፡ ነገር ግን ይኸ ወንጀለኛ በየትኛውም ዐለም ያሉ አምሳያዎቹ እየታደኑ ወኅኒ ቤት እንደሚወርዱት ሁሉ ውሎና አዳሩ ማረሚያ ቤት መሆን የነበረበት ሰው ነው፡፡ ዛሬ ያለው ሥርዓት ለጊዜው በመፈልፈያነት እያገለገለው ነው፡፡ ነገ ግን በተናገራትና ከተገኘባቸው የጥፋት ጀርባዎች ሁሉ ታድኖ ይጠያቃታል፡፡ ይኸው ነው፡፡
224
17
ሐምሌ 22 - “የእውነተኛ ጳጳሳት ቀን” ቢሆን ምን አለበት? የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በቅንነትና በታማኝነት ያገለገሉ ሁለት ታላላቅ አባቶች፣ አቡነ ጴጥሮስ እና አቡነ ጎርጎርዮስ ያረፉት ሐምሌ 22 ቀን ነው። ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ በፋሽስት ጣሊያን ግፍ የተገደሉት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ሲሆን፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ደግሞ በመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ሐምሌ 22 ቀን 1982 ዓ.ም ነበር። ለትውልዱ አርአያ ሊሆኑ የሚችሉትን የነዚህን የሁለቱን ጳጳሳት ዕረፍት ምክንያት በማድረግ፣ ሐምሌ 22 ቀን “የእውነተኛ ጳጳሳት ቀን” ተብሎ ቢከበርና ቢዘከር መልካም ነው። የጳጳስነትን ዓላማ ተረድተው በጎቻቸውን ከተኩላ መንጋጋ የጠበቁትን እውነተኛ እረኞች፣ መጻሕፍትን በመጻፍና ምዕመናንን በማስተማር ያለፉትን አባቶች መዘከር ይገባል። ከጳጳሳት መካከል በሃይማኖት ምnefeቅና ጎርፍ ያልተወሰዱትን ማሰብ ግድ ይለናል። የጳጳሳት ታሪክ እየተነሳ ከሕይወታቸው የምንማርበት መርሐ ግብር ቢዘጋጅ ምን አለበት? ይህ መርሐ ግብር ለወቅቱ አባቶችም “ዓላማችሁን ተረድታችሁ ብታገለግሉን እንዲህ እንዘክራችኋለን” የሚል መልእክት ያስተላልፋል። በአንጻሩ በጎሳ እየከፋፈሉ የሚያቆስሉንን፣ ቤተ ክርስቲያንን በመከፋፈል የሚገዘግዙትን ግን ከነመፈጠራቸው ማስታወስ እንደማንፈልግ የምንገልጽበት መድረክ መዘጋጀት አይገባውም? ካስታወስናቸውም ማስታወሻቸው እንደ ንስጥሮስና መሰሎቹ ለታሪክ ተወቃሽነት ብቻ ሊሆን ይችላል። በአጭሩ ሐምሌ 22 ቀን እውነተኛ ጳጳሳት የሚዘከሩበት ዕለት ቢሆን ምን አለበት? በቅንነት ከታሰበበት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ ከግቢ ጉባኤያትና ከማኅበራት ጀምሮ ቀስ በቀስ ቀኑ በቤተ ክህነት አካላት ዕውቅና እንዲያገኝ መሥራት ይቻላል። ለነገሩ ቤተ ክህነቱ ‘የእውነተኛ ጳጳሳት ቀን’ እንዲኖር ይፈልጋል? የሚለው ጥያቄ ራሱ ከባድ ቢሆንም፣ እኛ ግን የምንችለውን ያህል እንሞክር። እርስዎስ ምን ይላሉ?
332
18
+1
Sin texto...
211
19
ውሸት ረጅም እርቀት እንደማትሄድ ከነዚ ሁለት ኡስታዞች ተማሩ 😁 ኡስታዝ አብዱል ጀሊል የተባለ ወገናችን ከ2_3 ወር በፌት እስልምና በኢትዮጵያ ከቅደመ ክርስቶስ አስከዛሬ የሚል ተረት ተረት መፅሀፍ
ውሸት ረጅም እርቀት እንደማትሄድ ከነዚ ሁለት ኡስታዞች ተማሩ 😁 ኡስታዝ አብዱል ጀሊል የተባለ ወገናችን ከ2_3 ወር በፌት እስልምና በኢትዮጵያ ከቅደመ ክርስቶስ አስከዛሬ የሚል ተረት ተረት መፅሀፍ ማስመረቁና በብዙዎች ሲሸጥ ነበረ መፅሀፉ እኛም የመሀመድ አስተምህሮንና እስልምናን እንዴት ገደል እንደሚከተው አሳይተናቹ ነበር 😁በደንብ ሸቅሎ ሳይጨርስ አህመዲን ጀበል እስልምና ወደ ኢትዮጵያ መቼ ገባ በሚል ጉዳይ አንድ ፓለቲካ ይዘት ያለው ፅሁፍ አጋርቶ ነበር ብዙ ሙገሳ ና ሼር ያገኘ ነበር ዳሩ ወገናችን ሌላኛውን ኡስታዙን መፅሀፍ ገደል የሚከት ነበረ🤣 እሱም እስልምና በኢትዮጵያ የገባው በ7 ኛው ክፍለ ዘመን ነው የሚል ነበረ !! ውሸታቸው እረጅም እርቀት እንደማይሄድ ከነዚ ኡስታዞች መረዳት ትችላላችሁ የትኛው ነው ትክክል የሚለውም አጅግ ተጠባቂ ደርቢ ነው 😁 ለማንኛውም ወገኖች እኛ እያለን የምትቀጥፉለት እስልምና አይኖርም !!
235
20
#የሀዘን_መግለጫ_ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዕውቀት ብርሃን፣ የቅድስና ምሰሶ የነበሩት አባ ኪዳነማሪያም መዝገቡ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ✝️​ አባ ኪዳነማሪያም በቤተክርስ
#የሀዘን_መግለጫ_ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዕውቀት ብርሃን፣ የቅድስና ምሰሶ የነበሩት አባ ኪዳነማሪያም መዝገቡ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ✝️​ አባ ኪዳነማሪያም በቤተክርስቲያን ትምህርት በጥልቀት የተመረመሩ፣ ጥልቅ አዋቂ ነበሩ። ሕይወታቸውን በሙሉ ለወንጌል አገልግሎትና ለትውልድ ማስተማር የሰጡ ታላቅ አባት ናቸው። ✝️​ ከታላቁ የዘጌ ገዳም እስከ ቅድስት ዳጋ እስጢፋኖስ በነበራቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ፣ በትሕትናቸውና በፀሎታቸው በብዙዎች ዘንድ የተወደዱና የተከበሩ ነበሩ። ​✝️ በባሕር ዳር ከተማ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው፣ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በመጨረሻው የቅድስና ዕረፍታቸውን አግኝተዋል። ✝️ የአባታችን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በጣና ሐይቅ ላይ በምትገኘው ታሪካዊቷ የደሴት ገዳም ዳጋ እስጢፋኖስ ይፈጸማል። ✝️​ ነገ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት በባሕር ዳር ከተማ የባሕር ትራንስፖርት (ባርካ መውጫ) የአባታችን አስከሬን ሽኝት ይደረጋል። ✝️በመሆኑም መላው ምዕመናን፣ ወዳጅ ዘመዶች በዚህ ሽኝት ላይ ከጠዋቱ 12:30 በመገኘት የመጨረሻ ምስጋናችሁን በሽኝት እንድታቀርቡ ጥሪ ቀርቧል። ✝️​አባታችን የሠሩት በጎ ሥራ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ታስቦላቸው መንግስተ ሰማያትን ያዋርሳቸው። ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመድ ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን።
239