es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 084
Suscriptores
+524 horas
+107 días
+530 días
Archivo de publicaciones
አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ለከተራና ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ። የተከበራችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና ለመድ
+1
አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ለከተራና ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ። የተከበራችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። ከጥምቀት በዓል በዋናነት ትህትናን፣ ይቅርታን እና ታዛዥነት እንማራለን። ስለዚህ በዓሉን ስናከብር ሆነ ከበዓሉ በኋላ እነዚህን ሦስት ነገሮችን በተሰማራንበት መስክ ሁሉ ማሰብና መተግበር ይጠበቅብናል። በዓሉ ከኃይማኖታዊ በዓልነቱ ባሻገር የአብሮነታችን መገለጫ ከመሆኑም በተጨማሪ የሀገርና የህዝብ ሃብት እንዲሁም የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ የተመዘገበ ስለሆነ በዓሉን ስናከብር ሀገራዊ ገፅታን በሚያሳድግ መልኩ ማክብር ይገባናል። ህዝበ ክርስቲያኑም በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማብላት በማጠጣት እንዲሁም ከሁሉም ህብረተሰብ ጋር ሠላምና አብሮነትን በሚያጎለብት መልኩ ማክበር ያስፈልጋል። በድጋሚ እንኳን ለከተራና ለጥምቀት በዓል በሠላም አደረሳችሁ። አደረሰን መልካም በዓል።                    አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ

በ2017 ዓ.ም በአስተዳደሩ ለሚደረገው የቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራ ውድድር ከተቋምና ከአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች ለውድድሩ የተመለመሉ ተወዳዳሪ አሰልጣኝ መምህራኖች፣ ሰልጣኞች፣ ኢንተርፕራይዞችና ለአጠቃላይ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን ስለ ውድድሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ፡፡ በዚህም ውድድሩ በዘርፉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ መንግስት ባወጣው ፖሊሲና ስትራቴጂ መሰረት ለአሰልጣኞችና ሰልጣኞች፤ ለመምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን በአስተዳደሩና በአገር አቀፍ ደረጃ በየአመቱ በማወዳደር ለማበረታታትና ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ ነው፡፡ በተጨማሪ በአስተዳደሩ ያለውን የቴክኖሎጂ እድገት ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ የተያዘውን የቴክኖሎጂ መቅዳትና ማሸጋገር ሂደት ለማቀላጠፍ እንዲያስችል የቴክኒክና ሙያ መር የገበያ ትስስር የሚፈጥር ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ የካቲት እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ መጋቢት ላይ ውድድሩ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ከጋንቤላ አፔኖ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ከደቡብ ምዕራብ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተወጣጣ ልኡካን ቡድን ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልምድ ልውውጥ አደረ፡፡ ኮሌጆቹ በነበራቸው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የላቀ አፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችም በኮሌጁ ዲኖች አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረጉት ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃን መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያደረገው ያለው እንቅስቃሴ አስደናቂ መሆኑን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ምሳሌ መሆን የሚችልበት የአፈፃፀም ደረጃ ላይ እንደሚገኝም በውይይታቸው ወቅት አንስተዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኙትን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡባቸው ኮሌጆች ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 9/2017 ዓ.ም

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት መደበኛ ስራ የ6ወር አፈጻጸምና የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም ለኮሌጁ የቦርድ አባላት በዛሬው እለት ቀረበ፡፡ የኮሌጁ
+5
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት መደበኛ ስራ የ6ወር አፈጻጸምና የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም ለኮሌጁ የቦርድ አባላት በዛሬው እለት ቀረበ፡፡ የኮሌጁን ሪፖርት ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን በአቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ የኮሌጁ ከዝግጅ ት ምእራፍ እሰከ ትግበራ ምእራፍ ድረስ የተሰሩ ስራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን የገለጹ ሲሆን አያይዘውም የቴክኒክና ሙያ አዲሱን እሳቤ ከተቋሙ አሁናዊ ሁኔታ ጋር ያለበትን ሁኔታ ያስረዱ ሲሆን በቀጣይም የሚሰሩ ስራዎችን ለቦርድ አባላት አቅርበዋል፡፡በመቀጠልም የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም በፕሮጀክቶ M&E specialist በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቧል፡፡ ከሪፖርቶቹ በኋላም በቀረበው የእቅድ አፈጻጸም ላይ የቦርድ አባላቶች የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ የብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቦርድ ሰብሳቢ በኮሌጁ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የስራ መመሪያ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢንቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ኢንቲትዩቱ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢንቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ኢንቲትዩቱ ጋር በመተባበር እየሰራቸው ከሚገኙ ተግባራቶች በተጨማሪ ዘላቂነት ባለው መልኩ ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን እንዲረዳ ሁለቱ ተቋማት የመግባቢያ ስምምነቱን ተፈራርመዋል:: የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የኮሌጁ ዲን እቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የስራ አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ለገሰ ሲሆኑ ስምምነቱም በአቅም ግንባታ ስልጠናዎች፣በጥናቶች እንዲሁም በማማከር ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያለመ ሲሆን በቀጣይ በመግባቢያ ስምምነቱ መሰረት በማድረግ ወደ ትግበራ እንደሚገባም ትግልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 9/2017 ዓ.ም

በኮሌጅ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን የተቄም ውስጥ ምዘና አዘገጃጀት ላይ ስልጠና በመሰጠት ተገለጸ በማድረግ ለማዘጋጀት የተሰጠ ግንዛቤ ሲሆን ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የ2017 የስልጠና ዘመን በፌደራል ደረጃ በማዕከል በሁሉም ሙያዎች ለተሰሩ የሥርዓተ ትምህርቶች እና የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያዎች  በማዘጋጀት የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት ለማሻሻል ከሚያስችሉትና  ሚያግዙት የተለያዩ ሰነዶችን በማዘጋጀትና በማሰልጠን ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሃያ የስልጠና ፕሮግራሞች ላይ ከየትምህርት ክፍሉ ለተውጣጡ አሰልጣኞችና አዘጋጅ አሰልጣኞች የተቋም ውስጥ ምዘና መሳሪያዎችን ለማዘገጀት  ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የስልጠና አስተባባሪዎች እና ከግል ኮሌጆች  ለተውጣጡ አሰልጣኞች የምዘና መሳሪያዎች  አዘገጃጀት ስልጠና በመስጠት በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የ2016 ዓ.ም ቅድመ ሞዴል የ2017 ዓ.ም ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች በኢንተርፕርነርሽፕ እና በቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ላይ ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በተጋበዙ መምህራን ሰልጠና ተሰጠ። በዚህም ስልጠና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግና ያላቸውን ልምድ እርስ በእርሳቸው እንዲለዋወጡ ለቀጣይም የዕድገት ደረጃ ለማብቃት አቅማቸውን የሚገነባ ይሆናል። በመሆኑም ኢንተርፕራይዞቹ በቀጣይ በሞዴል መመዘኛ መሰረት ተመዝነው ከዛ ውስጥ የተሻለ የሚባሉትን ምርጥ ተሞክሮ የሚቀመር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ታዳጊ መካከለኛ በየአመቱ የሚሸጋገሩትን በመስፈርቱ መሰረት የመለየት ስራ በቀጣይ ተጠናክሮ ይሰራል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 8/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በግብርና ዘርፍ በከተማ ግብርና ዶሮ ዕርባታ ስራ ላይ የተሰማሩ የከተማና የገጠር ኢንተርፕራይዞች በጋራ በማቀናጀት ልምዳቸውን እንዲለዋወጡና ስለ ዘርፉ ሞያዊ የሆነ ስልጠና ተሰጠ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ በከተማና በገጠር ተደራጅተው በስራ ላይ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች የተለያዩ መንግስታዊ ድጋፎች ይሰጣል ከነዚህም ውስጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ምችችት፣ የብድር ምችችት እና አቅም የሚገነቡ ስልጠናዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ ለሚገኙ በዶሮ ዕርባታ ስራ ላይ ለተሰማሩ በከተማም በገጠርም ለተሰማሩ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ሞያዊ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል በቀጣይም ደግሞ የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ሌሎች ያጋጠሟቸው ችግሮች ላይ በመወያየት መፍታት የሚቻልበት አግባብ ላይ መግባባት ተፈጥሯል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ በሚገኘው የብስራተ ገብርኤል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::  የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር ተቀራርቦ በጋራ ለመስራት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው አለትም በብስራተ ገብርኤል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ግንዛቤን የመፍጠር ስራ ሰርቷል:: የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለት/ቤቱ ተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት ሀላፊና የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በመድረኩም ተማሪዎቹ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላቸውን የተዛባ አመለካከት የሚቀርፍና የቴክኒክና ሙያ ነባራዊ ሁኔታን በግልፅ በሚያሳይ መልኩ በመተንተን ዘርፉ ለተማሪዎቹ የሚያስገኘውን ምቹ አጋጣሚ ሰፋ ባለ ማብራሪያ ገለፃ ያደረጉላቸው ሲሆን ተማሪዎች የነገ መዳረሻችውን ከዚሁ ትኩረት ሰተው በጥንቃቄ መምረጥ እንደሚገባቸውም ምክር ለግሰዋል:: እንዲሁም በአዲሱ ፖሊሲ መሰረት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎችንም አያይዘው የሚሰለጥኑ በመሆኑ በዘርፉ የሚሰጡትን የስልጠና አይነቶች ቀድመው በግልፅ እንዲረዷቸው በማድረግ ካላቸው ዝንባሌ ጋር የሚጣጣም የስልጠና አይነትን ምርጫቸው እንዲያደርጉ የሚረዳቸውን ግንዛቤ ማግኘትም ችለዋል:: በተጨማሪም ከት/ቤቱ ጋር የጋራ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም እንዲሁም በት/ቤቱ የቴክኒክና ሙያ ክበብ በማቋቋም ተማሪዎቹ ላይ ቀጣይነት ያለው ሰፊ የግንዛቤ ስራ እንደሚሰራ የተገለፀ ሲሆን በተጨማሪም የቴክኖሎጂ ፈጠራ አቅም ያላቸውን ተማሪዎች በመለየት ከኮሌጁ የሚያስፈልገውን ድጋፍ እንዲያገኙ የሚደረግ መሆኑም ተገልፇል:: የግንዛቤ ማስጨበጫው በት/ቤቱ ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም ለ92 ሴት እና ለ80 ወንድ በድምሩ 172 ለሚሆኑ የት/ቤቱ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ግንዛቤ የተፈጠረበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም

በድሬደዋ አስተዳደር ከተለያዩ ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የአስተዳደሩን ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን የ2017 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ፤ በቢሮው እንዲሁም በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የተከናወነ የ2017 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ቀርቦም ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል። በመጨረሻም የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ የቀረበው ሪፖርት አቀራረቡንና የተከናወኑ ስራዎችን አድንቀው በቀጣይ ሊተኮርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገባቸውን ጉዳዮች ሀሳብና አስተያየቶች አክለው አቅጣጫ ሰጥተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት እና ኮሌጁን እንቅ
+6
የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት እና ኮሌጁን እንቅስቃሴ ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ኮሌጁ በቀጣይ የባቡር ምህንድስና እና የICT የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ለድሬዳዋ መመስረት ምክንያት የሆነውን የባቡር እና ICT መሰረተ ልማቶችን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና አሁን ያሉትን ባለሞያዎች የሚረከቡ ባለሞያዎችን እያፈራ የሚገኝ ተቋም ነው ብለዋል፡፡ የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት ልኡክ ቡድኑን የመሩት የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ብሩክ አለማየሁ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አራያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለመላው ሃገራችን የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ያገኙትንም ልምድ በአካባቢያቸው ተግባራዊ እንደሚያደርጉት ተናግረዋል፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የፕሮጀክቶ አፈጸጸም እንዲሁም የግንባታ ሂደቱን እስካሁን የደረሰበት ደረጃ በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቧል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ