Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 071
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት መደበኛ ስራ የ6ወር አፈጻጸምና የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም ለኮሌጁ የቦርድ አባላት በዛሬው እለት ቀረበ፡፡
የኮሌጁን ሪፖርት ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን በአቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ የኮሌጁ ከዝግጅ ት ምእራፍ እሰከ ትግበራ ምእራፍ ድረስ የተሰሩ ስራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን የገለጹ ሲሆን አያይዘውም የቴክኒክና ሙያ አዲሱን እሳቤ ከተቋሙ አሁናዊ ሁኔታ ጋር ያለበትን ሁኔታ ያስረዱ ሲሆን በቀጣይም የሚሰሩ ስራዎችን ለቦርድ አባላት አቅርበዋል፡፡በመቀጠልም የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የSIFA ፕሮጀክት አፈጻጸም በፕሮጀክቶ M&E specialist በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቧል፡፡
ከሪፖርቶቹ በኋላም በቀረበው የእቅድ አፈጻጸም ላይ የቦርድ አባላቶች የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በቦርዱ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ የብልጽግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቦርድ ሰብሳቢ በኮሌጁ እንዲሁም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የስራ መመሪያ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኘው የስራ አመራር ኢንቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ኢንቲትዩቱ ጋር በመተባበር እየሰራቸው ከሚገኙ ተግባራቶች በተጨማሪ ዘላቂነት ባለው መልኩ ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን እንዲረዳ ሁለቱ ተቋማት የመግባቢያ ስምምነቱን ተፈራርመዋል::
የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የኮሌጁ ዲን እቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የስራ አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ለገሰ ሲሆኑ ስምምነቱም በአቅም ግንባታ ስልጠናዎች፣በጥናቶች እንዲሁም በማማከር ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያለመ ሲሆን በቀጣይ በመግባቢያ ስምምነቱ መሰረት በማድረግ ወደ ትግበራ እንደሚገባም ትግልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥር 9/2017 ዓ.ም
በኮሌጅ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን የተቄም ውስጥ ምዘና አዘገጃጀት ላይ ስልጠና በመሰጠት ተገለጸ በማድረግ ለማዘጋጀት የተሰጠ ግንዛቤ ሲሆን ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የ2017 የስልጠና ዘመን በፌደራል ደረጃ በማዕከል በሁሉም ሙያዎች ለተሰሩ የሥርዓተ ትምህርቶች እና የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያዎች በማዘጋጀት የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት ለማሻሻል ከሚያስችሉትና ሚያግዙት የተለያዩ ሰነዶችን በማዘጋጀትና በማሰልጠን ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ሃያ የስልጠና ፕሮግራሞች ላይ ከየትምህርት ክፍሉ ለተውጣጡ አሰልጣኞችና አዘጋጅ አሰልጣኞች የተቋም ውስጥ ምዘና መሳሪያዎችን ለማዘገጀት ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የስልጠና አስተባባሪዎች እና ከግል ኮሌጆች ለተውጣጡ አሰልጣኞች የምዘና መሳሪያዎች አዘገጃጀት ስልጠና በመስጠት በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የ2016 ዓ.ም ቅድመ ሞዴል የ2017 ዓ.ም ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች በኢንተርፕርነርሽፕ እና በቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ላይ ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በተጋበዙ መምህራን ሰልጠና ተሰጠ።
በዚህም ስልጠና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግና ያላቸውን ልምድ እርስ በእርሳቸው እንዲለዋወጡ ለቀጣይም የዕድገት ደረጃ ለማብቃት አቅማቸውን የሚገነባ ይሆናል።
በመሆኑም ኢንተርፕራይዞቹ በቀጣይ በሞዴል መመዘኛ መሰረት ተመዝነው ከዛ ውስጥ የተሻለ የሚባሉትን ምርጥ ተሞክሮ የሚቀመር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ታዳጊ መካከለኛ በየአመቱ የሚሸጋገሩትን በመስፈርቱ መሰረት የመለየት ስራ በቀጣይ ተጠናክሮ ይሰራል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 8/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በግብርና ዘርፍ በከተማ ግብርና ዶሮ ዕርባታ ስራ ላይ የተሰማሩ የከተማና የገጠር ኢንተርፕራይዞች በጋራ በማቀናጀት ልምዳቸውን እንዲለዋወጡና ስለ ዘርፉ ሞያዊ የሆነ ስልጠና ተሰጠ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ በከተማና በገጠር ተደራጅተው በስራ ላይ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች የተለያዩ መንግስታዊ ድጋፎች ይሰጣል ከነዚህም ውስጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ምችችት፣ የብድር ምችችት እና አቅም የሚገነቡ ስልጠናዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በዚህም በአስተዳደሩ ለሚገኙ በዶሮ ዕርባታ ስራ ላይ ለተሰማሩ በከተማም በገጠርም ለተሰማሩ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ሞያዊ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል በቀጣይም ደግሞ የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ሌሎች ያጋጠሟቸው ችግሮች ላይ በመወያየት መፍታት የሚቻልበት አግባብ ላይ መግባባት ተፈጥሯል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ በሚገኘው የብስራተ ገብርኤል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር ተቀራርቦ በጋራ ለመስራት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የሚያከናውናቸውን ተግባራት አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው አለትም በብስራተ ገብርኤል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ግንዛቤን የመፍጠር ስራ ሰርቷል::
የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለት/ቤቱ ተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት ሀላፊና የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በመድረኩም ተማሪዎቹ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላቸውን የተዛባ አመለካከት የሚቀርፍና የቴክኒክና ሙያ ነባራዊ ሁኔታን በግልፅ በሚያሳይ መልኩ በመተንተን ዘርፉ ለተማሪዎቹ የሚያስገኘውን ምቹ አጋጣሚ ሰፋ ባለ ማብራሪያ ገለፃ ያደረጉላቸው ሲሆን ተማሪዎች የነገ መዳረሻችውን ከዚሁ ትኩረት ሰተው በጥንቃቄ መምረጥ እንደሚገባቸውም ምክር ለግሰዋል::
እንዲሁም በአዲሱ ፖሊሲ መሰረት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎችንም አያይዘው የሚሰለጥኑ በመሆኑ በዘርፉ የሚሰጡትን የስልጠና አይነቶች ቀድመው በግልፅ እንዲረዷቸው በማድረግ ካላቸው ዝንባሌ ጋር የሚጣጣም የስልጠና አይነትን ምርጫቸው እንዲያደርጉ የሚረዳቸውን ግንዛቤ ማግኘትም ችለዋል::
በተጨማሪም ከት/ቤቱ ጋር የጋራ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም እንዲሁም በት/ቤቱ የቴክኒክና ሙያ ክበብ በማቋቋም ተማሪዎቹ ላይ ቀጣይነት ያለው ሰፊ የግንዛቤ ስራ እንደሚሰራ የተገለፀ ሲሆን በተጨማሪም የቴክኖሎጂ ፈጠራ አቅም ያላቸውን ተማሪዎች በመለየት ከኮሌጁ የሚያስፈልገውን ድጋፍ እንዲያገኙ የሚደረግ መሆኑም ተገልፇል::
የግንዛቤ ማስጨበጫው በት/ቤቱ ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም ለ92 ሴት እና ለ80 ወንድ በድምሩ 172 ለሚሆኑ የት/ቤቱ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ግንዛቤ የተፈጠረበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም
በድሬደዋ አስተዳደር ከተለያዩ ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የአስተዳደሩን ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን የ2017 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ፤
በቢሮው እንዲሁም በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የተከናወነ የ2017 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ቀርቦም ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።
በመጨረሻም የሱፐርቪዥን ቡድን አባላቱ የቀረበው ሪፖርት አቀራረቡንና የተከናወኑ ስራዎችን አድንቀው በቀጣይ ሊተኮርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገባቸውን ጉዳዮች ሀሳብና አስተያየቶች አክለው አቅጣጫ ሰጥተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት እና ኮሌጁን እንቅስቃሴ ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ኮሌጁ በቀጣይ የባቡር ምህንድስና እና የICT የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ለድሬዳዋ መመስረት ምክንያት የሆነውን የባቡር እና ICT መሰረተ ልማቶችን በቴክኖሎጂ ለማዘመንና አሁን ያሉትን ባለሞያዎች የሚረከቡ ባለሞያዎችን እያፈራ የሚገኝ ተቋም ነው ብለዋል፡፡
የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት ልኡክ ቡድኑን የመሩት የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ብሩክ አለማየሁ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አራያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለመላው ሃገራችን የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ያገኙትንም ልምድ በአካባቢያቸው ተግባራዊ እንደሚያደርጉት ተናግረዋል፡፡
በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና የፕሮጀክቶ አፈጸጸም እንዲሁም የግንባታ ሂደቱን እስካሁን የደረሰበት ደረጃ በአቶ መሳይ ጥላሁን ቀርቧል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የ2016/17 የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያና የዕውቅና እና የምስጋና መረሃ- ግብር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃርን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደሩ የመንግስትና የፓርቲ አመራሮች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ አባገዳዎችና ኡጋዞች እና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት ተካሂዷል።
በመርሀ-ግብሩም የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀ -ግብሩ ሲያከናውናቸው ለቆየው መልካም ተግባራት በቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በኩል የዋንጫ ሽልማት እና ሰርተፍኬት ተረክቧል።
ጥር 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
የአሰልጣኝ መምህራንን አቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው መሰጠታቸው የስልጠና ጥራትን ለማምጣት እንደ ሚጠቅም ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን የስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅና ስልጠናዎችን በተገቢው መንገድ መስጠት እንዲቻል በተለያዩ ጊዜያት የአሰልጣኝ መምህራንን አቅም የመገንባታ ስራዎች እየተሰሩ እንዳለ የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ ገለጹ፡፡
ም/ዲኑ በባቡር ምህንድስና ዘርፍ ስር የሚደገፉ የአውቶሞቲቭ፣የኤሌክትሪካል እና የማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል አሰልጣኝ መምህራንን አቅም ለማጎልበት በEASTRIP ፕሮጀክት በጀት አመቻችነት በፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የስልጠና ማእከል ስልጠናዎችን እየወሰዱ ያሉ መምህራንን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የአሰልጣኝ መምህራንን አቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው መሰጠታቸው የስልጠና ጥራትን ለማምጣት እንደ ሚጠቅም ተናግረዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ለሚያደርጉ የግልና የመንግስት አሰልጣኝ መምህራንና ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት መድረክ አዘጋጀ።
በአስተዳደሩ የሚገኙ ሁለቱ መንግስታዊ ኮሌጆች እንዲሁም በዚህ አመት ድጋፍ ማድረግ የጀመሩት የግል ኮሌጆች በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማዕቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችንና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪግ ኢንደስትሪዎችን የምርትና ምራታማነት ለማሻሻልና ብቁ የሆነ የሰዉ ሃይል ለማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ ለማስቻል ድጋፍ እንደሚሰጡ ይታወቃል።
በዚህም ቢሮው ይህን መድረክ ሲያዘጋጀ ለአሰልጣኝ መምህራኑና ለባለድርሻ አካላት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ጽንሰ ሃሳብ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ከዚህ በፊት በነበሩ ድጋፍ አሰጣጥ፣ ምዘና እና የዕድገት ሽግግር ጋር በተያያዘም ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ለቀጣይ የመፍትሔ አማራጮች የተጠቆሙ ሲሆን ከግልና ከመንግስት ኮሌጆች የመጡ አሰልጣኝ መምህራን ትውውቅ የፈጠሩበትና በቅንጅት ወደ ስራ እንዲገቡ የተደረገበት መድረክ ሆኗል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ::
በዛሬው ዕለት በአስተዳደሩ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ ለሰልጣኞች የሰርተፍኬት መስጠትና የተመደቡበትን ኢንደስትሪ ዕጣ የማውጣት ፕሮግራም ተካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት ቢሮው በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑና በዚህም የመጀመሪያ ዙር ለአርባ አምስት ቀናት በተሰጠ ስልጠና ሰላሳ አንድ ሰልጣኞችን ማሰልጠን መቻሉን ተናግረዋል::
የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴ/ሙ/ት/ስ ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ይህ የተሰጠው ስልጠና ኮሌጆች ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰው ሃይል በማፍራቱ ረገድ በቅንጅት እየተሰሩ ከሚገኙ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑን አንስተው ሰልጣኞች በስልጠናው የቀሰሙትን በስራው አለም በተግባር ውጤት እንዲያመጡ አሳስበዋል።
የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም በበኩላቸው በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ ተመርቀው ስራ ለሚፈልጉ ወጣቶች የስራ ዕድል ከመፈጠሩ ጎን ለጎን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ጋር በተያያዘ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን ክፍተት የመሙላቱ ተግባር በተመሳሳይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በቅንጅት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
