1 076
Suscriptores
+224 horas
+37 días
+230 días
Archivo de publicaciones
በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ::
በዛሬው ዕለት በአስተዳደሩ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ ለሰልጣኞች የሰርተፍኬት መስጠትና የተመደቡበትን ኢንደስትሪ ዕጣ የማውጣት ፕሮግራም ተካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት ቢሮው በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ባለሙያዎች እጥረት ለመቅረፍ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑና በዚህም የመጀመሪያ ዙር ለአርባ አምስት ቀናት በተሰጠ ስልጠና ሰላሳ አንድ ሰልጣኞችን ማሰልጠን መቻሉን ተናግረዋል::
የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴ/ሙ/ት/ስ ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ይህ የተሰጠው ስልጠና ኮሌጆች ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የሰው ሃይል በማፍራቱ ረገድ በቅንጅት እየተሰሩ ከሚገኙ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑን አንስተው ሰልጣኞች በስልጠናው የቀሰሙትን በስራው አለም በተግባር ውጤት እንዲያመጡ አሳስበዋል።
የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሀመድ ኢብራሂም በበኩላቸው በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ ተመርቀው ስራ ለሚፈልጉ ወጣቶች የስራ ዕድል ከመፈጠሩ ጎን ለጎን የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ጋር በተያያዘ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን ክፍተት የመሙላቱ ተግባር በተመሳሳይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብርና በቅንጅት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#ዜና በምስራቅ አየር ምድብ ዋና አዛዥ ኮረኔል ደረጀ እንዲሁም የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረገ፡፡
በመስክ ምልከታው ወቅት በመገኘትና ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉት የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ ኃላፊው በንግግራቸውም ከትምህርተና ስልጠናው በዘለለ ኮሌጁ በአስተዳደር ደረጃ የተጣለበትን ትልልቅ ኃላፊነቶች በመቀበል ያለምንም እንከን ከግብ እያደረሰ ያለ ትልቅ ተቋም ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በኮሌጁ ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም የተለያዩ እቅዶችን አዘጋጅትን ወደ ተግባር የገባን ሲሆን ለአስተዳደሩ ብሎም ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል ብሎም ለምስራቁ የአፍሪካ ክፍል የሚተርፍ አቅምን በመፍጠር ከሁሉም ተቋማት ጋር በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በባለፉት ጊዜያት በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተር ፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪዎችን የተለዋጭ ምርት ማምረት እና በዲጂታላይዜሽን አተገባበር ላይ ኮሌጁ ያለውን ልምድና ተሞክሮ የኮሌጅ ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ለልኡክ ቡድኑ አስረድተዋል፡፡
ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል እንደ መሆኑ መጠን ያለውን አቅም የአካባቢው ወጣቶች በአግባቡ መጠቀም እንዲችሉ ሁሉም ተቋማት ከኮሌጁ ጋር በጋራ ሊሰሩ አቅሙንም ሊጠቀሙ ይገባል ያሉት ልኡክ ቡድኑን የመሩት በምስራቅ አየር ምድብ ዋና አዛዥ ኮረኔል ደረጀ ሲሆኑ ዋና አዛዡ አያይዘውም ኮሌጁ ያለበትን ደረጃ በበቂ ሁኔታ መረዳት እንደቻሉ እንዲሁም ከትምህርትና ስልጠና ባሻገር ከኢንዱስትሪዎች እና አለም አቀፍ ተቋማት ጋር ባለው ትስስር አመርቂ ውጤት እያስመዘገባ እንዳለ መረዳት ችለናል ይህን ተሞክሮ ደግሞ ለሌሎች ተቋማት ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት አዲሱን እሳቤ እና የጥራት ስራ አመራር ስርዓት መሠረት አድርጎ በተከለሰው እቅድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ::
በመድረኩ አዲስ በተከለሰው እቅድ ዙሪያ ተሻሽለው የመጡና አዲስ በተጨመሩ የአዲሱ እሳቤዎች እና የጥራት ስራ አመራር ስርዓት መነሻ በሆነው እቅድ ላይ ለትምህርትና ስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል::
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በዘርፉ አዲሱ እሳቤዎች ዓላማ ከሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ልማት አኳያ ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት የታለመውን ጥራቱን የጠበቅና የተሟላ ስልጠና መስጠት እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑም ተገልፇል::
በመድረኩ በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሳታፊዎች በቀረበው የተከለሰ እቅድ ዙሪያ ያላቸውን አስተያየትና ምክረ-ሃሳብ በማቅረብ ሰፊ ውይይትም ተደርጎበታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 6/2017 ዓ.ም
በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን አቅም ለማሳደግ ለሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው የOSH( Occupational Safety & Health) የሙያ ደህንነት ስልጠና ተጠናቀቀ::
በአስተዳደሩ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ በኢንጂነሪንግ እና በጤናው ዘርፍ የመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን ትኩረት ያደረጎ በተቀመጠ በመስፈርት መሰረት ተመልምለው የመጡ ወጣቶችን በማሰልጠን ወደ ኢንዱስትሪው ለማሰማራት በማሰብ በመጀመርያ ዙር 31 ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለአርባ አምስት ቀናት ማሰልጠን ተችሏል::
በዛሬው ዕለትም ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የነበራቸውን አፈጻጸም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም በቢሮው የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተገኝተው ተመልክዋል።
የቢሮ ኃላፊው እንደተናገሩት ሰልጣኞች በወሰዱት የLife skills ስልጠናን ጨምሮ በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባር፣የንድፍ ሃሳብን ጨምሮ ኢንዱስትሪዎች ላይ የትብብር ስልጠናዎችን መውሰዳቸውና ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ላይ በዘርፉ የሚታየውን የሰው ሃይል እጥረት የሚሞሉ ይሆናል::
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችን አቅም ለማሳደግ ለሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው የOSH( Occupational Safety & Health) የሙያ ደህንነት ስልጠና ተጠናቀቀ::
በአስተዳደሩ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር (OSH) ስልጠና በአስተዳደሩ ከየቀበሌው የተወጣጡ በኢንጂነሪንግ እና በጤናው ዘርፍ የመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን ትኩረት ያደረጎ በተቀመጠ በመስፈርት መሰረት ተመልምለው የመጡ ወጣቶችን በማሰልጠን ወደ ኢንዱስትሪው ለማሰማራት በማሰብ በመጀመርያ ዙር 31 ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለአርባ አምስት ቀናት ማሰልጠን ተችሏል::
በዛሬው ዕለትም ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የነበራቸውን አፈጻጸም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም በቢሮው የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተገኝተው ተመልክዋል።
የቢሮ ኃላፊው እንደተናገሩት ሰልጣኞች በወሰዱት የLife skills ስልጠናን ጨምሮ በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባር፣የንድፍ ሃሳብን ጨምሮ ኢንዱስትሪዎች ላይ የትብብር ስልጠናዎችን መውሰዳቸውና ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ላይ በዘርፉ የሚታየውን የሰው ሃይል እጥረት የሚሞሉ ይሆናል::
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
መገኘት የነበረበት
አባላት ብዛት ወ 127 ሴ 47 ድ 174
የተገኘ ወ 103 ሴ 38 ድ 141
ያልተገኘ ወ 24 ሴ 9 ድ 33
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የመንግስት ሰራተኞች የብልፅግና ፓርቲ መሠረታዊ ድርጅት የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።
በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የመሠረታዊ ድርጅቱ የፓርቲ ስራዎች አንዲሁም የስነ ምግባርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን የስድስት ወር የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እና የቀጣይ ስድስት ወር ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን በመጨረሻም አዳዲስ እጩ አባላት ቀርበው በጉባኤው በማጽደቅ ኮንፈረንሱ ተጠናቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሶማሊ ላንድ የመጡ ከ 45 በላይ ሰልጣኞችን በፍሽን ዲዛይን እንዲሁም በ ሆቴል ቱሪዝም ዘርፍ የሰለጠኑ ሰልጣኞችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ ለዛሬ የምርቃት ቀን የደረሳችሁ ሰልጣኖች ለድሬዳዋ ከተማችን አባሳደር ናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ አያይዘውም ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ወጣቶችም ማድረስ ይኖርብናል፡፡በቀጣይም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች የተለያዩ ሰልጣኞችን በመቀበል የምስራቅ አፍሪካን በትምህርትና ስልጠናው የማዋሃድ ስራን የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሠለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድ፣ ጅቡቲ፣ከኬንያ፣ከታንዛንያ እንዲሁም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ጋር በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት ስልጠናችሁን አጠናቃችሁ ለምርቃት የበቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለዚህ ውህደት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡ከዚህ ኮሌጅ ስልጠናችሁን ጨርሳችሁ ወደ ሀገራችሁ ስትሄዱ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያገኛችሁትን ስልጠና ሌሎች ወጣቶች እንዲያገኙ የአባሳደርነት ሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
በምርቃቱ መርሃ ግብር ላይ በስራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኞች ልማት ዳይሬክተር አቶ ጀማል እንዲሁም የኮሌጁ ም/ዲን አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ የተገኙ ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ለምርቃት በመድረሳቸው የተሰማቸውን ልባዊ ደስታ ገልጸዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 3/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሶማሊ ላንድ የመጡ ከ 45 በላይ ሰልጣኞችን በፍሽን ዲዛይን እንዲሁም በ ሆቴል ቱሪዝም ዘርፍ የሰለጠኑ ሰልጣኞችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ ለዛሬ የምርቃት ቀን የደረሳችሁ ሰልጣኖች ለድሬዳዋ ከተማችን አባሳደር ናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ አያይዘውም ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካ ወጣቶችም ማድረስ ይኖርብናል፡፡በቀጣይም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች የተለያዩ ሰልጣኞችን በመቀበል የምስራቅ አፍሪካን በትምህርትና ስልጠናው የማዋሃድ ስራን የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሠለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድ፣ ጅቡቲ፣ከኬንያ፣ከታንዛንያ እንዲሁም ከሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ጋር በትምህርትና ስልጠና ለማዋሃድ በንቃት ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት ስልጠናችሁን አጠናቃችሁ ለምርቃት የበቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ለዚህ ውህደት ማሳያ ናችሁ ብለዋል፡፡ከዚህ ኮሌጅ ስልጠናችሁን ጨርሳችሁ ወደ ሀገራችሁ ስትሄዱ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያገኛችሁትን ስልጠና ሌሎች ወጣቶች እንዲያገኙ የአባሳደርነት ሚናችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
በምርቃቱ መርሃ ግብር ላይ በስራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኞች ልማት ዳይሬክተር አቶ ጀማል እንዲሁም የኮሌጁ ም/ዲን አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ የተገኙ ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ለምርቃት በመድረሳቸው የተሰማቸውን ልባዊ ደስታ ገልጸዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 3/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
