The Remedial Tutorials
Ir al canal en Telegram
To register,use @the_remedial_tutorial_bot For any question contact us @Remedial_admins
Mostrar más2 352
Suscriptores
-224 horas
-237 días
-5930 días
Archivo de publicaciones
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!
በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇
https://student.ethernet.edu.et/
የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።
Telegram | TikTok | YouTube | Instagram
Repost from Tikvah-University
+4
#Remedial_Complaint
ዛሬ ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል።
በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ 'Disqualified' የተባለባቸው መሆኑን በመግለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ሌሎች በርካታ ተማሪዎች ደግሞ የሂሳብ ትምህርት ውጤታቸው ብቻ 'Disqualified' እንደሚል ገልፀዋል።
የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "በፈተና ወቅት ምንም አይነት የስነ-ምግባር ግድፈት አልፈፀንም" በማለት በእርማት ወቅት ቴክኒካል ችግር ከነበረ እንዲታይላቸው በትህትና ጠይቀዋል።
ቅሬታችሁን በኦንላይን አስገቡ 👇
https://result.ethernet.edu.et
ከውጤታችሁ ስር መጨረሻ ላይ ያለውን Submit Complaint የሚለውን ይጫኑ፣ Select a category የሚለውን ይክፈቱ፣ My result disqualified without reason የሚለውን ይምረጡ፣ አጠር ያለ መግለጫ ይፃፉ፣ የስልክ ቁጥርዎን ይሙሉ እና Submit Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታዎን ያስገቡ።
የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ 250 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (5 የትምህርት አይነቶች) እና 200 ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (4 የትምህርት አይነቶች) መሆኑ ታውቋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎቹ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ የሚሰጡትን ምላሽ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርሳችሁ ይሆናል።
@tikvahuniversity
#RemedialResult
በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል።
https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል።
@tikvahuniversity
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ትምህርት ሚኒስቴር በ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫው እስካሁን ያልተጀመረ ሲሆን መግለጫው መሰጠት እንደተጀመረ በቀጥታ የምናስተላልፍ ይሆናል።
@tikvahethiopia
📚 History Remedial Exam Questions Part Two
👉https://youtu.be/HXpPt91eSQ8
Practice smarter, revise important questions, and prepare with confidence.
Share with your friends 🤝
WE HAVE GOT YOUR BACK!!
Telegram | TikTok | YouTube | Instagram
📚 History Remedial Exam Questions Part Two
👉https://youtu.be/HXpPt91eSQ8
Practice smarter, revise important questions, and prepare with confidence.
Share with your friends 🤝
WE HAVE GOT YOUR BACK!!
Telegram | TikTok | YouTube | Instagram
#RemedialExam
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና ከሐሙስ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
የሪሚዲያል ፈተና የመግቢያ ትኬትዎን (Entrance Ticket) ያውርዱ!
➫ https://verify.ethernet.edu.et ላይ ይግቡ
➫ 'Get your entrance ticket here' የሚለውን ይጫኑ
➫ የመለያ ስምዎን (Username) እና የይለፍ ኮድዎን (Password) ያስገቡ
➫ 'Download Entrance Ticket' የሚለውን ይጫኑ
@tikvahuniversity
#RemedialExamSchedule
የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል (አቅም ማሻሻያ) ፕሮግራም ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ለአምስት ቀናት እንደሚሰጥ ይታወቃል።
በተጠቀሱት ቀናት በሁለት ፈረቃ በጠዋት እና በከሰዓት መርሐግብር የሚሰጠው የሪሚዲያል ፕሮግራም (የተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች) የፈተና መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።
@tikvahuniversity
#Update
ሀገር አቀፍ ፈተናዎች በሚሰጥባቸው የጊዜ መርሐግብር ላይ ማሻሻያ መደረጉን ሰምተናል።
በዚህም፥
➫ የሪሚዲያል ፈተና ከግንቦት 27/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም
➫ የቅድመ-ምረቃ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም
➫ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል።
ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የመርሐግብር ለውጡን ከዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ለማረጋገጥ ችሏል። የመርሐግብር ለውጥ መደረጉን የተወሰኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻቸው እያጋሩ ይገኛሉ።
@tikvahuniversity
📚Geography Entrance Exam Questions (2017)
These questions are compiled from the 2017 entrance examination to help you practice smarter and prepare with confidence.
In this video, you’ll find:
✨ Carefully selected past entrance exam questions
✨Clear and brief explanations for each question
✨ Quick reviews of the related Geography topics
✨ Important concepts frequently tested in exams
Share with your friends 🤝
We’ve got your back !
