es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 333 suscriptores, ocupando la posición 2 647 en la categoría Bloques y el puesto 2 350 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 333 suscriptores.

Según los últimos datos del 25 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -108, y en las últimas 24 horas de -4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 38.62%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.61% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 538 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 808 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 26 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 333
Suscriptores
-424 horas
-317 días
-10830 días
Archivo de publicaciones
photo content

ገዳም ውስጥ ያሉ መነኮሳትን የፊጥኝ አስሮ የሚረሸነውና በቪዲዮ ቀርጾ አረመኔነቴን ተመልከቱልኝ የሚለው የዐቢይ አሕመድ ሠራዊት ከአማራ ክልል ተጠራርጎ መውጣት ይገባዋል።
ገዳም ውስጥ ያሉ መነኮሳትን የፊጥኝ አስሮ የሚረሸነውና በቪዲዮ ቀርጾ አረመኔነቴን ተመልከቱልኝ የሚለው የዐቢይ አሕመድ ሠራዊት ከአማራ ክልል ተጠራርጎ መውጣት ይገባዋል።

photo content

"በበጀት ክልከላ የሚጣል ማንነት፣ በፈተና ብዛት የሚዝል አማራነት እኛ ዘንድ የለም" ይልኻል ቆራጡ የወልቃይት አማራ!!
"በበጀት ክልከላ የሚጣል ማንነት፣ በፈተና ብዛት የሚዝል አማራነት እኛ ዘንድ የለም" ይልኻል ቆራጡ የወልቃይት አማራ!!

ከስር ባለው ሊንክ ገብተው የቀጥታ ሥርጭታችንን መከታተል ይችላሉ።👇 https://www.youtube.com/live/192YrJpxdOE?feature=share

በሸዋ፣ በጎጃምና በወሎ አማራ ላይ የሚካሄደው ዘመቻ ዋነኛ ዓላማው የአማራ ሕዝብን ሕልውና እና ስነ ልቦና ማንኮታኮት ሲሆን ሁለተኛው ዓላማ ደግሞ ተረኛው አካል ከተባረረው ኃይል ጋር ተባብሮ በጎንደር አማራ ላይ ሊፈጽም ያሰበውን መጠነ ሰፊ የክሕደት ዘመቻ የማያደናቅፉ ሦስት ዞኖች መፍጠር መቻል ነው። እናም እልኻለሁ... የጋራ ጥቃታችንን በወረፋ ማስተናገድ እስካላቆምን ድረስ ዋጋ መክፈላችን ይቀጥላል።

photo content

ብልጽግናዎች ፓርቲያቸውን የሚቃወሙባቸው ፌክ አካውንቶች ▬▬▬▬ "ጥቅመኛ" የሚል ኮሜንት የሚያስገኙ ጽሑፎችን እየጻፈ በትክክለኛ አካውንቱ ሲለጥፍ የነበረው ልጅ ባለፈው ሰይጣን አሳስቶት ብልጽግናን ለመተቸት ደፈረ። በማግስቱም በታጣቂዎች ታፍኖ አንድ ሳምንት ታሠረ። ከእስር ቤት በወጣ ማግሥትም በማይታወቅ ሰው ሥም ባወጣው ሐሰተኛ አካውንቱ "ትክክለኛ ሐሳብ" የሚል ኮሜንት የሚያስገኙ ሐሳቦችንና መረጃዎችን ማቀበል ጀመረ።😆 ምን ለማለት ፈልጌ ነው? ➔በትክክለኛ አካውንታቸው ገዢውን ፓርቲ የሚተቹ አስር አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ሲታሠሩ አስር ሺህ ፌክ አካውንቶች ተከፍተው ያድራሉ። ➔ለስሜት ሕዋሳት የሚሰቀጥጥ ግፍ በምታስተናግድ አገር ውስጥ ግፍን ተቃወማችሁ ተብለው የሚታሠሩ ይቅርና ግፍን ይደግፉ ዘንድ የሚከፈሉ ካድሬዎች እንኳን ብሶታቸውን የሚተነፍሱበት ፌክ አካውንት ለማውጣት ይገደዳሉ። ከዚህ ጋር በተያያዘ ለምሳሌ ባለፈው አንዱን "የኮንዶሚኒየም ምርኮኛ" መንገድ ላይ አገኘሁትና "አንት የማትረባ" ማለት ስጀምር የሆዱን በሚቀባጥርበት ፈንታ የልቡን የሚተነፍስበትን ሐሰተኛ አካውንት ከፍቶ የኔን ትክክለኛ አመለካከት ማወቅ ከፈለግክ በዚህኛው አካውንት ፎሎው አድርገኝ" ይለኝ ጀመር።😆 አሁንም ምን ለማለት ፈልጌ ነው? ጠቅላይ ሚኒስትሩ እራሱ ብልጽግናን የሚቃወምበት ፌክ አካውንት እንደሚኖረው አልጠራጠርም 😂

photo content

ሕዝብን መፈተን ጥሩ ስላልሆነ አርበኛውን ልቀቁት።
+1
ሕዝብን መፈተን ጥሩ ስላልሆነ አርበኛውን ልቀቁት።

photo content

photo content

photo content

አርበኛ ዘመነ ካሴን ፍርድ ቤቱ ነጻ ሰው ነህ ብሎታል። Yalelet Wondye የንጹሑ ወንድማችን ንጽሕና በፍርድ ቤት የተረጋገጠው ግን በርካታ ሙስሊም በተጨፈጨፈበት፣ የጎጃም አርሶ አደር አመጽ በጀ
አርበኛ ዘመነ ካሴን ፍርድ ቤቱ ነጻ ሰው ነህ ብሎታል። Yalelet Wondye የንጹሑ ወንድማችን ንጽሕና በፍርድ ቤት የተረጋገጠው ግን በርካታ ሙስሊም በተጨፈጨፈበት፣ የጎጃም አርሶ አደር አመጽ በጀመረበትና ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በጄኖሳይድ በተከሰሰበት ወቅት መሆኑን ልብ ይሏል።

photo content

ለዶክተር ለጤናህ እጅጉ አሳዬ ደርቤ በማዳበሪያ ፋብሪካው ዙሪያ የሚከተሉትን ሐሳቦች መስጠት ፈለግሁ። ➼ማዳበሪያ ከውጭ አስገብቶ መሸጥ ያልቻለ ሥርዓት የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታን ያሳካል ተብሎ አይገመትም። ➼ባዶ ካዝና ተሸክሞ የሚንገታገተውን ሥርዓት በማዳበሪያ ፋብሪካ ሥም ስልሳ ቢሊዮን ብር ላመጣልህ ነው" ስትለው እንቢ ይላል ተብሎ አይታሰብም። ➼የማዳበሪያ ፋብሪካው ግንባታ ለይስሙላ ያክል ቢጀመር እንኳን "እኔ ከወረድኩ ይሄን ፋብሪካ ጨርሶ የሚያስረክብህ አይኖርም" እያለ ብአዴን አስር ዓመት ዘና ብሎ ፖለቲካ እንደሚሰራበት አያጠራጥርም። ➼የማዳበሪያ ፋብሪካ መገንባት እንደ ሌሎች አክሲዮኖች ቀላል ተግባር አይደለም። ለዚያም ነው በርካታ የውጪና የአገር ውስጥ ባለሃብቶች በሲሚንቶ ዘርፍ ሲሰማሩ የማዳበሪያ ፋብሪካን ያልሞከሩት። ካላመንክ ያዮ ሔምስፌር ላይ ሄደህ ሳይጀመር የቆመውን የማዳበሪያ ፋብሪካ ተመልከት። ➼ነዳጅ መኖሩ ሳይረጋገጥ የነዳጅ አውጪ አክሲዮን ማሕበር እንደማይመሠረት ሁሉ ለማዳበሪያ ምርት እንደ ዋና ግብዓትነት የሚያገለግሉት እንደ Phosphate rock,sulfur and Ammonia ያሉ ግብአቶች መኖራቸው በጥናት ሳይረጋገጥ ስለ ማዳበሪያ ፋብሪካ አይወራም። እናም በጥድፊያ የተሞላ ፕሮጀክትህ ወደ ብልጽግና ካዝና ስልሳ ቢሊዮን ብር ገቢ ከማድረግ የዘለለ ግብ አይኖረውም። በተረፈ ወገንህን በኢኮኖሚ ለማሳደግ ለምትሠራው በጎ ተግባር ሁሉ ትልቅ አክብሮት አለኝ።

ያልተዘመረላቸው ጀግኖች ▬▬▬▬▬▬▬▬▬ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ " " ሰለሞን ገዛኸኝ " " አዲሱ ጌታነህ " " ቤተማርያም አለማየው " " አዲሱ አርጋው " " እታለማው ➔ጭቆናን እና ባርነትን በመቃወም
ያልተዘመረላቸው ጀግኖች ▬▬▬▬▬▬▬▬▬ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ " " ሰለሞን ገዛኸኝ " " አዲሱ ጌታነህ " " ቤተማርያም አለማየው " " አዲሱ አርጋው " " እታለማው ➔ጭቆናን እና ባርነትን በመቃወምህ የተነሳ በገዢው ፓርቲ አፋኝ እጆች ተጠፍንገህ ከእስር ቤት ስትወረወር ከቤተሰቦችህ ባልተናነሰ መልኩ ጠያቂ ቤተሰብ ሆነው የምታገኛቸው፤ ➔"ጠበቆች" ከሚለው መጠሪያ ይልቅ "የነጻነት ታጋዮች" የሚለው ሐረግ የሚገልጻቸው፤ ➔ከእስር ቤት በላይ ችሎት ላይ መገኘት እጅግ አሰልች ቢሆነም ዓመቱን ሙሉ ችሎት ላይ የማታጣቸው፤ ➔ማንኛውም የፖለቲካ እስረኛ ያለምንም ክፍያ ጥብቅና የሚያቆማቸው፤ ➔ሕዝባዊ እውቅናም ሆነ ግላዊ ጥቅም በሌለው የትግል መስመር ውስጥ ተሰማርተው ብሎም ለፍትሕ ለሚሟገቱ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች፤ ጸሐፊዎችና ፖለቲከኞች ተሟጋች ሆነው ችሎት ለችሎት መንከራተት የማይደክማቸው፤ . . . ሼር እና ፖስት በማድረግ አክብሮታችንን እንግለጽላቸው።

በገበሬዎች ምናብ ትናንትና ሲታሰብ!! አሳዬ ደርቤ በዘመነ ኢሕአዴግ ለብአዴን አመራሮች እጅግ ከባዱ ተግባር ለማዳበሪያ ግዢ ከፍተኛ የበጀት ድጎማ በማድረጉ የሚታወቀው የግብርና ሚኒስትር ከክልሉ የግዢ ፍላጎት በላይ በሆነ መልኩ በኮታ ደልድሎ በዝቅተኛ ዋጋና በብድር በገፍ የሚልከውን ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ማሠራጨት መቻል ነበረ። የአርሶ አደሩም ቅሬታ "ሁለት ኩንታል ማዳበሪያ ጠይቄ አራት ኩንታል አምጥተው አሸከሙኝ" የሚል ነበረ። ዛሬሳ? ➼ዛሬማ...ግብርና መር ፖሊሲው ቀርቶ "መናፈሻና ፓርክ መር ፖሊሲ" እውን በመሆኑ ምርጥ ዘር በኩንታል ሲከፋፈሉ የኖሩ አርሶ አደሮች በስንት ፍለጋ ከገበያ ያገኙትን ምርጥ ዘር በፍሬ ቆጥረው እየተከፋፈሉ ነው። ➼ዛሬማ..... ከምርምር ጣቢያዎች የሚወጡ ምርጥ ዘሮችን ሲያባዙ የነበሩ የዘር ብዜት ጣቢያዎች ፈርሰው ዘርን መሠረት ባደረገ ጥቃት የሚሳደዱ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻቸውን ጥለው መከራቸውን እየበሉ ነው። ➽ዛሬማ....በተፈጥሮ ሐብት ዘመቻ ሲሰሩ የኖሩ የውሃ ማቆር ትሬንቾች ምሽጎች ሆነው ደም እየታቆረባቸው ነው። ➼ዛሬማ... የክልላቸው መንግሥት ቀበሌያቸው ድረስ አጓጉዞ ማዳበሪያ ሲያቀርብላቸው የኖሩ ገበሬዎች ክልል ድረስ ሄደው "የማዳበሪያ ያለህ" እያሉ ነው። ➼ዛሬማ...በመከላከያ ኢንጂነሪንግ የሚመረቱና እንደ ታይሬጀርና BBM ያሉ የተሻሻሉ የእርሻ ቴክኖሎጂዎችን ሲወስዱ የነበሩ አርሶአደሮች በBM እና ሞርታር እየተንገበገቡ ነው። ➼ዛሬማ... ከማሳቸው የተፈናቀሉ፣ በርሐብ አለንጋ የሚቆሉና 'እሕል እሕል' የሚሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮች "በመኸር ለሚያመርተው አርሶ አደር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ማቅረብ ያልቻለው መንግሥት በበጋ ያመረተውን ስንዴ Export ማድረጉን ሲያወራ ርሐብ ያደረቀውን ከንፈራቸውን በግርምት ከፍተው "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እያሉ ነው። Share

በቀጣይ ደግሞ ቪላ ቤቶችን አፍርሶ "የጽንፈኞች ማዕከል ስለሆኑ ነው" "ይልኻል። 😁 መስጊዶችስ የፈረሱት ስለምን ይሆን?
በቀጣይ ደግሞ ቪላ ቤቶችን አፍርሶ "የጽንፈኞች ማዕከል ስለሆኑ ነው" "ይልኻል። 😁 መስጊዶችስ የፈረሱት ስለምን ይሆን?

ዶክተር ሐይለ ማሪያም ይባላል። "ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ባለማቅረብ ፥ የአማራ ገበሬዎችን ማስራብ" የሚለውን የብልጽግና ፕሮጀክት ተግባራዊ ያደርግ ዘንዳ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ሆኖ የተሾመ
ዶክተር ሐይለ ማሪያም ይባላል። "ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ባለማቅረብ ፥ የአማራ ገበሬዎችን ማስራብ" የሚለውን የብልጽግና ፕሮጀክት ተግባራዊ ያደርግ ዘንዳ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ሆኖ የተሾመ ሰው ነው። እናም እንላለን.... "የአማራ ገበሬ ጅራፉን ይዞ እየመጣልህ ስለሆነ ሥልጣንህን አስረክበህ ተሰወር።