ar
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie

تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 351 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 646 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 354 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 351 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 22 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -133، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.76‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 11.78‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 562 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 691 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 34.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.

14 351
المشتركون
-324 ساعات
-387 أيام
-13330 أيام
أرشيف المشاركات
ከስር ባለው ሊንክ ገብተው የቀጥታ ሥርጭታችንን መከታተል ይችላሉ።👇 https://www.youtube.com/live/192YrJpxdOE?feature=share

በሸዋ፣ በጎጃምና በወሎ አማራ ላይ የሚካሄደው ዘመቻ ዋነኛ ዓላማው የአማራ ሕዝብን ሕልውና እና ስነ ልቦና ማንኮታኮት ሲሆን ሁለተኛው ዓላማ ደግሞ ተረኛው አካል ከተባረረው ኃይል ጋር ተባብሮ በጎንደር አማራ ላይ ሊፈጽም ያሰበውን መጠነ ሰፊ የክሕደት ዘመቻ የማያደናቅፉ ሦስት ዞኖች መፍጠር መቻል ነው። እናም እልኻለሁ... የጋራ ጥቃታችንን በወረፋ ማስተናገድ እስካላቆምን ድረስ ዋጋ መክፈላችን ይቀጥላል።

photo content

ብልጽግናዎች ፓርቲያቸውን የሚቃወሙባቸው ፌክ አካውንቶች ▬▬▬▬ "ጥቅመኛ" የሚል ኮሜንት የሚያስገኙ ጽሑፎችን እየጻፈ በትክክለኛ አካውንቱ ሲለጥፍ የነበረው ልጅ ባለፈው ሰይጣን አሳስቶት ብልጽግናን ለመተቸት ደፈረ። በማግስቱም በታጣቂዎች ታፍኖ አንድ ሳምንት ታሠረ። ከእስር ቤት በወጣ ማግሥትም በማይታወቅ ሰው ሥም ባወጣው ሐሰተኛ አካውንቱ "ትክክለኛ ሐሳብ" የሚል ኮሜንት የሚያስገኙ ሐሳቦችንና መረጃዎችን ማቀበል ጀመረ።😆 ምን ለማለት ፈልጌ ነው? ➔በትክክለኛ አካውንታቸው ገዢውን ፓርቲ የሚተቹ አስር አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ሲታሠሩ አስር ሺህ ፌክ አካውንቶች ተከፍተው ያድራሉ። ➔ለስሜት ሕዋሳት የሚሰቀጥጥ ግፍ በምታስተናግድ አገር ውስጥ ግፍን ተቃወማችሁ ተብለው የሚታሠሩ ይቅርና ግፍን ይደግፉ ዘንድ የሚከፈሉ ካድሬዎች እንኳን ብሶታቸውን የሚተነፍሱበት ፌክ አካውንት ለማውጣት ይገደዳሉ። ከዚህ ጋር በተያያዘ ለምሳሌ ባለፈው አንዱን "የኮንዶሚኒየም ምርኮኛ" መንገድ ላይ አገኘሁትና "አንት የማትረባ" ማለት ስጀምር የሆዱን በሚቀባጥርበት ፈንታ የልቡን የሚተነፍስበትን ሐሰተኛ አካውንት ከፍቶ የኔን ትክክለኛ አመለካከት ማወቅ ከፈለግክ በዚህኛው አካውንት ፎሎው አድርገኝ" ይለኝ ጀመር።😆 አሁንም ምን ለማለት ፈልጌ ነው? ጠቅላይ ሚኒስትሩ እራሱ ብልጽግናን የሚቃወምበት ፌክ አካውንት እንደሚኖረው አልጠራጠርም 😂

photo content

ሕዝብን መፈተን ጥሩ ስላልሆነ አርበኛውን ልቀቁት።
+1
ሕዝብን መፈተን ጥሩ ስላልሆነ አርበኛውን ልቀቁት።

photo content

photo content

photo content

አርበኛ ዘመነ ካሴን ፍርድ ቤቱ ነጻ ሰው ነህ ብሎታል። Yalelet Wondye የንጹሑ ወንድማችን ንጽሕና በፍርድ ቤት የተረጋገጠው ግን በርካታ ሙስሊም በተጨፈጨፈበት፣ የጎጃም አርሶ አደር አመጽ በጀ
አርበኛ ዘመነ ካሴን ፍርድ ቤቱ ነጻ ሰው ነህ ብሎታል። Yalelet Wondye የንጹሑ ወንድማችን ንጽሕና በፍርድ ቤት የተረጋገጠው ግን በርካታ ሙስሊም በተጨፈጨፈበት፣ የጎጃም አርሶ አደር አመጽ በጀመረበትና ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በጄኖሳይድ በተከሰሰበት ወቅት መሆኑን ልብ ይሏል።

photo content

ለዶክተር ለጤናህ እጅጉ አሳዬ ደርቤ በማዳበሪያ ፋብሪካው ዙሪያ የሚከተሉትን ሐሳቦች መስጠት ፈለግሁ። ➼ማዳበሪያ ከውጭ አስገብቶ መሸጥ ያልቻለ ሥርዓት የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታን ያሳካል ተብሎ አይገመትም። ➼ባዶ ካዝና ተሸክሞ የሚንገታገተውን ሥርዓት በማዳበሪያ ፋብሪካ ሥም ስልሳ ቢሊዮን ብር ላመጣልህ ነው" ስትለው እንቢ ይላል ተብሎ አይታሰብም። ➼የማዳበሪያ ፋብሪካው ግንባታ ለይስሙላ ያክል ቢጀመር እንኳን "እኔ ከወረድኩ ይሄን ፋብሪካ ጨርሶ የሚያስረክብህ አይኖርም" እያለ ብአዴን አስር ዓመት ዘና ብሎ ፖለቲካ እንደሚሰራበት አያጠራጥርም። ➼የማዳበሪያ ፋብሪካ መገንባት እንደ ሌሎች አክሲዮኖች ቀላል ተግባር አይደለም። ለዚያም ነው በርካታ የውጪና የአገር ውስጥ ባለሃብቶች በሲሚንቶ ዘርፍ ሲሰማሩ የማዳበሪያ ፋብሪካን ያልሞከሩት። ካላመንክ ያዮ ሔምስፌር ላይ ሄደህ ሳይጀመር የቆመውን የማዳበሪያ ፋብሪካ ተመልከት። ➼ነዳጅ መኖሩ ሳይረጋገጥ የነዳጅ አውጪ አክሲዮን ማሕበር እንደማይመሠረት ሁሉ ለማዳበሪያ ምርት እንደ ዋና ግብዓትነት የሚያገለግሉት እንደ Phosphate rock,sulfur and Ammonia ያሉ ግብአቶች መኖራቸው በጥናት ሳይረጋገጥ ስለ ማዳበሪያ ፋብሪካ አይወራም። እናም በጥድፊያ የተሞላ ፕሮጀክትህ ወደ ብልጽግና ካዝና ስልሳ ቢሊዮን ብር ገቢ ከማድረግ የዘለለ ግብ አይኖረውም። በተረፈ ወገንህን በኢኮኖሚ ለማሳደግ ለምትሠራው በጎ ተግባር ሁሉ ትልቅ አክብሮት አለኝ።

ያልተዘመረላቸው ጀግኖች ▬▬▬▬▬▬▬▬▬ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ " " ሰለሞን ገዛኸኝ " " አዲሱ ጌታነህ " " ቤተማርያም አለማየው " " አዲሱ አርጋው " " እታለማው ➔ጭቆናን እና ባርነትን በመቃወም
ያልተዘመረላቸው ጀግኖች ▬▬▬▬▬▬▬▬▬ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ " " ሰለሞን ገዛኸኝ " " አዲሱ ጌታነህ " " ቤተማርያም አለማየው " " አዲሱ አርጋው " " እታለማው ➔ጭቆናን እና ባርነትን በመቃወምህ የተነሳ በገዢው ፓርቲ አፋኝ እጆች ተጠፍንገህ ከእስር ቤት ስትወረወር ከቤተሰቦችህ ባልተናነሰ መልኩ ጠያቂ ቤተሰብ ሆነው የምታገኛቸው፤ ➔"ጠበቆች" ከሚለው መጠሪያ ይልቅ "የነጻነት ታጋዮች" የሚለው ሐረግ የሚገልጻቸው፤ ➔ከእስር ቤት በላይ ችሎት ላይ መገኘት እጅግ አሰልች ቢሆነም ዓመቱን ሙሉ ችሎት ላይ የማታጣቸው፤ ➔ማንኛውም የፖለቲካ እስረኛ ያለምንም ክፍያ ጥብቅና የሚያቆማቸው፤ ➔ሕዝባዊ እውቅናም ሆነ ግላዊ ጥቅም በሌለው የትግል መስመር ውስጥ ተሰማርተው ብሎም ለፍትሕ ለሚሟገቱ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች፤ ጸሐፊዎችና ፖለቲከኞች ተሟጋች ሆነው ችሎት ለችሎት መንከራተት የማይደክማቸው፤ . . . ሼር እና ፖስት በማድረግ አክብሮታችንን እንግለጽላቸው።

በገበሬዎች ምናብ ትናንትና ሲታሰብ!! አሳዬ ደርቤ በዘመነ ኢሕአዴግ ለብአዴን አመራሮች እጅግ ከባዱ ተግባር ለማዳበሪያ ግዢ ከፍተኛ የበጀት ድጎማ በማድረጉ የሚታወቀው የግብርና ሚኒስትር ከክልሉ የግዢ ፍላጎት በላይ በሆነ መልኩ በኮታ ደልድሎ በዝቅተኛ ዋጋና በብድር በገፍ የሚልከውን ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ማሠራጨት መቻል ነበረ። የአርሶ አደሩም ቅሬታ "ሁለት ኩንታል ማዳበሪያ ጠይቄ አራት ኩንታል አምጥተው አሸከሙኝ" የሚል ነበረ። ዛሬሳ? ➼ዛሬማ...ግብርና መር ፖሊሲው ቀርቶ "መናፈሻና ፓርክ መር ፖሊሲ" እውን በመሆኑ ምርጥ ዘር በኩንታል ሲከፋፈሉ የኖሩ አርሶ አደሮች በስንት ፍለጋ ከገበያ ያገኙትን ምርጥ ዘር በፍሬ ቆጥረው እየተከፋፈሉ ነው። ➼ዛሬማ..... ከምርምር ጣቢያዎች የሚወጡ ምርጥ ዘሮችን ሲያባዙ የነበሩ የዘር ብዜት ጣቢያዎች ፈርሰው ዘርን መሠረት ባደረገ ጥቃት የሚሳደዱ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻቸውን ጥለው መከራቸውን እየበሉ ነው። ➽ዛሬማ....በተፈጥሮ ሐብት ዘመቻ ሲሰሩ የኖሩ የውሃ ማቆር ትሬንቾች ምሽጎች ሆነው ደም እየታቆረባቸው ነው። ➼ዛሬማ... የክልላቸው መንግሥት ቀበሌያቸው ድረስ አጓጉዞ ማዳበሪያ ሲያቀርብላቸው የኖሩ ገበሬዎች ክልል ድረስ ሄደው "የማዳበሪያ ያለህ" እያሉ ነው። ➼ዛሬማ...በመከላከያ ኢንጂነሪንግ የሚመረቱና እንደ ታይሬጀርና BBM ያሉ የተሻሻሉ የእርሻ ቴክኖሎጂዎችን ሲወስዱ የነበሩ አርሶአደሮች በBM እና ሞርታር እየተንገበገቡ ነው። ➼ዛሬማ... ከማሳቸው የተፈናቀሉ፣ በርሐብ አለንጋ የሚቆሉና 'እሕል እሕል' የሚሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮች "በመኸር ለሚያመርተው አርሶ አደር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ማቅረብ ያልቻለው መንግሥት በበጋ ያመረተውን ስንዴ Export ማድረጉን ሲያወራ ርሐብ ያደረቀውን ከንፈራቸውን በግርምት ከፍተው "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እያሉ ነው። Share

በቀጣይ ደግሞ ቪላ ቤቶችን አፍርሶ "የጽንፈኞች ማዕከል ስለሆኑ ነው" "ይልኻል። 😁 መስጊዶችስ የፈረሱት ስለምን ይሆን?
በቀጣይ ደግሞ ቪላ ቤቶችን አፍርሶ "የጽንፈኞች ማዕከል ስለሆኑ ነው" "ይልኻል። 😁 መስጊዶችስ የፈረሱት ስለምን ይሆን?

ዶክተር ሐይለ ማሪያም ይባላል። "ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ባለማቅረብ ፥ የአማራ ገበሬዎችን ማስራብ" የሚለውን የብልጽግና ፕሮጀክት ተግባራዊ ያደርግ ዘንዳ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ሆኖ የተሾመ
ዶክተር ሐይለ ማሪያም ይባላል። "ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ባለማቅረብ ፥ የአማራ ገበሬዎችን ማስራብ" የሚለውን የብልጽግና ፕሮጀክት ተግባራዊ ያደርግ ዘንዳ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ሆኖ የተሾመ ሰው ነው። እናም እንላለን.... "የአማራ ገበሬ ጅራፉን ይዞ እየመጣልህ ስለሆነ ሥልጣንህን አስረክበህ ተሰወር።

photo content

አገዛዙ ቤተክርስቲያንን እና ገዳማትን የሚመዘብረው ሲኖዶሱን ከመዳፉ ውስጥ አስቀምጦ ነው። መስጊድ የሚያፈርሰው መጅሊሱን ተቆጣጥሮ ነው።
አገዛዙ ቤተክርስቲያንን እና ገዳማትን የሚመዘብረው ሲኖዶሱን ከመዳፉ ውስጥ አስቀምጦ ነው። መስጊድ የሚያፈርሰው መጅሊሱን ተቆጣጥሮ ነው።

አቢሲኒያ ባንክ የማይካድራ ቅርንጫፍን በመቀሌ ዲስትሪክት ስር አድርጎ ያወጣው የሥራ ማስታወቂያ...
+1
አቢሲኒያ ባንክ የማይካድራ ቅርንጫፍን በመቀሌ ዲስትሪክት ስር አድርጎ ያወጣው የሥራ ማስታወቂያ...

ጌታቸው ረዳ "ህውሓት ትጥቅ አስረከበ የሚለው ዜና ድራማ መሆኑን.... ጥበብ በተሞላበት መንገድ የአማራን ልዩ ሃይል ማፍረስ መቻሉን... እንዲሁም ባሁኑ ሰዓት በአማራ ክልል ምንም አይነት የተደራጀ
ጌታቸው ረዳ "ህውሓት ትጥቅ አስረከበ የሚለው ዜና ድራማ መሆኑን.... ጥበብ በተሞላበት መንገድ የአማራን ልዩ ሃይል ማፍረስ መቻሉን... እንዲሁም ባሁኑ ሰዓት በአማራ ክልል ምንም አይነት የተደራጀ ሃይል አለመኖሩን..." ተናገረ የሚል መረጃ ሲንሸራሸር እያየሁ ነው። እኔ ግን እላለሁኝ... የአማራ ልዩ-ሃይልን ያፈረሰው ብአዴን የተባለ ጸረ ሕዝብ ድርጅት እንጂ የጌታቸው ረዳ ጥበብ አይደለም። ፋኖን በከባድ መሣሪያ የሚያስደበድበውም የኦነግ ቅጥረኛ የሆነው የብአዴን አመራር እንጂ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ስላልሆነ የዶክተር ይልቃል ካድሬ በክልሉ ሕዝብ ሕልውና ላይ የፈጸመውን አስነዋሪ ድርጊት ነጥቆ ጌታቸው ረዳ ማቅራራቱ ልክ አይደለም። በተረፈ ልዩ ሃይል ሲበተን ሕዝባዊ ሃይል እንደሚወለድ አያጠራጥርም።

Assaye Derbie - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @asayede