Grace Commission
Ir al canal en Telegram
2 536
Suscriptores
-324 horas
-67 días
-530 días
Archivo de publicaciones
2 536
መሪነት እጅግ አስቸጋሪ ነው። እንዲህም ሆኖ በጥሩ ሁኔታ ላደርገው እፈልጋለሁ። ከሁሉ በላይ ደግሞ፣ በኢየሱስ የአመራር ዘይቤ እየመራሁ መሆኔን ርግጠኛ መሆን እሻለሁ። _ Matt's Story
2 536
አንድ ወንድማችን ... የኑሮ ውድነቱ ሲጨምር እምነት ጨምሩ አለን። ስለዚህ
✍️ እምነት እንጨምር!
✍️ የገቢ ምንጭ (የሥራ ዘርፍ) እንጨምር!
✍️ ትጋት እንጨምር!
✍️ ወጪ እንቀንስ!
ወገኖቼ፣ ኑሮው ካሰብነው መፈናፈኛ ያሳጣናል። አኗሪውን እግዚአብሔርን ካሰብነው ግን መላ አናጣም! "መኖሪያህ የዘላለም አምላክ ነው" እንደ ተባለ፣ በርሱ ዐርፈን እንኑር!
2 536
#የዕለቱ #ቃል
"በተስፋ ደስተኞች ሁኑ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ።" _ ሮሜ 12፥12
"አንዳንድ ጊዜ የመኖር ቊልፍ፣ ጥርስን ነክሶ ውጫዊ ሁኔታዎች ምንም ቢሆኑ እግዚአብሔር እንደሚረዳ በማመን መቀጠል ነው። ከመሰበር ይልቅ በተስፋ በኲል ደስታን ለማግኘት መምረጥ፣ በፈተና ጊዜ ለመታገስ መምረጥና በጸሎት ለመጽናት መምረጥ፣ ኢየሱስን ከሞት ያስነሣው እግዚአብሔር፣ የእኛንም ሁኔታ ሊቀይር እንደሚችል ማመናችንን የምናሳይባቸው ውሳኔዎች ናቸው።" _ ዐዲሱ መደበኛ ትርጒም
2 536
እግዚአብሔር፣ ኢየሱስን መስቀል ላይ ትቶት ነበረ፤ ፊቱን አዙሮበት ነበረ። (ማቴ. 27፥46) መቃብር ውስጥ ግን አልተወውም፤ የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው። (ሐዋ. 2፥24)።
2 536
#የመንፈስ_ቅዱስ_ነገር
የአብዛኞቻችን ክርክር/ውይይት፣ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ላይ ያጠነጠነ ነው። ራሱ መንፈስ ቅዱስ ላይ የሚደረጉ ጥናቶች/ውይይቶች፣ እንኳን አሁን ድሮም ስስ/ጥቂት ናቸው። በነገረ መንፈስ ቅዱስ ዙሪያ፣ ንባባችንን የሚዘውሩ/ዕይታችንን የሚሞግቱ በአገርኛ ቋንቋዎች የተተየቡ መጻሕፍት ያስፈልጉናል። እንደዚህ ዐይነት ሙግት የያዙ እና ወደ ሰጪው/ምንጩ የሚመልሱ ሦስት መጻሕፍት፣ በሚቀጥለው ግማሽ ዓመት ይወጣሉ። እግዚአብሔር ይመስገን!
2 536
እኛ የትንሣኤ ማኅበረ ሰብ ነን፤ በኢየሱስ መነሣት የተነሣን/መነሣታችንን ያረጋገጥን። የትንሣኤ የልቦና ውቅር (ትንሣኤ ልቦና/የትንሣኤ ሥነ ልቦና) ልናዳብር ይገባል! እንደ ወንጌል ማኅበረ ሰብ ይህን የትንሣኤ ተስፋ (የኛን ብቻ ሳይሆን ለከንቱነት የተገዛውን ፍጥረት መታደስ) እንጠባበቃለን። ትንሣኤን ከበዓል ዕሳቤ አውጥተን በሕይወትነቱ እንረዳለን። ትንሣኤ በዓል ወይም ቀን ወይም የአንድ ሰው ስም ሳይሆን የጌታ ኢየሱስ ማንነት ነው።
2 536
"ክርስትና፣ የክርስቶስን ማንነት እና ተልእኮ ማእከል ያደረገ ነው። ክርስትና፣ እግዚአብሔር በልጁ በኩል የሠራውን ሥራና ዓለምን የወደደበትን መውደድ መግለጫ መንገድ ነው።"
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
