ch
Feedback
Grace Commission

Grace Commission

前往频道在 Telegram

የታረቀ ማኅበረ ሰብ _ 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥20

显示更多
2 536
订阅者
-324 小时
-67
-530
帖子存档
#ወንጌል ለሁሉም፤ ሁሉም #ለወንጌል!

photo content

photo content

መሪነት እጅግ አስቸጋሪ ነው። እንዲህም ሆኖ በጥሩ ሁኔታ ላደርገው እፈልጋለሁ። ከሁሉ በላይ ደግሞ፣ በኢየሱስ የአመራር ዘይቤ እየመራሁ መሆኔን ርግጠኛ መሆን እሻለሁ። _ Matt's Story

አንድ ወንድማችን ... የኑሮ ውድነቱ ሲጨምር እምነት ጨምሩ አለን። ስለዚህ ✍️ እምነት እንጨምር! ✍️ የገቢ ምንጭ (የሥራ ዘርፍ) እንጨምር! ✍️ ትጋት እንጨምር! ✍️ ወጪ እንቀንስ! ወገኖቼ፣ ኑሮው ካሰብነው መፈናፈኛ ያሳጣናል። አኗሪውን እግዚአብሔርን ካሰብነው ግን መላ አናጣም! "መኖሪያህ የዘላለም አምላክ ነው" እንደ ተባለ፣ በርሱ ዐርፈን እንኑር!

#የዕለቱ #ቃል "በተስፋ ደስተኞች ሁኑ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ።" _ ሮሜ 12፥12 "አንዳንድ ጊዜ የመኖር ቊልፍ፣ ጥርስን ነክሶ ውጫዊ ሁኔታዎች ምንም ቢሆኑ እግዚአብሔር እንደሚረዳ በማመን መቀጠል ነው። ከመሰበር ይልቅ በተስፋ በኲል ደስታን ለማግኘት መምረጥ፣ በፈተና ጊዜ ለመታገስ መምረጥና በጸሎት ለመጽናት መምረጥ፣ ኢየሱስን ከሞት ያስነሣው እግዚአብሔር፣ የእኛንም ሁኔታ ሊቀይር እንደሚችል ማመናችንን የምናሳይባቸው ውሳኔዎች ናቸው።" _ ዐዲሱ መደበኛ ትርጒም

እግዚአብሔር፣ ኢየሱስን መስቀል ላይ ትቶት ነበረ፤ ፊቱን አዙሮበት ነበረ። (ማቴ. 27፥46) መቃብር ውስጥ ግን አልተወውም፤ የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው። (ሐዋ. 2፥24)።

ኢየሱስ ሕያውም (ራእይ 1፥18)፥ ያውም (ዕብ. 13፥8) ነው!

#የመንፈስ_ቅዱስ_ነገር የአብዛኞቻችን ክርክር/ውይይት፣ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ላይ ያጠነጠነ ነው። ራሱ መንፈስ ቅዱስ ላይ የሚደረጉ ጥናቶች/ውይይቶች፣ እንኳን አሁን ድሮም ስስ/ጥቂት ናቸው። በነገረ መንፈስ ቅዱስ ዙሪያ፣ ንባባችንን የሚዘውሩ/ዕይታችንን የሚሞግቱ በአገርኛ ቋንቋዎች የተተየቡ መጻሕፍት ያስፈልጉናል። እንደዚህ ዐይነት ሙግት የያዙ እና ወደ ሰጪው/ምንጩ የሚመልሱ ሦስት መጻሕፍት፣ በሚቀጥለው ግማሽ ዓመት ይወጣሉ። እግዚአብሔር ይመስገን!

እኛ የትንሣኤ ማኅበረ ሰብ ነን፤ በኢየሱስ መነሣት የተነሣን/መነሣታችንን ያረጋገጥን። የትንሣኤ የልቦና ውቅር (ትንሣኤ ልቦና/የትንሣኤ ሥነ ልቦና) ልናዳብር ይገባል! እንደ ወንጌል ማኅበረ ሰብ ይህን የትንሣኤ ተስፋ (የኛን ብቻ ሳይሆን ለከንቱነት የተገዛውን ፍጥረት መታደስ) እንጠባበቃለን። ትንሣኤን ከበዓል ዕሳቤ አውጥተን በሕይወትነቱ እንረዳለን። ትንሣኤ በዓል ወይም ቀን ወይም የአንድ ሰው ስም ሳይሆን የጌታ ኢየሱስ ማንነት ነው።

ክርስቶስ አንድን ሰው ሲጠራ የሚያቀርብለት ጥሪ፣ "ና እና ሙት" የሚል ጥሪ ነው!   _ ዲትሪክ ቦንሆፈር

"ክርስትና፣ የክርስቶስን ማንነት እና ተልእኮ ማእከል ያደረገ ነው። ክርስትና፣ እግዚአብሔር በልጁ በኩል የሠራውን ሥራና ዓለምን የወደደበትን መውደድ መግለጫ መንገድ ነው።"

ጌታዬ ኢየሱስን፣ መስቀል ላይ ያወጣውና ያቆየው ችንካሩ ሳይሆን ለእኔ ያለው መሥዋዕታዊ እና ዘላለማዊ ፍቅር ነው!

photo content

photo content