Zeraf Books
Ir al canal en Telegram
Your #1 Source For Ethiopian Books Shipping Worldwide 🇺🇸🇨🇦🇩🇪🇬🇧🇰🇷🇮🇹~🌎 & Delivering Locally. Work Phone 📲 +251985333153 Inbox Your Inquiries To @Zerafb
Mostrar más7 853
Suscriptores
+124 horas
-107 días
-1930 días
Archivo de publicaciones
7 853
📖 አቶባዮግራፊ ~ ፊታውራሪ ተክለሐዋርያት
📖 የትውልድ አደራ ~ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም
📖 የሕይወቴ ታሪክ ~ ተክለጻድቅ መኩሪያ
📖 ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ ~ አፄ ኃይለሥላሴ
📖 ኢትዮጵያ ሀገሬና ትዝታዬ ~ በላይ ግደይ
📖 ሞት አምባ ደርሶ መልስ ~ ኃይለማርያም መንገሻ
📖 አንዳፍታ ላውጋችሁ ~ ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ
7 853
"ቡናዬ እስኪሰክን" ዝርጓ ጣፋጭ እንጎቻ!
(ደረጀ በላይነህ)
ይህቺን "ቡናዬ እስኪሰክን"የምትል መጽሐፍ አነበብኳት።በጣም ማራኪና ውብ ሆና አግኝታለሁ። መጽሐፏ ብዙ ነገሮቿ ዝርግ ሆነው ሲምቦሊክ ናቸው።ዘውጓ ግለታሪካዊ ልቦለድ ሆኖ ፣ነባሩና ዘመናዊው እውነታዊ ልቦለድ ውስጥ እንዲመደብ የሚያደርጉ ብዙ አላባውያን አሉ።
ጭብጡ የዘመን አሻራ ማኅተም ያረፈበት ጥልቅ ምልከታ ውስጥ አንድ የትራጀዲ ኪስ የተበጀለት፣ግን ደግሞ ሳቅ የተርከፈከፈበት በውበት ጸዳል ያጌጠና የተከፈፈ ነው።
ደራሲው ቤተማርያም ተሾመ ከተለያዩ ዘመናትና የታሪክ ጥጋጥግ የሰበሰባቸው በርካታ የጥበብ የፖለቲካና የማኅበራዊ ሕይወት ስልቶችን በፈረቃ የሚያጫውትበት ስልት ፈጥሯል።
ከሁሉ ከሁሉ የገረመኝና ልቤ ላይ በሕመም ታትሞ የቀረውና እንባዬን እንደጠጠር ያጠነከረው(የማይሟሟ እንባ ያደረገው) በየዘመኑ የፖለቲካ መዋቅሮች ስል ሰይፍ ተከትፈው አልለያይ ያሉትና በደም ሐረግ ተንጠልጥለው የቀሩት የሰሜኑ፣የደቡቡና የሌላዊ ኢትዮጵያዊ ልቦች ናቸው።
ትረካዋም በዘመኑ ዐውድ፣በትውልዱ መልክ አንዳንዴ አማርኛና እንግሊዝኛን በአንድ ዐረፍተ ነገር እያዛነቀ የሚሄደው "ኮድ ሚክሲንግ" ሆኖ፣አርስቶትል ዘመን መነሻ አድርጎ እስካሁን የዘለቀው "ስካርሊያን"የተባለው የአንድ ቀን ውሎ ትረካ ነው። ቅርጹ ከዲያሪ ጋር የሚመሳሰልባቸው የጋራ ነጥቦች ቢኖሩም የተለየና ብቻውን የቆመ ከመሆኑ ባሻገር ደራሲው መሙን ጠብቆ ከግብ አድርሶታል።
ስለዚህ በለሰለሰ ቃላት፣ጣሪያ ባልነኩ ዘይቤዎች እንደ ዘይት የሚፈስሰው የትረካው ጉዞ በውስጡ የያዛቸውን የዘመኑን መልኮች በሚገባ ስላዘለ ሲነበብ ይጥማል፣ብዙ ጓዳ ይፈትሻል።በርካታ ሥነ ልቦናዊ ንትርኮችንም አደባባይ ላይ ያሰጣል።በግልና በሀገር ደረጃ የሚያሙንን ቁስሎች እያባበለ ያወራናል።ገጸባህርያቱን ከየአጠገባችን ወስዶ በተሰፋንበት የደም ገመድ ውስጥ የሚፈስሰውን አንድነት ከልባችን ቆስቁሶ እንድንሞቀው ይጋብዘናል።በተሳሳተ ትርክት የተበታተነውን ዝምድና "እንዲህ ነን"በሚል አዝመራውን ከጎንደር፣አታክልቲን ከትግራይ፣እነማቴዎስን ከደቡብ አምጥቶ የተበተነውን የታሪክ ዶቃዎች አንድ ላይ ሰክቶ ጌጥ የሚያደርገው ብልህ ይጋብዛል።
በዚህ መሐል ገጸባህርይው በቤቱ፣በጎረቤቱና በግል ሕይወቱ ሲፈተን፣ሕሊናው ሲሞግተውና ጥርሱን ስሎ ሲነክሰው በካውንስሊንግ ሳይኮሎጂ ላይ የሚነበቡት ራስን የመከላከያ ጋሻዎችያነሣል።
መጽሐፉ በዕለት ተዕለት ቋንቋ ቢጻፍም ሰንሰለቱን የጠበቀ ትስስር ስላለው ውብና ሳቢ ነው።
እውነት ለመናገር ሳይጎረብጥ ይነበባል። አልፎ አልፎ የሰው ስም ስህተት (ለምሳሌ ጆን ሚልተንን፣በሐሚልተን መቀየር፣የደርግ አባቶች"ብሎ ጄነራል አማን አምዶንን መጥቀስ የመሳሰሉ ጥቂትና ተራ ሕጸጾች በስተቀር የሚወደድ መጽሐፍ ነው።
በግሌ እንዳየሁት አጨራረሱ እንደ sermon ዝግጅት ከአሁን ጋር ለማገጣጠም መሞከሩን አልደግፍም። ዞሮ ዞሮ ደስ ብሎኝ ተገርሜ አንብቤዋለሁ። በዘመናችን ብቅ ብቅ ያሉ ችቦዎች የሀገራችንን የጥበብ አድማስ እንደሚያደምቁትም አሳይቶኛል።
